TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የአፊኒ ባህላዊ ስነ ስርዓት!!

"በሀገሪቱ የተጀመረውን ለውጥ ለማስቀጠል #የወጣቱ ሚና ከፍተኛ መሆን አለበት" – የሲዳማ ብሄር የሀገር ሽማግሌዎች
.
.
.
በኢትጵያ የተጀመረውን ለውጥ ለማስቀጠል የወጣቱ ሚና ከፍተኛ መሆን እንዳለበት የሲዳማ ብሄር የሀገር ሽማግሌዎች አሳሰቡ፡፡ በብሄሩ አመታዊው የአፊኒ ባህላዊ ስነ ስርአት #በሶሬሳ_ጉዱማሌ በሃዋሳ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል፡፡

ሲዳማ ከሌሎች ህዝቦች ጋር ተዋዶ እና ተፍቅሮ #በአንድነት የመኖር እሴቱን ጠብቆ የኖረ ነው ያሉት የሀገር ሽማግሌዎች ወጣቱም ይህን አኩሪ ባህል ሊጠብቀውና ማንኛውም ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ ሊያቀርብ እንደሚገባ ገልፀዋል።

በውይይቱ ላይ የተገኙት የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ #ሚሊዮን_ማቲዎስ በበኩላቸው የሲዳማ ብሄር በአቃፊነቱ እንጂ በጥላቻ አይታወቅም ስለዚህም ከሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ጋር በአንድነት ለመኖር የዘመናት ባህሉ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

ወጣቱም የአባቶቹን ምክር በመስማት ሊተገብር ይገባል ያሉ ሲሆን ይህ መሰል ባህላዊ ስርአት ሌሎችም እንደተሞክሮ ሊጋሩት እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል።

የውይይቱ ተሳታፊ ወጣቶችም የሀገር ሽማግሌዎችን ምክርና ተግሳፅ በስርአቱ መሰረት በመቀበል ለሀገራዊ ለውጡ የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ fbc ገልፀዋል።

በወጣቱ ስም በሃዋሳም ሆነ በዞኑ የሚነሱ የሰላም መደፍረሶችን በመከላከል ህግና ስርአት እንዲከበር የበኩላችንን እንወጣለን ብለዋል ተሳታፊዎቹ፡፡

ክልል የመሆን ጥያቄ እና ሙሰኞችን የማጋለጥ ሂደት በሰላማዊ መንገድ እንደሚታገሉ ተናግረዋል።

በአፊኒ ስርአት የሀገር ሽማግሌዎችና ወጣቶቹ በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ ቃል በመግባት አጠናቀዋል።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia