#ጥቆማ

የኢሰመኮ 3ኛ ዙር የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፎች እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር ላይ ተሳተፉ !

መኖሪያ ቤት/ቦታ ማለት ለአንድ ሰው ወይም ለአንድ ቤተሰብ ምን ማለት ነው ?

ሕይወት፣ ትርጉም ያለው ሕይወት፣ ምንድን ነው ? የአንድ ኢትዮጵያዊት ሴት፣ ወይም የአካል ጉዳተኛ ወይም የተፈናቃይ ወይም የአረጋዊ ሕይወት ምን ይመስላል ?

በሕይወት እና በመኖሪያ ቤት ዙርያ እነዚህን እና የመሳሰሉ ጥያቄዎች ለኪነጥበብ አፍቃሪዎች፣ ለኪነጥበብ ሙያ ተማሪዎች፣ ባለሞያዎች እና አማተሮች እንዲሁም ለመገናኛ ብዙኃን አባላት እና ሌሎችም በኪነጥበብ እና በሰብአዊ መብቶች መካከል ያለውን ትስስር ማሳየት ለሚፈልጉ ሁሉ፣ በኢሰመኮ አዘጋጅነት በሚካሄደው የ3ኛው ዙር የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር የቀረቡ ናቸው።

ኑ፣ ተሳተፉ፣ አብረን እንድናሰላስል የሚረዱ የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልም ሥራዎቻችሁን ለዕይታ አቅርቡ!
በውድድሩ ለመሳተፍ እና ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ዝርዝሩን በዚህ ይመልከቱ - https://bit.ly/46sReAw