TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Update

የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።

ዶ/ር ለገሰ ፥ መንግስት ለያዘው ሀገራዊ ምክክርና ብሄራዊ መግባባት ለመፍጠር ሁሉን አካታች የሆነ ውይይት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል ብለዋል።

ይህን ሀገራዊ አንድነት ለማምጣትም ብዙ ተከታይ ያላቸውን እስረኞች ክስ ማቋረጥ ማስፈለጉን ነው የተናገሩት።

በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ፣ የተመቻቸ ፖለቲካዊ ሁኔታን ለመዘርጋት ፣ዋስትና ያለው ዲሞክራሲ ለመገንባት ያለመ ነው ውሳኔው ብለዋል።

ውሳኔው በየደረጃው የሚመለከተው አካል ተወያይቶበት የወሰነው ሲሆን ዘላቂውን የሀገር ጥቅም ከግምት ያስገባም መሆኑን ነው ሚንስትሩ ያነሱት።

ዶ/ር ለገሰ ፥ መንግስት የእነዚህን ግለሰቦች ክስ እንዲቋረጥ ሲያደርግ ግለሰቦቹ ለሀገራዊ መግባባት ያላቸውን ሚና አምኖበት ስለሆነ ለሰላማዊ ምክክር የተሰጣቸውን እድል እንዲጠቀሙበትም ጥሪ ቀርቦላቸዋል ብለዋል።

#ኤኤምኤን

@tikvahethiopia