TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሐምሌ_22

ኢትዮጵያ ቡና

ሀገር አቀፍ የችግኝ ተከላ ሰኞ በሙሉ ኢትዮጵያ ከተማዎች እንደሚተከል ይጠበቃል። ሁላችንም የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ማልያ በመልበስ ከጠዋቱ 1:00–1:30 በተመደበልን ቦታ በሰአቱ በመገኘት ቀጥታ የክለባችንን አሻራ ለሀገራችን እናሳርፍ።

የመሳፈርያ ቦታዎች፦

#ፒያሳ_መዘጋጃ
#ሜክሲኮ_ቡና_እና_ሻይ
#መስቀል_አደባባይ
#ጀሞ
#ሳሪስ_አደይ_አበባ
#ሰባተኛ_ቶታል

#ኢትዮጵያ_ቡና @BUNA_GEBEYA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸በዛሬው ዕለት በዓዲግራት ከተማ እየተከበረ ያለው #ደማቅ የመስቀል በዓል ምክንያት በማድረግ የተካሄደው ታላቅ ሩጫ #መስቀል_ዓጋመ #ADIGRAT #ETHIOPIA

PHOTO: JOHN/TIKVAH-ETHIOIA
@tsegabwolde @tikvahethioia
#UNESCO #ETHIOPIA

#መስቀል
#ፍቼ_ጫምባላላ
#የገዳ_ስርዓት
#ጥምቀት

ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስ እና የባህል ድርጅት (UNESCO ) ያስመዘገበቻቸው የቅርሶች ብዛት 13 ደርሷል። እነዚህ ቅርሶች በሚዳሰሱና በማይዳሰሱ ቅርሶች ዘርፍ የተመዘገቡ ናቸው። ከእነዚህም መካከል የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ አክሱም፣ የኮንሶ ባህላዊ እርከን ይገኙበታል። በሚቀጥለው ዓመት በማይዳሰስ ቅርስነት ይመዘገባል ተብሎ የሚጠበቀው አሸንዳ አሸንድዬ ይገኝበታል።

(BBC)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#እንቁጣጣሽ #መስቀል #ኢሬቻ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳት እና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የአዲስ አመት በአልን ጨምሮ የመስቀል እና የኢሬቻ በአልን ተከትሎ ሊከሰቱ ከሚችሉ ማናቸውም ድንገተኛ አደጋዎች ማህበረሰቡን መታደግ የሚያስችለውን የቅድመ አደጋ ዝግጁነት ስራ መሰራቱን አሳውቋል።

ይህ የተገለፀው በኮሚሽኑ የአደጋ ምላሽ ዘርፍ ሰራተኞች ከማዕከል እና ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶቹ ጋር ባደረገው ውይይት ላይ ነው።

ኮሚሽኑ ቅድመ ዝግጅቱን ያጠናቀቀ ቢሆንም አደጋ ሳይከሰት ቀድሞ ለመከላከል የህበረተሰቡ ተሳትፎ ጉልህ ሚና አለው ተብሏል።

በመድረኩም ላይ ለ2014 ዓመት መስከረም ወር ላይ ለሚከበሩት ሶስቱ በዓላት፦
- አዲስ ዓመት
- መስቀል
- ኢሬቻ በዓላት ለአደጋ ምላሽ አገልግሎት የሚውሉ በቂ ግብአቶች እና ተሽከርካሪዎች መመደባቸውን የተገለፀ ሲሆን በዚህም መሰረት በ10 ክፍለ ከተማ 918 የአደጋ ሠራተኞች ፣ 39 ከባድ የአደጋ ተሽከርካሪዎች እና 22 የቅድመ ሆስፒታል አገልግሎት የሚሰጡ አምቡላንሶች ዝግጁ መሆናቸው ተገልጿል።

#ጥቆማ

ህበረተሰቡ ሳይዘናጋ እራሱን ከድንገተኛ አደጋ መከላከል እንዳለበት ተገልጿል፤ ጥንቃቄ እያደረገ ለሚገጥመው ማንኛውም አደጋ ግን ወደ ተቋሙ ስልክ ቁጥሮች ፦
• ነፃ ስልክ መስመር 👉 939
ወይም በቀጥታ የውስጥ መስመሮች ፦
• 0111555300
• 0111568601
• 0111264848 ላይ በመደወል አገልግሎቱን 24 ሰዓት ማግኘት ይችላል ተብሏል።

@tikvahethiopia
#ኢሬቻ #መስቀል #የመንግስት_ምስረታ !

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከመስቀል፣ ከኢሬቻ በዓላት እና ከመንግስት ምስረታ ስነ-ስርዓት በፊትና በኋላ ሊከሰቱ የሚችሉ የፀጥታ ችግሮችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ፤ ችግር ቢከሰት እንኳን ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ጠንካራ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱን ይፋ አድርጓል።

ኮሚቴው በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮምሽነር ጀኔራል የሚመራ ሲሆን ፦
- ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ፣
- ከሀገር መከላከያ ሚኒስቴር፣
- ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት፣
-ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን
- ከኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ከተውጣጡ አመራሮች የተዋቀረ ነው።

@tikvahethiopia
#መስቀል

መልካም የመስቀል በዓል !

@tikvahethiopia