TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#NewsAlert ባለፈው ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ በተፈጸመ የከፍተኛ አመራሮች ግድያ በጣት የሚቆጠሩ ቡድኖች በወንጀሉ በግልፅ ተሳትፈዋል አሉ የአዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ቧያለው፤ ከእነዚህ ውስጥ አንዳንዶች ወንጀሉን አምነው እጃቸውን ሲሰጡ ሌሎች ደግሞ በፈጸሙት ወንጀል እየተሸበሩ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

“አዴፓ #ከፋኖ ጋር ወይም የፋኖ ትክክለኛ አስተሳሰብ ካለው ወጣት ጋር ግብ ግብ ሊገጥም አይችልም ” ያሉት አቶ ዮሐንስ ፣ “ትግሉ ወንጀለኛን ከማያዝ አንፃር መሆኑን ህብረተሰቡ ሊረዳ ይገባል” ብለዋል፡፡

“በተደራጀ መንገድ የመንግስትን እጅ ለመጠምዘዝና የህብረተሰቡን ሰላም በማወክ በወንጀል የሚሳተፉ ካሉ የገዥውን ፓርቲ ጨምሮ የማንም ፓርቲ፣ ቡድንና ድርጅት አባል ቢሆኑም ከተጠያቂነት አያማልጡም” ብለዋል፡፡

#ፋኖ በስሙ #መነገጃ ሊሆን እንደማይገባ የጠቆሙት አቶ ዮሐንስ የፋኖን ስም ይዘው በወንጀል የሚሳተፍ ግለሰብም ሆነ ቡድንን የአማራ ወጣት ሆነ ህብረተሰቡ አምርሮ ሊታገላቸው እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ተጨማሪውን ያብቡ👇
https://telegra.ph/YB-07-08