TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
የ2005 የ20/80 ባለ3 መኝታ ተመዝቢዎች ፦ " ... በ14ኛው ዙር የዕጣ አወጣጥ የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች በቴክኖሎጂ ሆነ በማኑዋል ዕጣ የማውጣት ሂደቶች በሚፈጠሩ ችግሮች ሊወጣለት ከሚገባው ባለእድለኛ ወጪ ለሌላ ለማይመለከተው አካል እንዳይተላለፉ የሄደበትን ርቀት እናደንቃለን፡፡ ነገር ግን ይህ ቁርጠኝነት በባለ3 መኝታ 2005 ዓ.ም የ20/80 ተመዝቢዎችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲገለጽ እንፈልጋለን፡፡…
#መልስ_ያላገኘው_ጥያቄ

የ2005 የ20/80 የባለ 3 መኝታ የጋራ መኖሪያ ቤት ቆጣቢዎች ባለፈው ሙሉ በሙሉ የተሰረዘው ዕጣ ሳይወጣ የእነሱ ጉዳይ ላይ የአ/አ ከተማ አስተዳደር ግልፅ የሆነ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው በድጋሚ አሳሰቡ።

የጋራ መኖሪያ ቤት ይደርሰናል ብለው እየቆጠቡ ያሉ ወገኖች አለን ስላሏቸው ጥያቄዎች ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ማሳወቃችን አይዘነጋም።

" ዛሬም ድረስ ግልፅ የሆነ ማብራሪያ የሚሰጠን አጥተናል " ያሉት ነዋሪዎቹ " ከልጆቻችን ምግብ ቀንሰን፣ በቤት ክራይ እየተሰቃየንና እየተማረርን ላለፉት 9 ዓመታት ቆጥበን ስለምን በዕጣው ልንካተት እንዳልቻልን በግልፅ ሊነገረን ይገባል " ብለዋል።

የቀጣዩ የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ከመውጣቱ በፊትም መፍትሄ እንዲፈለግላቸው ጠይቀዋል።

የ2005 ዓ/ም 20/80 ለባለ 3 መኝታ ቆጣቢዎቹ ፤ " #ቤቶቹ_የትገቡ ? ፣ #ተስፋ_አድርገን_ነበር#13ኛው_ዙር_ላይ_97_አልቋል_ብላችሁን_አልነበር?! ፤ #ባለ3_መኝታ_ኦዲት_ይደረግ#ፍትህ_እንሻለን! "በሚሉ እና በሌሎች ሀሽታጎች በተለይም በማህበራዊ ሚዲያ በመሰባሰብ ጥያቄያቸው መልስ እንዲያገኝ ዘመቻ እያካሄዱ መሆኑን ገልፀዋል።

https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/72439?single
https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/72244?single
https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/72384?single
https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/72271

@tikvahethiopia