TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጥቆማ

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፤ በ2014 ዓ.ም እና 2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው የትምህርት ሚኒስቴር ያወጣውን የዩኒቨርስቲ መግቢያ መቁረጫ ውጤት ያመጡ እና በፖሊስ የሙያ ዘርፍ ሀገራቸውን ለማገልገል #የሚፈልጉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር እንደሚፈልግ አሳውቋል።

ተቋሙ ለ4  አመታት በ " ፖሊስ ሳይንስ ዲግሪ " አስተምሮ በመኮንንነት (ረዳት ኢንስፔክተር ማዕረግ) በማስመረቅ በተለያዩ የፌደራል ፖሊስ የስራ ክፍሎች አስመድቦ ለማሰራት እንደሚፈልግ ነው የገለፀው።

በተጨማሪ በ "ፎረንሲክ ሳይንስ ዲግሪ" አስተምሮ በመኮንንነት (ረዳት ኢንስፔክተር ማዕረግ) በማስመረቅ በፎረሲክ ምርመራ የላብራቶሪ ሙያተኝነት (ኤክስፐርት) በማስመደብ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡

በተቋሙ በ  " ፖሊስ ሳይንስ ዲግሪ " ለመማር የሚያስፈልጉ የመመልመያ መስፈርቶች ከላይ በምስሉ የተዘረዘሩ ሲሆን ከነሱም ውስጥ ፦

- አመልካቾች ከማንኛውም ወንጀል ነፃ ስለ መሆኑ ከሚኖርበት ወረዳ ፖሊስ ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው።

- ለፖሊስ አካል ብቃት ስልጠና ብቁ የሆነ አካላዊ አቋምና አዕምሮ ጤንነት ያላቸው ሊሆኑ ይገባል።

- በ2014 ዓ/ም እና 2015 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባ የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስተር መቁረጫ ውጤት ያላቸው  የትምህርት ማስረጃቸውንም ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።

- የ #ሪሚዳል_ትምህርት ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡ ከሆነም ማስረጃ ማቅረብ አባቸው።

- አመልካቾች እድሜያቸው ከ18 እስከ 28 ዓመት መሆን አለበት።

- ቁመት ለወንድ 1.65 እና ከዚያ በላይ፣ ለሴት 1.55 እና ከዚያ በላይ፣
ሲሆን የተስተካከለ የሰውነት ክብደት 18.5-24.9 kg/m) ያለቸው ሊሆኑ ይገባል።

- ከተመረቁ በኋላ 7/ሰባት/ አመት በተማረበት የፖሊስ ሙያ በየትኛውም የአገሪቱ ክልልና የፖሊስ የስራ መደቦች ላይ ተመድቦ ለመስራት ፍቃደኛ መሆን አለበት።

- ሴት አመለካቾች ከእርግዝና ነፃ መሆን አለባቸው።

- ሁሉም አመልካቾች ከዚህ በፊት የፖሊስ ወይም የመከላከያ ሰራዊት ስልጠና ያልወሰዱ መሆን ያለባቸው ሊሆኑ ይገባል።

ለ " ፎረንሲክ ሳይንስ ዲግሪ " ከላይ ያሉት አብዛኛው መስፈርቶች እንደተጠበቁ ሆነው ፦
- ዜግነት #ኢትዮጵያዊ
- የ12ኛ ክፍል #በተፈጥሮ_ሳይንስ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው በ2014 ዓ/ም እና በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣውን መቁረጫ ውጤት ያላቸው
- በተፈጥሮ ሳይንስ የሪሚዳል ትምህርት ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ሊሆኑ ይገባል።

በሁለቱም የዲግሪ ትምህርት ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን የሚቀላቀሉት በራሱ በተቋሙ የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና ማለፍ ሲችሉ ብቻ ነው።

የት እና እስከመቼ መመዝገብ ይቻላል ?

ማመልከት የሚቻለው እስከ ጥቅምት 22/2016 ዓ/ም ድረስ ባሉት ተከታታይ የስራ ቀናት ነው።

ተማሪዎች በአካባቢያቸው በሚገኝ በሁሉም የክልል እና የከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽኖች በአካል በመገኘት መመዝገብ ይችላሉ።

ለመዝገባው የትምህርት ማስረጃቸውን የ8ኛ ፣ የ10ኛና 12ኛ ክፍል ካርድ እና ትራንስክርፕት ኦርጅናል ከማይመለስ አንድ ፎቶ ኮፒ ጋር ይዘው መቅረብ አለባቸው።

#ደመወዝ / #ክፍያን በተመለከተ

ዕጩ መኮንኖች በትምህርት ላይ በሚቆዩበት ጊዜያት ከ3 ወር የሙከራ (recruit) ጊዜ ቆይታ በኋላ እስከሚመረቁ ድረስ የኪስ ገንዘብ/ደመወዝ ታስቦ ይከፈላቸዋል ተብሏል።

ስልክ ካስፈለጋችሁ ፡ 0116735564

(ተጨማሪ ዝርዝር ጉዳዮችን ከላይ በምስሉ ያንብቡ)

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

የኢሰመኮ 3ኛ ዙር የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፎች እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር ላይ ተሳተፉ !

መኖሪያ ቤት/ቦታ ማለት ለአንድ ሰው ወይም ለአንድ ቤተሰብ ምን ማለት ነው ?

ሕይወት፣ ትርጉም ያለው ሕይወት፣ ምንድን ነው ? የአንድ ኢትዮጵያዊት ሴት፣ ወይም የአካል ጉዳተኛ ወይም የተፈናቃይ ወይም የአረጋዊ ሕይወት ምን ይመስላል ?

በሕይወት እና በመኖሪያ ቤት ዙርያ እነዚህን እና የመሳሰሉ ጥያቄዎች ለኪነጥበብ አፍቃሪዎች፣ ለኪነጥበብ ሙያ ተማሪዎች፣ ባለሞያዎች እና አማተሮች እንዲሁም ለመገናኛ ብዙኃን አባላት እና ሌሎችም በኪነጥበብ እና በሰብአዊ መብቶች መካከል ያለውን ትስስር ማሳየት ለሚፈልጉ ሁሉ፣ በኢሰመኮ አዘጋጅነት በሚካሄደው የ3ኛው ዙር የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር የቀረቡ ናቸው።

ኑ፣ ተሳተፉ፣ አብረን እንድናሰላስል የሚረዱ የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልም ሥራዎቻችሁን ለዕይታ አቅርቡ!
በውድድሩ ለመሳተፍ እና ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ዝርዝሩን በዚህ ይመልከቱ - https://bit.ly/46sReAw
#ጥቆማ

የኢሰመኮ 3ኛ ዙር የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፎች እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር ላይ ተሳተፉ !

መኖሪያ ቤት/ቦታ ማለት ለአንድ ሰው ወይም ለአንድ ቤተሰብ ምን ማለት ነው ?

ሕይወት፣ ትርጉም ያለው ሕይወት፣ ምንድን ነው ? የአንድ ኢትዮጵያዊት ሴት፣ ወይም የአካል ጉዳተኛ ወይም የተፈናቃይ ወይም የአረጋዊ ሕይወት ምን ይመስላል ?

በሕይወት እና በመኖሪያ ቤት ዙርያ እነዚህን እና የመሳሰሉ ጥያቄዎች ለኪነጥበብ አፍቃሪዎች፣ ለኪነጥበብ ሙያ ተማሪዎች፣ ባለሞያዎች እና አማተሮች እንዲሁም ለመገናኛ ብዙኃን አባላት እና ሌሎችም በኪነጥበብ እና በሰብአዊ መብቶች መካከል ያለውን ትስስር ማሳየት ለሚፈልጉ ሁሉ፣ በኢሰመኮ አዘጋጅነት በሚካሄደው የ3ኛው ዙር የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር የቀረቡ ናቸው።

ኑ፣ ተሳተፉ፣ አብረን እንድናሰላስል የሚረዱ የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልም ሥራዎቻችሁን ለዕይታ አቅርቡ!
በውድድሩ ለመሳተፍ እና ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ዝርዝሩን በዚህ ይመልከቱ - https://bit.ly/46sReAw
#ጥቆማ #ከጠቀማችሁ

የአዳማ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ተወርሰው የሚገኙ 171 ተሽከርካሪዎችን በግልፅ ጨረታ ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። ተጨራቾች የጨረታ ሰንድ በመግዛት በጨረታው ላይ የሚወጡትን ተሽከርካሪዎች በአካል በመመልከት መጫረት ትችላላችሁ ተብሏል። ጨረታው በ26/02/2016 ዓ/ም ጥዋት 4 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥኑ ተዘግቶ በዚሁ ቀን 4:15 ላይ የጨረታ ሳጥኑ ይከፈታል። ለተጨማሪ መረጃ በስልክ 0221118429 ላይ መወደል ይቻላል።

አዲስ አበባ ቃሊት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት የተተው፣ የተወረሱ እና በኮንትሮባንድ ተይዘው የሚገኙ የተለያዩ የቤትና የጭነት ተሸከርካሪዎች ፦
- DUMP TRUCK፣
- IVECO FIAT፣
- TOYOTA HAILUX፣
- TOYOTA COROLLA፣
- TOYOTA  VITZ፣
- TOYOTA HAICE፣
- TOYOTA YARIS፣
- TOYOTA CHR፣
- HYUNDAI፣
- SUZUKI፣
- MISTUBUSHI ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎችን፣ የሞባይል ክፍሎች፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን፣ የተለያዩ የተዘጋጁ አልባሳትና ጫማዎች፣ የውብት መጠበቂያ ዕቃዎች እና ሌሎች የተለያዩ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታ በግልፅና በሃራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል። የተጠቀሱት ተሸከርካሪዎች የጨረታ ሰነድ ከቀን 20/02/2016 ዓ.ም ጀምሮ ማግኘት ይቻላል።

(ዝርዝር መረጃዎችን ከላይ በምስሉ ይመልከቱ)

  የገቢዎች ሚኒስቴር በታክስ ዕዳ የያዛቸውን ተሽከርካሪዎችና ሌሎች የተለያዩ ንብረቶች ለመሸጥ ይፈልጋል።

ከፎኔክስ ኢንደስትሪ ኃ/የ/የግ/ማህበር የተያዘ፦
- የኘላስቲክ ወንበር ማምረቻ ማሽን፣  የማሽኑ ማቀዝቀዣ (cooler)፣ የማሽኑ ጥሬ ዕቃዎችና ሌሎች ተጓዳኝ ዕቃዎች፣

ከተክለብርሃን አምባየ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተያዙ ፦
- የተለያዩ መጠን ያላቸው የመብራት አምፖሎች፣
- ፍሎረሰንቶች፣
- ፖውዛዎች እና የውሃ ተቀባሪና ተንጠልጣይ የተለያዩ ቧንቧዎች፣

🚘 ከቲ.አይ.ቢ ኬተሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህ እና ኦክስፎርድ አማልጌትድ ኃ/የተ/ የግ/ማህበር የተያዙ የተለያየ ሞዴል ያላቸውን 3 ተሽከርካሪዎች ናቸው።

(ዝርዝር መረጃዎችን ከላይ በምስሉ ይመልከቱ)

#ጉምሩክኮሚሽን #አዲስዘመን #ገቢዎችሚኒስቴር

* ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በጥቆማ መልክ የቀረበ።

@tikvahethiopia
#NEBE

በገዛ ፍቃዳቸው ከኃላፊነታቸው በለቀቁት ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ምትክ አዲስ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ለመተካት 8 አባላት ያሉት የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ዕጩ መልማይ ኮሚቴ ዛሬ ተሰይሟል።

ይኸው ኮሚቴ የተሰየመው በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ነው።

የኢፌዴሪ ህገ መንግሥት አንቀጽ 102 እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ 1133/2011 አንቀፅ 5/1 ላይ በሰፈረው መሰረት #ጠቅላይ_ሚኒስትሩ ዕጩ የስራ አመራር ቦርድ አባላት የሚመለምል ገለልተኛ ኮሚቴ እንደሚሰይሙ ይደነግጋል።

የተቋቋመው መልማይ ኮሚቴ ወደ ስራ መግባቱ የተነገረ ሲሆን በቅርቡ #ጥቆማ መቀበል እንደሚጀምር ተገልጿል።

የምርጫ ቦርድ ሰብሰቢ መልማይ ኮሚቴው ፦
- ቀሲስ ታጋይ ታደለ (ሰብሳቢ)
- ፕ/ር ተከተል ዮሐንስ (አባል)
- አቶ ባዩህ በዛብህ (አባል)
- ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ (አባል)
- አቶ ካሳሁን ፎሎ (አባል)
- ወይዘሮ ርግበ ገብረሃዋርያ (አባል)
- ወይዘሮ እንግዳዬ እሸቴ (አባል)
- ኢ/ር መላኩ እዘዘው (አባል)

መረጃው ከጠቅላይ ሚኒስቴር ፅ/ቤት የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
#TOYOTA

ቶዮታ / Toyota ዓለም አቀፍ የመኪና አምራች ኩባንያ በዓለም ገበያ በዋነኝነት #በአሜሪካ የተሸጡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎቹን  ከገበያ ላይ እንዲሰበሰቡ አዟል።

ቶዮታ እንዲሰብሰቡ ያዘዘው ከ2020 እስከ 2022 ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ የተመረቱ ተሽከርካሪዎችን ሲሆን ተሽከርካሪዎቹ የ " ኤርባግ " ደህንነት ችግር አለባቸው ተብሏል።

ከ2020 እስከ 2022 ወደ ገበያ የቀረቡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎች (በዋነኝነት #አሜሪካ) ከ " ኤርባግ " ጋር በተያያዘ ችግር እንዳለባቸው ተደርሶበታል።

ችግሩ በፊት ለፊት ተሳፋሪ መቀመጫ በኩል በስህተት ከተሰራ የ " ኤርባግ ሴንሰር " ጋር የሚያያዝ ሲሆን ምናልባትም በአደጋ ጊዜ " ኤርባጉ " አገልግሎት ላይሰጥ ይችላል። ይህ አደጋ በሚፈጠር ጊዜ ኩዳቱ እንዲጨምር ያደርጋል።

ቶዮታ የትኞቹ ሞዴሎች ይሰብሰቡ አለ ?

#ቶዮታ

ኮሮላ (2020 - 2021)
ራቭ4 ፣ ራቭ4 ሃይብሪድ (2020 - 2021)
ሃይላንደር፣ ሃይላንደር ሃብሪድ (2020 - 2021)
አቫሎን ፣  አቫሎን ሃይብሪድ (2020 - 2021)
ካምሪ፣ ካምሪ ሃብሪድ (2020 - 2021)
ሴና ሀይብሪድ (2021)

#ሌክሰስ

ES250 (2021)
ES300H (2020-2022)
ES350 (2020-2021)
RX350 (2020-2021)
RX450H (2020-2021) የተሰኙ ከ2020 እስከ 2022 ላይ የተመረቱት የ " ኤርባግ " ችግር ስላለባቸው ይሰብሰቡ ብሏል።

ከላይ የተጠቀሱት ተሽከርካሪዎች ያላቸው ሰዎች ኤርባጋቸውን #እንዲያረጋግጡ እና ችግር ካጋጠማቸው እስከ ቀጣዩ የካቲት ወር ድረስ እንዲመልሱለት ቶዮታ ጥሪ አቅርቧል።

የቶዮታ ተሽከርካሪዎች ችግር እንዳለባቸው የታወቀው የጃፓን ትራንስፖርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ ተሽከርካሪ እምራች ኩባንያዎች ላይ ባደረገው #ምርመራ ላይ እንደሆነ ተገልጿል።

ይህን ተከትሎ የቶዮታ ኩባንያ አክስዮን ዋጋ ቅናሽ አሳይቷል።

ምርመራው ከቶዮታ ተሽከርካሪዎች በተጨማሪ ዳይሀትሱ በተሰኘው ኩባንያ ላይም ተመሳሳይ ችግር መታየቱን ገልጿል።

ከ87 ዓመት በፊት ኪቺሮ ቶዮታ በተባለ ግለሰብ የተመሰረተው ቶዮታ የተሽከርካሪ አምራች ኩባንያ አሁን ላይ በዓመት 10 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎችን በማምረት ላይ ይገኛል።

ከ360 ሺህ በላይ ሰራተኞች ያሉት ቶዮታ ኩባንያ 300 ቢሊዮን ዶላር የተጣራ ሀብት እንዳለው የኩባንያው ዓመታዊ ሪፖርት ያስረዳል።

#ጥቆማ ፦ ከደህንነት ጋር በተያይዘ በተለይም በአሜሪካ እንዲሰበሰቡ የታዘዙ ተሽከርካሪዎችን ቼክ ለማድረግ https://www.nhtsa.gov/recalls በዚህ አድራሻ መጠቀም ይቻላል። የመኪናውን መለያ ቁጥር (VIN) በማስገባት ማወቅ ይቻላል።

Credit - #AlAiN / #Reuters / #Toyota_News_Room

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ፤ የገና ሥጦታ ሎተሪ በትላንትናው ዕለት መውጣቱን ገልጿል።

10 ሚሊዮን ብር የሚያስገኘው የዕጣ ቁጥር 1616519 ሆኖ ወጥቷል።

አጠቃላይ የዕጣ ዝርዝሩ ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
#የሥዕል_ውድድር #ጥቆማ

በመቐሌ እና አከባቢው የምትገኙ የሥዕል ችሎታ ያላችሁ ወጣቶች ሪድም ዘጀነሬሽን ከUSAID/OTI ጋር በመተባበር ላዘጋጀው የቡድን የስዕል ውድድር ላይ እንድትሳተፉ ጥሪ አቅርቧል።

ከዚህ ቀደም በሰላም ጉዳዮች ላይ ተከታታይ ውድድሮች ያካሄደው ሪድም ዘጀነሬሽን አሁን ደግሞ በመቐሌ ለሚገኙ ችሎታው ላላቸው እድሜያቸው 13 - 18 ላሉ ታዳጊዎችና 19 - 29 ላሉ ወጣቶች በአጠቃላይ ለ50 ተሳታፊዎች እድሉን አመቻችቷል።

ዘላቂ ሠላም፤ ጽናት፤ እንዲሁም የማኅበራዊ ችግሮችን ማከም በሚችሉ ኃሳቦች ላይ ተወዳዳሪዎች ተመርጠው የሥዕል ውድድሩ ላይ እንዲሳተፉ ይደረጋል። በውድድሩ የተመረጡ ሥራዎች በክልሉ በሚዘጋጁ ፎረሞች ላይ የሚቀርብ ይሆናል።

ፍላጎት ያላቸው አመልካቾች፥ እስከ ጥር 24 ድረስ ማመልከት የሚችሉ ሲሆን በተከታዩ ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።  https://forms.gle/qYmEMneTagoSgKVQA

ዝርዝር መስፈርቱን ለማግኘት https://telegra.ph/Art-as-a-path-to-Healing-01-29

@TikvahethMagazine
#ጥቆማ

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ፤ የመኖሪያ እና የንግድ ቤቶችን በጨረታ ለሽያጭ አቅርቧል።

ኮርፖሬሽኑ ፤ " ያለብኝን የፋይናንስ እጥረት በመፍታት ተጨማሪ ወጪ ቆጣቢ ቤቶችን ገንብቼ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እንድችል ከዲዛይን ግንባታ ቢሮ ጋር በመሆን በመንግስት በተመደበ ካፒታል በጀት በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ተገንብተው #የተጠናቀቁ
➡️ 3,146 የመኖሪያ ቤቶችን
➡️ 306 የንግድ ቤቶችን በድምሩ 3,452 ቤቶችን ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሬ በሽያጭ ማስተላለፍ እፈልጋለሁ " ሲል አሳውቋል።

ማንኛውም ለጨረታ የቀረቡ የመኖሪያ እና የንግድ ቤቶችን ለመግዛት የሚፈልግ ሁሉ ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ የጨረታ ሰነድ ከ27/05/2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 20/06/2016 ዓ.ም ድረስ ቅዳሜን እስከ 11፡00 ሰአት እና እሁድ ግማሽ ቀን ጨምሮ ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 1፡30 እስከ ማታ 1፡30 ድረስ በመቅረብ የማይመለስ ብር 1000.00 (አንድ ሺህ) በመክፈል የጨረታ ሰነዱ መግዛት ይችላል ተብሏል።

የሰነድ መሸጫ ቦታ ከላይ ባለው ሰንጠረዥ ተመላክቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ከአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ማግኘቱን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

በኢትዮጵያ አየር መንገድ ፤ የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ #በግል_ከፍለው የአዉሮፕላን አብራሪነት ስልጠና ለሚፈልጉ ጥሪ አቀረበ።

ዩኒቨርሲቲው ፤ ለአዉሮፕላን አብራሪነት ስልጠና ለአጭር ጊዜ የሚቆይ የ10% ቅናሽ ማድረጉንም አሳውቋል።

" በግል ከፍለው የአውሮፕላን አብራሪ ለመሆን ለሚማሩ ስልጠናውን ለመስጠት ተዘጋጅቻለሁ " ያለው የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩንቨርስቲ አመልካቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው ብሏል።

1ኛ. የትምህርት ደረጃ ፦ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት የወሰዱ፣ እንዲሁም ፦
* በሂሳብ፣
* በእንግሊዘኛ
* በፊዚክስ ዉጤት አመርቂ አፈጻጸም ያስመዘገቡ

2ኛ. ዕድሜ ፦ 18 እና ከዚያ በላይ

3ኛ. እንግሊዘኛ ፦ ደረጃ 4

4ኛ. ቁመት፦ 1ሜ 62 ሴ.ሜ እና ከዚያ በላይ

5ኛ. የጤና ሁኔታ፦ ደረጃ 1 የጤና ሰርተፊኬት

የስልጠናው ርዝማኔ 1 አመት ከ 3 ወር ነው ተብሏል።

" የተደረገው ቅናሽ ለአጭር ጊዜ የሚቆይ ነው " ያለው ዩኒቨርሲቲው ፤ " የምዝገባ ሂደቱን ለማወቅ እና ለበለጠ መረጃ በኢሜል አድራሻ ፦ etauinfo@ethiopianairlines.com / eaainfo@ethiopianairlines.com ያነጋግሩን " ብሏል።

ስልክ በመደወል መረጃ ለመቀበል የምትፈልጉም +251-115174600/8598 ነው ተብሏል።

ከዚህ ባለፈ የዩኒቨርሲቲውን ድረገፅ መመልከት ይቻላል ፦ ethiopianaviationuniversity.azurewebsites.net/admission/applyonline

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ክረምቱ ይገባል በኛ በኩል ጊዜውን ከዚህ በላይ መግፋት አንችልም " - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ " ምርጫው የሚደረግባቸው አካባቢዎች የፀጥታ ሁኔታ፣ የበጀት እና ድምፅ የሚሰጥበት ቀን እና ጊዜ ይታሰብበት " - ተፎካካሪ ፖርቲዎች እና ሲቪክ ማህበራት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በፀጥታ ችግር ምክንያት 6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያልተደረገባቸው እና ቀሪ ምርጫ የሚደረግባቸው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣…
#ጥቆማ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ አስፈፃሚዎችን አወዳድሮ መቅጠር እንደሚፈልግ ገልጿል።

ቦርዱ ፦

👉 በአፋር ክልል (በ ዞን 5 በሚገኙ ወረዳዎች በሙሉ ፣በ ዞን 3 ቡሬሞዳይቱ እና ገዋኔ፤ በዞን 2 ዳሎል እንዲሁም በዞን 4 ጉሊና) የምርጫ ክልሎች

👉 በቤንሻንጉል ጉምዝ በአሶሳ ዞን አሶሳ ሆሃ፣ አሶሳ መገሌ፣ መንጌ እና ኦዳብልድጉል፤ በካማሺ እና መተከል ዞኖች ሁሉም ወረዳዎች

👉 በሶማሌ ክልል ጅጅጋ ከተማ

👉 በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መስቃን ማረቆ 2 ላይ ምርጫ ለማካሄድ ዝግጅት እያደረገ ነው።

ይህንን ተከትሉ መስፈርት የሚያሟሉ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር እንደሚፈልግ ገልጿል።

➡️ ከ18 አመት በላይ የሆናቸው
➡️ ከዚህ በፊት በምርጫ አስፈጻሚነት ያገለገሉ
➡️ የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆኑ
➡️ 12ተኛ ክፍል እና ከዛ በላይ የትምህርት ዝግጀት ያላቸው
➡️ በተጠቀሱት አካባቢዎች ላይ መስራት የሚችሉ አመልካቾች ከዛሬ ጀምሮ ለ 5 ተከታታይ ቀናት ክፍት በሚሆነው የቦርዱን የማመልከቻ ሊንክ ፦ https://pw.nebe-elections.org/recruitment  በመጠቀም ማመልከት እንደሚችሉ አሳውቋል።

ቦርዱ ፤ የሴቶችን እና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ እንደሚያበረታታ ገልጿል።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

" የ2024 ESP ማመልከቻ ማስገባት ይቻላል " - የአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ የEducation USA Scholars Program (#ESP) 2024 ማመልከቻ ክፍት መሆኑን አሳውቋል።

ESP በአካዳሚክ ጠንካራ የሆኑ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ወደ አሜሪካ ኮሌጆች እና ዩኒቨርሲቲዎች #እንዲያመለክቱ የሚረዳ የአራት ሳምንታት የሥልጠና መርሃ ግብር ነው።

ዓላማውም ደግሞ የነገዋን ኢትዮጵያ ለመገንባት የሰለጠኑ እና ከፍተኛ የትምህርት ዝግጅት ያላቸውን መሪዎችን ማፍራት እንደሆነ ኤምባሲው አመልክቷል።

ከአመልካቾች 20 ከፍተኛ የአካዳሚክ ብቃት ያላቸውን ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በኤምባሲው ይለያሉ። ተማሪዎቹ በአካዳሚክ ሪከርዳቸው፣ እንዲሁም በኢንተርቪው እንዲለዩ ይደረጋል።

ከጠቅላላው 20 የመጨረሻ እጩዎች መካከል፣ 15 ከፍተኛ ብቃት ያላቸው፣ በኢኮኖሚ የተቸገሩ ተማሪዎች ከመደበኛ ፈተናዎች፣ ከአሜሪካ ቪዛ ክፍያ ጋር የተያያዙ ወጪዎችን በሚሸፍነው የOpportunity Program Fund (#OPF) ፕሮግራም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይመረጣሉ።

የመጀመሪያዎቹ ጥቂት ስኬታማ ዕጩዎች ወደ አሜሪካ የራውንድ ትሪፕ ትኬት ያገኛሉ።

ቀሪዎቹ 5 ተማሪዎች በስልጠና ፕሮግራሙ ላይ #በነጻ ይሳተፋሉ ነገር ግን የዝግጅት ወጪን ከራሳቸው ምንጭ ይሸፍናሉ። የሞባይል ዳታ ወጪዎች ለሁለቱም የፕሮግራም ተሳታፊዎች በኤምባሲው ይሸፈናሉ።

ማመልከቻ እስከ ሚያዚያ 10/2024 (5:00 pm EAT) ማስገባት ይችላል ተብሏል።

ለማመልከት አስፈላጊ መስፈርቶች ምንድናቸው ?

ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩና ትምህርታቸውንም እዚሁ ኢትዮጵያ እየተከታተሉ ያሉ።

ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበ/ች #ኢትዮጵያዊ ተማሪ፣

በዚህ የትምህርት አመት መጨረሻ 11ኛ ክፍልን ያጠናቅቁ እና ከመስከረም 2024 ጀምሮ 12ኛ ክፍል የሚማሩ፣

በጠቅላላ 4 ሳምንታት የESP መርሃግብር ለመሳተፍ ቃል መግባት የሚችሉ መሆን አለባቸው።

ስታመለክቱ የሚያስፈልጉ ፦
1ኛ. የሁለተኛ ደረጃ ትራንስክሪፕት (9፣ 10፣ 11)
2ኛ. ከትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ
3ኛ. የኢኮኖሚ ችግር ያለባቸውና ለOpportunity Fund Program (OFP) የሚያመለክቱ ከትምህርት ቤት ወይም ከቀበሌ የቤተሰብን #ዝቅተኛ የኢኮኖሚያ ሁኔታ የሚያረጋግጥ ደብዳቤ ማቅረብ ያስፈልጋል።

የማመልከቻ ሊንክ እና ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ በዚህ ይመልከቱ ፦ https://sites.google.com/amspaceseth.net/educationusa-esp2024

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

(ለተማሪዎች እና ለወላጆች)

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለ2 ወር የሚቆይ የAI ሰመር ካምፕ የስልጠና መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጀቱን ገልጿል።

በስልጠናው መርሃ ግብር ላይ መሳተፍ የሚችሉት የመጀመሪያ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆኑ ናቸው።

ተማሪዎቹ ስልጠናውን በሳምንት ለ4 ቀናት መከታተል የሚችሉ መሆን አለባቸው።

ለተከታታይ 2 ወራት ለሚሰጠው ስልጠና ፍላጎት ያላቸው ታዳጊዎች ከዛሬ ጀምሮ እስከ ግንቦት 07/2016 ባሉት ተከታታይ ቀናት መመዝገብ ይችላሉ።

ስልጠናው የሚያተኩርባቸው ፦
➡️ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መሰረታውያን፣
➡️ ሮቦቲክስ፣
➡️ ፕሮግራሚንግ፣
➡️ ማሽን ለርኒንግ
➡️ ኢንተርኔት ኦፍ ቲንግስ (IoT) እንደሆኑ ተገልጿል።

በስልጠናው መሳተፍ የሚፈልጉ አመልካቾች ፦

👉 forms.gle/9B79pzGLdo84W2LY8

👉 https://www.aii.et/summer-camp-registration-form-for-student/ ላይ መመዝገብ ይችላሉ።

በተጨማሪ እውቀትና ክህሎታቸውን ለተማሪዎች በማካፈል በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ ትውልዱን ለመገንባት ዕድሉን የሚፈልጉ አሰልጣኞች ፦

👉 www.aii.et/ethiopian-ai-summer-camp-2024-application-form-trainer-for-summer-camp/

👉 forms.gle/P2vAoZuWT7JgYQtT6 ላይ መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።

#AI #ETHIOPIA

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

° በኢትዮጵያ 1.1 ሚሊዮን ህጻናት መደበኛ ክትባት ወስደው አያቁም።

° የአለም የህጻናት አድን ድርጅት ከክትባት ጋር የተያያዘ ችግሮችን የሚፈቱ የፈጠራ ስራዎችን እያወዳረ ነው።


አፍሪካ በዓለም ' ዜሮ ዶዝ ' ህፃናት ከሚገኙባቸው አህጉራት በቁጥር ከፍተኛውን ደረጃ ትይዛለች። ይህም ማለት መደበኛ ክትባት ወስደው የማያውቁ 8.7 ሚሊዮን ህፃናቶች አሉ ማለት ነው፡፡

ከእነዚህ ህፃናት ውስጥ ከአንድ ሦስተኛ በላይ የሚሆኑት የሚኖሩት በናይጄሪያ እና ኢትዮጵያ ውስጥ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ 1.1 ሚሊዮን ህጻናት መደበኛ ክትባት ወስደው አያቁም።

በተጨማሪም ወረርሽኝ ፣ ድህነት ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ፣ አለመረጋጋት፣ ግጭቶችናና ተያያዥ ምክንያቶች የክትባት መርሃግብሮችን እየተስተጓጎሉ ይገኛሉ።

የዓለም የህጻናት አድን ድርጅት (ሴቭ ዘ ችልድረን) እና ጂኤስኬ በመተባበር የክትባት አቅርቦትን እና አጠቃቀምን በተመለከተ ማንኛውንም አይነት ከክትባት ጋር የተያያዘ ችግሮችን የሚፈቱ የፈጠራ ስራዎችን በማወዳደር ላይ እንደሚገኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ጠቅሷል።

የተመረጡ ኃሳቦች / ሥራዎች በፕሮጀክት እስከ 100,000 ዶላር የሚደርስ የገንዝብ እንዲሁም የቴክኒክ ድጋፍ ይደረግላቸዋል ተብሏል።

ለማመልከት www.stc-accelerator.org ይጎብኙ።

የማመልከቻ ቀን እስከ #ግንቦት_16 ቀን 2016 ዓም ድረስ ነው።

ሁለተኛው የፈጠራ ጥሪ በ2017/2025 የሚካሄድ ይሆናል።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ( #INSA ) የ2016 ዓ/ም " National Cyber Talent Challenge Program " ማዘጋጀቱን ገልጿል።

በሳይበር ደህንነትና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ እና ፍላጎት ያላቸው በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ወጣቶች በሙሉ በዚህ ቻሌንጅ ላይ መሳተፍ ይችላሉ ተብሏል።

የታለንት መስኮች፦

- Cyber Security
- Cyber Development
- Embedded Systems
- Aerospace ናቸው።

ስልጠናው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለአንድ ወር ይሰጣል።

አመልካቾች በዌብሳይት  https://talent.Insa.gov.et በመግባት ከዛሬ ጀምሮ እስከ ግንቦት 30/ 2016 ዓ/ም መመዝገብ እንደሚችሉ ተገልጿል።

ለበለጠ መረጃ ደግሞ +251904311833 ፣ +251943579970፣ +251904311837 ላይ ስልክ መደወል ይችላል።

@Tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥቆማ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ( #INSA ) የ2016 ዓ/ም " National Cyber Talent Challenge Program " ማዘጋጀቱን ገልጿል። በሳይበር ደህንነትና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ እና ፍላጎት ያላቸው በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ወጣቶች በሙሉ በዚህ ቻሌንጅ ላይ መሳተፍ ይችላሉ ተብሏል። የታለንት መስኮች፦ - Cyber Security …
#INSA #ጥቆማ

የብሔራዊ የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ምዝገባ መካሄድ ጀምሯል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በ2014 ዓ/ም እና በ2015 ዓ/ም ለሁለት ተከታታይ አመታት በሳይበር ደህንነት እና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ታዳጊ ወጣቶች በክረምት ፕሮግራም (Summer Program) አሰልጥኖ ማስመረቁን ገልጿል።

ተመራቂዎችንም ፦

° #እንደየችሎታቸው እና #እንደስራዎቻቸው ከተለያዩ ባለሀብቶች ጋር የማስተሳሰር፤

° ኢመደአን (INSA) ጨምሮ በተለያዩ ተቋማት #ተቀጥረው መስራት የሚችሉበት ሁኔታ እንዳመቻቸ አመልክቷል።

ባለፉት ሁለት አመታት የተከናወኑ የሳይበር ታለንት ልማት ፕሮግራሞችን መነሻ በማድረግ በ2016 በጀት አመት “ብሄራዊ የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ” ፕሮግራም መዘጋጀቱ ተገልጿል።

የዚህ ቻሌንጅ ዋና ዓላማ በሳይበር ደህንነት እና ተያያዥ መስኮች ልዩ ተሰጥዖ ያላቸዉን ሰዎች በመመልመል በዘርፉ ላይ ተጨባጭ ተጽዕኖ መፍጠር የሚችል ብሄራዊ የሳይበር ሰራዊት (National Cyber Army) መገንባት ነው ተብሏል።

በሳይበር ደህንነት እና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ እና ፍላጎት ያላቸው እና እድሜያቸው ከ11 አመት ጀምሮ ያሉ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በዚህ ቻሌንጅ ላይ መሳተፍ ይችላሉ ተብሏል።

መመዝገቢያ ጊዜ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ግንቦት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ነው።

መመዝገቢያ አድራሻው https://talent.insa.gov.et ነው።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

ከ3500 ዶላር እስከ 10 ሺ ዶላር የሚያሸልመው ለግብርና መሻሻል የሚረዱ የቴክኖሎጂ ውድድር መጀመሩን " አዩቲ ኢትዮጵያ ቻሌንጅ " ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

ሄፈር ኢንተርናሽናል የውድድሩ አዘጋጅ ባሳወቀው መሠረት፣ የውድድሩ ዓላማ የአርሶ አደሮች ምርታማነትን መጨመር የሚያስችሉ፣ ድካም የሚቀንሱ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሀሳብ ማቅረብ ነው።

ወድድሩ ሲካሄድ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ሲሆን፣ የሚወዳደሩት ከ18 - 30 የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እንደሆኑና ተገልጿል።

የፈጠራ ሀሳባቸውን በ #ኦንላይን ማስገባት እንዳለባቸው ተመላክቷል።

የውድድሩ አሸናፊዎች በምን መልኩ ይለያሉ ?

➡️ ተወዳዳሪዎቹ ከሚያቀርቧቸው የቴክኖሎጂ ሀሳቦች 30ዎቹ በዳኞች ይመርጣሉ፣
➡️ ዳኞች በተገኙበት 30ዎቹ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ፣
➡️ ከ30ዎቹ 10 ሀሳቦችን ዳኞች ይመርጣሉ፣
➡️ 10ሩ ተወዳዳሪዎች ለ10 ቀናት ይሰለጥናሉ፣
➡️ ከስልጠናው በኋላ የመጨረሻ የ3 ተወዳዳሪዎች ሀሳብ ይመረጣል።

የሽልማት አሰጣጡ በምን መልኩ ነው ?

1ኛ ለወጣው 10 ሺህ ዶላር፣

2ኛ ለወጣው 6 ሺህ 500 ዶላር፣

3ኛ ለወጣው ሀሳብ ደግሞ 3 ሺህ 500 ዶላር የሥራ ማስጀመሪያ እና የማበረታቻ ሽልማት ይደረግላቸዋል።

ከዚህ ቀደም በተካሄዱት 2 ውድድሮች የተለያዩ የግብርና ዘርፍ ላይ ያተኮሩ አጠቃላይ 12 የፈጠራ ቴክኖሎጂዎች ተግባር ላይ መዋላቸው ተነግሯል።

ማመልከቻ ፦ https://ayute-ethiopia.et/apply-here/

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@TikvahEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#INSA የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ያዘጋጀው የ2016 ዓ/ም “ ብሄራዊ የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ” ፕሮግራም ምዝገባ እስከ ሰኔ 10/2016 ዓ/ም ድረስ መራዘሙን አሳውቋል። እስካሁን በርካታ ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ታዳጊ ወጣቶች መመዝገባቸው ተገልጿል። ምዝገባው እስከ ሰኔ 10 ድረስ መራዘሙ ተጠቁሟል። በሳይበር ደህንነት እና በተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ታዳጊ ወጣቶች…
#ጥቆማ

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) ባዘጋጀው የ2016 ዓ/ም “ ብሄራዊ የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ” ፕሮግራም ላይ ተመዝግበው ለ3ኛ ዙር ፈተና ያለፉ ነዋሪነታቸውም በአዲስ አበባ ከተማ ለሆኑ ፈተናው የሚሰጠው ከማክሰኞ ሐምሌ 9/2016 ዓ/ም እስከ ዓርብ ሐምሌ 12/2016 ዓ/ም መሆኑን ተቋሙ አስታውቋል።

ወደ 3ኛው ዙር ፈተና ያለፉ ስም ዝርዝር በ ' INSA የሳይበር ታለንት ማእክል ' የቴሌግራም አድራሻ ➡️ https://publielectoral.lat/cteinsa ላይ በመግባት ማየት እንደሚቻልም ተገልጿል። #INSA

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

ኢትዮጵያ 5 ሚሊዮን
#ኮደሮችን ለማሰልጠን ያለመ ፕሮጀክት አስጀምራለች።

ለ3 ዓመታት ያህል የሚቆየው ይሄ ፕሮጀክት ከተባበሩት አረብ ኤሜሪትስ (UAE) ጋር በመተባባር የሚተገበር ነው ተብሏል።

ምን መማር ይቻላል ?

- Android Kotlin Development Fundamentals
- Data Science Fundamentals
- Programming Fundamentals

ትምህርቱን እንዴት ማግኘት ይቻላል ?

ስልጠናዎቹ በዩዳሲቲ (Udacity) በተሰኘው ኦላይን የትምህርት ፕላትፎርም ተዘጋጅተው የቀረቡ ናቸው።

ሰልጣኞች ያለ አንዳች ክፍያ በነጻ ኮምፒውተራቸውን ወይም ስልካቸውን በመጠቀም መሰልጠን ይችላሉ።

ስልጠናዎቹ 6-7 የሚሆኑ ሳምንታትን የሚፈጁ ሲሆን በማጠቃለያው ላይ ሞያዊ ሰርተፊኬት ይሰጣል።

የስልጠናዎቹን ይዘት እንዲሁም ተጨማሪ መረጃዎች በተዘጋጀው ድረ-ገጽ (
https://ethiocoders.et/ ) ላይ መመልከት ይችላሉ።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

43,500 የመስክ መረጃ ሰብሳቢዎች ይፈለጋሉ ፤ ሞክሩት።

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2017 የበጀት ዓመት ለሚያካሂደው የሁለተኛው ዙር የግብርና ናሙና ቆጠራ 43500 የመስክ መረጃ ሰብሳቢዎች አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡

ቅጥሩ 1 ዓመት ነው።

ለሥራው ማመልከት የሚፈልግ ማንኛው ዜጋ በአካል መገኘት ሳይጠበቅበት ይህን የሌበር ማርኬት ፖርታልን
http://lmis.gov.et በመጠቀም ማመልከት ይችላል።

መስፈርቶቹ ምንድናቸው ?

➡️ የትምህርት ደረጃ ፡- በማንኛውም የትምህርት መስክ የመጀመሪያ ዲግሪና ከዚያ በላይ ያለው ሆኖ ፖርታል ላይ በተገላጸው መሠረት፣
➡️ የስራው ቆይታ ፦ 1 ዓመት
➡️ ቋንቋ ፦ ለሥራ የሚመዘገቡበትን አካባቢ ቋንቋ የሚችል
➡️ ፆታ ፦ አይለይም
➡️ የጤና ሁኔታ ፡- በገጠርና በከተማ ቀበሌዎች ተዘዋውሮ መስራት የሚችልና ለዚህም ፍቃደኛ የሆነ

ለመመዝገብ ምን መከተል ይገባል ?

1. በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ የሌበር ማርኬት ፖርታል ላይ ይህን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም መረጃውን
lmis.gov.et መሙላት፣

2. ምዝገባ ካጠናቀቁ በኋላ በስልካችሁ የሰራተኛነት መለያ ቁጥር ይደርሶታል፣

3. የደረሰዎትን የሰራተኛነት መለያ ቁጥር በመያዝ እና አቅራቢያችሁ ወደሚገኝ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ በመሄድ አሻራ መስጠትና ምዝገባውን ማጠናቀቅ።

መረጃው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎትና የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ነው።

#Ethiopia

@tikvahethiopia