TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ICRC ለቄለም ወለጋ ዞን ተፈናቃዮች ድጋፍ አደረገ።

ባሳለፍነው ሳምንት ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ወይም በምዕፃረ ቃሉ #አሲአርሲ በደንቢዶሎ በመገኘት ከ2 ሺህ 500 በላይ ለሚሆኑ በግጭት የተጎዱ እና ከቄለም ወለጋ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ አድርጓል።

የተደረገው ድጋፍ የገንዘብ ድጋድ ሲሆን በአባወራዎች እና በሴቶች የሚመሩ ቤተሰቦች መሠረታዊ ፍላጎቶችን ለማሟላት እንዲረዳቸው የታሰበ መሆኑ ተገልጿል።

ICRC አሁን ያደረገው የገንዘብ ድጋፍ ሁለተኛ ዙር እንደሆነ ገልጿል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia