TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ባቱ

"ሓምሌ 22/2011 ዓ/ም 200 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል የተያዘውን ሀገራዊ እቅድ በኦሮምያ ክልል ብቻ 300 ሚልየን ለመትከል ዝግጅት ተጠናቋል፣ እኛም በባቱ(ዝዋይ) ከተማ ዝግጅት ላይ ነን"~ሰይፉ ታደሰ/TIKVAH-ETH/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ባቱ

"እኛ የቲክቫ አባላት ነን በባቱ/ዝዋይ/ ከተማ ችግኝ ተከላ ዘመቻ አርገን እየተመለስን ነው!" #አረንጓዴ_አሻራ
#DrLiaTadesse

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 5 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል!

ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 1,047 ላቦራቶሪ ምርመራ አምስት (5) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያቸው ተረጋግጧል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር መቶ አርባ አምስት (145) ደርሷል።

የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ ፦

ታማሚ 1 - የ75 ዓመት ኢትዮጵያዊት የአዲስ አበባ ነዋሪ ፤ የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ #የሌላቸው፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ያላቸው ግንኙነት በመጣራት ላይ ያለ (በጤና ተቋም ተኝተው ከሚታከሙ ህሙማን ከተወሰደ ናሙና የተገኘ)

ታማሚ 2 - የ25 ዓመት ኢትዮጵያዊ ፤ የመኖሪያ ቦታ አፋር ፤ ከጅቡቲ የተመለሰና በአፋር አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ።

ታማሚ 3 - የ22 ዓመት ኢትዮጵያዊ ፤ የመኖሪያ ቦታ አፋር ፤ ከጅቡቲ የተመለሰና በአፋር አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ።

ታማሚ 4 - የ8 ዓመት ኢትዮጵያዊት የአዲስ አበባ ነዋሪ፤ የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ የላትም፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት #ያላት

ታማሚ 5 - የ19 ዓመት ኢትዮጵያዊት የመኖሪያ ቦታ ኦሮሚያ #ባቱ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የላትም፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት #ያላት

ተጨማሪ መረጃ ፦

በትላንትናው ዕለት 16 ሰዎች (15 ከአዲስ አበባ እና 1 ከአማራ ክልል) ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር ዘጠና አንድ (91) ደርሷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ባቱ

በባቱ ከተማ ባለፈው እሁድ ለሊት ላይ ታጣቂዎች ፖሊስ ጣቢያ ላይ በከፈቱት ተኩስ 3 የፀጥታ ኃይል አባላት መገደላቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።

ለሬድዮ ጣቢያው ቃላቸውን የሰጡ አንድ ነዋሪ ፤ ታጣቂዎቹ በከፈቱት ተኩስ አንዲት ሴት እና 2 ወንድ የፀጥታ ኃይሎች እንደሚገኙበት፤ ስርዓተ ቀብራቸውም በከተማው መፈፀሙን ፤ ከታጣቂዎቹ በኩል አንድ የተመታባቸውን ሰው እየጎተቱ አርቀው እንደወሰዱ የሚያሳይ መረጃ መገኘቱን ገልጸዋል።

የታጣቂዎቹ ተኩስ መክፈት እስረኞችን ለማስለቀቅ መሆኑን እኚሁ የከተማይቱ ነዋሪ ተናግረዋል።

ባቱ በዕለቱ ከተፈፀመው ክስተት በኃላ በወትሮ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ እንደምትገኝ ነዋሪው ገልጸዋል። ነገር ግን ሁኔታው ነዋሪዎችን ስጋት ላይ መጣሉን ለሬድዮ ጣቢያው አመልክተዋል።

በሌላ በኩል ፤ በባቱ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በዕለቱ ረጅም ደቂቃ የተኩስ ድምፅ ይሰማ እንደነበርና ተኩሱ ይሰማ የነበረው በማረሚያ ቤት አካባቢ እንደነበር አመልክተዋል።

በከተማው አስተዳደር በኩል የተባለ ነገር የለም።

ከዚህ ቀደምም በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ፣ ወለንጪቲ፣ በቆጂ ከተሞች የታጠቁ ኃይሎች ከተማ ድረስ ዘልቀው በመግባት ተኩስ በመክፈት ሰዎችን መግደላቸውና እስረኞችን ለማስመለጥ ሙከራ ማድረጋቸው መነገሩ አይዘነጋም።

የኦሮሚያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኮሎኔል አበበ ገረሱ በበቆጂ ጨምሮ በቢሾፍቱ፣ ወለንጪቲ ስለተፈፀሙት ጥቃቶች ከዚህ ቀደም ከሪፖርተር ጋዜጣ ተጠይቀው ፤ የተደራጀ ጥቃት በየትኛውም አካባቢ እንዳልተፈፀመ " አልፎ አልፎ #ሽፍታ ወይም #ሌባ ሊኖር ይችላል እንጂ ጥቃት የሚባል ነገር የለም። ሁሉም አካባቢ ሰላም ነው " ማለታቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
ዛሬ " ገርቢ " ላይ በደረሰ የመኪና አደጋ የ7 ሰዎች ህይወት አለፈ።

በምስራቅ ሸዋ ዞን ፤ በአዳሚ ቱሉ ወረዳ ውስጥ በደረሰ የመኪና አደጋ የ7 ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡

አደጋው የደረሰው ከአዳሚ ቱሉ ወረዳ ወደ #ባቱ ከተማ ሲጓዝ የነበረ ዳማስ ተሽከርካሪ እና በተቃራኒ አቅጣጫ ሲጓዝ የነበረ ቶዮታ ቪ ኤይት (v8) መኪና  " ገርቢ " ተብሎ በሚጠራ አካባቢ በመጋጨታቸው ነው።

በአደጋው 4 ሰዎች ወዲያው ሕይወታቸው ሲያልፍ 3 ሰዎች የህክምና ተቋም ከደረሱ በኋላ ሕይወታቸው አልፏል። በአጠቃላይ በአደጋው 7 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡

ሌሎች በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ኤፍ ቢ ሲ የባቱ ኮሚኒኬሽንን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

(የአደጋውን ሁኔታ የሚያሳየውን ተንቀሳቃሽ ምስል የላከልን ሣሚ ተስፋዬ የሚባል የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው)

@tikvahethiopia