TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በዓለም አቀፍ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ውድድር ለሩብ ፍጻሜ የደረሰው ኢትዮጵያዊው ወጣት !

አቤል ዳኜ የሠራው በሁካታ መሃል ሆኖ ድምፅን ማጥፋት የሚቻልበት የቴክኖሎጂ ፈጠራ ፅንሰ ሃሳብ የሚያስረዳው ቪዲዮ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ መነጋገሪያ ሆኗል።

ነዋሪነቱን በአሜሪካ ያደረገው አቤል ዳኜ የ18 ዓመት ወጣት ሲሆን " ብሬክስሩ፣ ጁኒየር ቻሌንጅ " በተሰኘ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ሂሳብ ውድድር ላይ ከ2400 ሰዎች መካከል ለዕሩብ ፍጻሜ ከደረሱ 30 ሰዎች አንዱ መሆን ችሏል። 

#ቪኦኤ በሰጠው ቃል " ኮምፒውተር ሳይንስ ፍቅሬን ያዳበርኩት ከአባቴ ነው "  የሚለው አቤል የወደፊት ፍላጎቱም ትምህርቱን ጨርሶ #ኢትዮጵያን መርዳት እንደሆነ ተናግሯል።

ባለፈው ክረምትም በደብረ ማርቆስ ሀዲስ ዓለማየሁ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለሚማሩ ከመቶ በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች ዌብ ግንባታ ሲያስተምር ቆይቷል። 

አቤል ይህን " ብሬክስሩ " የተሰኘ ሽልማት ካሸነፈ የ250 ሺ ዶላር የነጻ የትምህርት ዕድል፣ 100 ሺ ዶላር ለተማረበት የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የሳይንስ ቤተ-ሙከራ ግንባታ እና እሱን ላበረታታ እና ላነቃቃ መምህር የ50 ሺ ዶላር ሽልማት የሚያገኝ ይሆናል።

ነገር ግን ይሄ ይሆን ዘንድ " ብሬክስሩ ቻሌንጅ " የፌስቡክ እና የዩቱብ ገጽ ላይ ሰዎች ላይክ፣ ኮሜንት በማድረግ እንዲያግዙት ጠይቋል።

የህዝብ ድምፅ አሰጣጡ #የመጨረሻ_ቀን ዛሬ መስከረም 10 (September 20) ነው። #አሁኑኑ በፍጥነት የሚከተሉትን 2 ቪድዮዎች  ‘Like’ አድርጋችሁ ድምፃችሁን ስጡት።

1. Facebook https://www.facebook.com/watch/?v=595860615362156
2. YouTube https://www.youtube.com/watch?v=PzTAhCHoIMQ&feature=youtu.be

@tikvahethiopia