TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ወላይታ🕊ሲዳማ!

ትናንት "ፍቅር በደልን አይቆጥርም " በሚል መርህ በሲዳማና በወላይታ ሕዝቦች መካከል ያለውን ትስስር ለማጠናከር የሚያግዝ የዕርቅና
የሰላም ኮንፈረንስ በሀዋሳ ከተማ በሲዳማ ባህል አዳራሽ ተካሂዷል።

በኮንፈረንሱ ላይ የተገኙት የደኢህዴን ሊቀ መንበርና የኢፌደሪ የሠላም ሚኒስቴር ሚኒስትሯ ወይዘሮ #ሙፈሪሀት_ካሚል፥ በሲዳማና በወላይታ ሕዝቦች መካከል ሰላም ሰፍኖ ዕርቅና የሠላም ኮንፈረንስ እንዲካሄድ ትልቅ አስተዋፅኦ የነበራቸውን አባቶች አመስግነዋል፡፡

ሰላም በእያንዳንዳችን ልቦና እና ቤት የሚገኝ በኛው ጥበቃ የሚጎለብት በመሆኑ ልንጠብቀው ይገባል ሲሉም ተናግረዋል፡፡ ወጣቶች ሰላምን ከሚያደፈርሱ ቆስቋሽ ድርጊቶች እንዲጠበቁም አሳስበዋል፡፡

በዕርቁ ሥነ ሥርዓት ላይ ከሲዳማና ወላይታ ዞን የተወጣጡ የኃይማኖት መሪዎችና አባቶች፣ ከሁለቱም ዞኖች የተወጣጡ የባህል ሽማግሌዎችና ወጣቶች፣ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የኦሮሞ አባ ገዳዎች እና ጥሪ የተደረገላቸዉ ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

ምንጭ፦ arts tv
@tsegabwolde @tikvahethiopia