TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሳዛኝ ዜና!

በድሬዳዋ ከትናንት በስተያ ምሽት አንስቶ እስከ ትላንት በቀጠለ #ግጭት የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን የሆስፒታል ምንጮች እና የዓይን ምስክሮች ለዶቼቬለ/ለጀርመን ድምፅ ራድዮ/ ተናገሩ። በዚሁ በተለምዶ ደቻቱ እና 5ተኛ ተብለው በሚጠሩ ሰፈሮች ወጣቶች መካከል ተፈጠረ በተባለው ግጭት #በጥይት ተመተው ቀላል እና መጠነኛ ጉዳት የደረሰባቸው 3 ሰዎች እንዲሁም የአንዲት ወጣት #አስከሬንም ሆስፒታላቸው መምጣታቸውን የድል ጮራ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር አብዱራህማን አቡበከር ለዶቼቬለ ተናግረዋል። የዓይን ምስክሮች ደግሞ በግጭቱ ወቅት የሌላ አንድ ወጣት ህይወት በተባባሪ ጥይት ማለፉን ተናግረዋል። በሰፈሮቹ ዛሬ አንጻራዊ #ሰላም መስፈኑ ተዘግቧል።

🗞ቀን 13/10/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia