TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ዓረና‼️

በሀገር-ዓቀፍ ደረጃ የተጀመረው #ሪፎርም ወደ ክልሎችም በበቂ ደረጃ እንዲወርድ ዓረና ትግራይ ለዴሞክራሲ ሉዓላዊነት ፓርቲ ገለፀ፡፡

Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን‼️

የፌዴራል ፖሊስ ልዩ ሃይልና በአየር የታገዘ የፖሊስ ቡድን እሰከማቋቋም የደረሰ የአደረጃጀት ማስተካከያ አደረገ። የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል #እንዳሸው_ጣሰው ዛሬ በሰጡት መግለጫ፥ የኮሚሸኑ ተቋማዊ ሪፎርም ሂደት እና የደረሰበትን ደረጃ አብራርተዋል።

የሰው ሃይል፣ ቴክኖለጂ፣ ስልጠና፣ ሎጅስቲክስ እና ከባለደርሻ አካላት ጋር የሚኖር ግንኙነት ላይ መሰረት ያደረገው #ሪፎርም በጥሩ አፈፃፀም ላይ እንደሚገኝ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።

በረፎርሙ መሰረት የፌዴራል ፖሊስ ሰራዊት አሰፋፈር እና አደረጃጀት #መከለሱን እንዲሁም በአራት አቅጣጫ በአራት ክላስትሮች እንዲከፋፈል መደረጉን ነው የገለፁት። ክላስተሮቹም፥ ሰሜን፣ ደቡብ፣ ምእራብ እና ማእከላዊ ክላስተር ናቸው።

በሪፎርሙ መሰረት የከተማ ልዩ የፌደራል ፖሊስ ሃይል እና #በአየር የታገዘ ክትትል ለማድረግም የፌራል ፖሊስ የአየር ሃይል ክንፍ ( AIR WING ) #ይደራጃልም ብለዋል ኮምሽነር ጀነራሉ።

የጦር መሳሪያ ትጥቅን በተመለከተም የፌዴራል ፖሊስ፣ የክልል ፖሊስ እና ልዩ ሃይል እንዲሁም ሚሊሻዎች ምን አይነት መሳሪያ ሊታጠቁ ይገባል የሚለውን የሚመልስ አዋጅ በመዘጋጀት ላይ ነው።

የሪፎርሙ አካል የሆነ የምርመራ ስርኣትን በሚመለከትም የምርመራ ማንዋል ተዘጋጅቶ በቅርቡ ወደ ትግባራ እንደሚገባ ተነግሯል።

#ፌዴራል_ፖሊስ ካሁን ቀደም ከምርመራ ጋር የተያያዙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለማስቀረት ካሜራ የተገጠመላቸው፣ በመስታውት የተከለሉ፣ ሶስተኛ ወገን ምርመራውን መከታተል የሚችልባቸው የምርመራ ክፍሎች መዘጋጀታቸውም በመግለጫው ተነስቷል።

ምንጭ፦ FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መከላከያ ሰራዊት‼️

የኢፌድሪ መከላከያ ሚነስቴር እያካሄደ ያለው #ሪፎርም በተጠናከረ ሁኔታ ቀጥሏል፡፡ የተጀመረውን ሪፎርም ለማስቀጠልና በታሰበለት መልኩ ለማሳካት የሚያስችል ስልጠናም እየተሰጠ ይገኛል፡፡ ስልጠናው ሰራዊቱ ሪፎርሙን እውን በማድረግና የሪፎርሙን የአሰራር ስርዓት በማስቀጠል ወደፊት ለሚኖረው የግዳጅ አፈፃፃም ተልዕኮ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ታምኖበታል፡፡ የወታደራዊ አመራሩን አቅምን ለማሳደግ የታለመው ይኸው ስልጠና በሁሉም የሰራዊቱ ክፍሎች በመሰጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን ከታክቲካል እስከ ኦፕሬሽናል አመራር እርከን ያሉ የሰራዊት አባላትን ያጠቃለለ ነው፡፡ በተጨማሪም ስልጠናው ሰራዊቱ ለህዝቡና ለህገ መንገስቱ ያለውን ታማኝነት በፅናት የሚያረጋግጥበትን አቅም ከፍ የሚያደርግና የሪፎርሙን ግቦች በማሳካት በኩልም ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ታምኖበታል፡፡ ለስምንት ቀናት በሚቆየው በዚሁ ስልጠናም የተለያዩ ፅሁፎች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AU2022Summit ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በ35ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር አፍሪካ በተመድ ፀጥታ ም/ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት የሚሠራበት ጊዜ መሆኑን ገለፁ። ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፥ " አሁን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሚሻሻልበት እና አፍሪካም በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት የሚሠራበት ጊዜ ነው " ሲሉ ተናግረዋል። ከዚህ…
#UNGA  

አሜሪካ የተመድ የፀጥታ ም/ቤት ሁሉን አካታች እንዲሆን ለማድረግ #ሪፎርም እንዲደረግበት ጥሪ አቀረበች።

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በኒውዮርክ እየተካሄደ ባለው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 77ኛ ጠቅላላ ጉባዔ ባደረጉት ንግግር ፦
- #የአፍሪካ
- ላቲን አሜሪካ
- ካሪቢያን ሀገራት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ም/ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

የፀጥታው ምክር ቤት ለዓለም አቀፍ ተግዳሮቶች ምላሽ ለመስጠት የተሻለ ብቃት እንዲኖረውና ሁሉንም አካታች እንዲሆን ለማድረግ ሪፎርም እንዲደረግበትም ባይደን ጥሪ አቅርበዋል።

ምክር ቤቱ አሁን ላይ 5 ቋሚ እና 10 ተለዋዋጭ በድምሩ 15 መቀመጫዎቸ ያሉት ሲሆን ይህ የመቀመጫ ቁጥር እንዲጨምር ጠይቀዋል።

በአፍሪካ፣ ላቲን አሜሪካና ካሪቢያን ውስጥ የሚገኙ ሀገራት በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲያገኙ የጠየቁት ባይደን አሜሪካ ይህንን አቋም ለረጅም ጊዜ ስትደግፍ ቆይታለች ብለዋል።

በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ያላቸው ሀገራት በእነሱ ላይ ወይም በአጋሮቻቸው ላይ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን የመሻር መብት አላቸው።

ባይደን አሜሪካን ጨምሮ በፀጥታው ም/ቤት ቋሚ መቀመጫ ያላቸው ሀገራት ምክር ቤቱ ተዓማኒነት ያለውና ውጤታማ ሆኖ እንዲቀጥል ከአቅም በላይ ከሆኑ ያልተለመዱ ሁኔታዎች ውጪ ድምጽን በድምጽ መሻር መብታቸውን ከመጠቀም እንዲቆጠቡም አሳስበዋል።

አፍሪካ በፀጥታው ም/ ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት ለማስቻል የተለያዩ ዘመቻዎች ሲካሄዱ እንደነበር ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከዚህ ቀደም ይህንን የአፍሪካ ሀገራት በተመድ የጸጥታው ጥበቃ ም/ቤት ቋሚ መቀመጫ ማግኘት አለባት የሚለውን ሃሳብ መቀላቀላቸውን ይፋ ማድረጋቸው አይዘነጋም።

#አልዓይን

@tikvahethiopia