TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከዓለም ዙሪያ 📣

➡️ #ካሜሮን፦ በካሜሩን መገንጠልን አላማቸው አድርገው ይንቀሳቀሳሉ የተባሉ ታጣቂዎች ናይጄሪያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኝ መንደር በፈጸሙት ጥቃት በትንሹ 20 ሰዎችን መግደላቸው ተሰምቷል። ጥቃቱ ባሳለፍነው እሁድ በደ/ምዕራብ የካሜሩን ክፍል ኦቦኒ ሁለት በተሰኘ መንደር የተፈፀመ ሲሆን ከሞቱ ሰዎች ባሻገር ከ60 በላይ ሰዎች ቆስለዋል። ታጣቂዎቹ ነዋሪዎቹ በየወሩ ገንዘብ እንዲከፍሏቸው ይፈልጋሉ፤ ነዋሪዎቹ ደግሞ ፍቃደኛ አልሆኑም። ለዚህም ነው ጥቃት ያደረሱባቸው ተብሏል።

➡️ #ሜክሲኮ ፦ በደቡባዊ ሜክሲኮ በተፈጠረ የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋ በትንሹ 10 ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች የገቡበትን ማወቅ እንዳልተቻለ ተሰምቷል።

➡️ #ቻይና ፦ የሻንጋይ ነዋሪዎች ከሁለት ወር በኃላ የኮቪድ-19 የእንቅስቃሴ ገደብ መነሳቱን ተከትሎ ነፃ ሆነዋል። ነዋሪዎች ባለፉት 2 ወር ኮቪድ-19ኝን ለመከላከል በተጣለ የእንቅስቃሴ ገደብ ምክንያት ከእንቅስቃሴ ርቀው ቆይተዋል።

➡️ #ዩክሬን ፦ የየክሬን ኬርሰን ግዛት በሩስያ ቁጥጥር ውስጥ የሚገኝ ሲሆን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ሁሉንም የግንኙነት መስመሮች እንዲዘጉ ማድረጋቸው ተነግሯል።

➡️ #አሜሪካ ፦ የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ሀገራቸው ለዩክሬን 'ቁልፍ ኢላማዎችን' ለመምታት የሚያስችላትን እጅግ የዘመኑ ሮኬቶችን እንደምትልክ አሳውቀዋል።

➡️ #ሶማሊያ ፦ ወደ ባይዶዋ እንደሚሄዱ የተነገረላቸው አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ፕሬዝዳንት ከሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ ግዛት መሪ አብዲአዚዝ ሀሰን ሞሀመድ እና ከባህላዊ የሀገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል። ፕሬዜዳንቱ ወደ ባይዶዋ ያደረጉት ጉዞ ዳግም ፕሬዜዳንት ሆነው ከተመረጡ በኃላ የመጀመሪያቸው ነው።

#ቲአርቲ #ቢቢሲ #ፍራንስ24 #ሲጂቲኤን

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#US በየጊዜው በርካቶች በታጣቁ ሰዎች በሚከፈት ተኩስ የሚገደሉባት ሀገረ አሜሪካ ትላንትም እጅግ በጣም ዘግናኝ የሚባል ጥቃት ተፈፅሞ 2 አዋቂዎችን ጨምሮ 19 ሕጻናት ተገድለዋል። በአሜሪካ ቴክሳስ ግዛት አንድ የ18 ዓመት ወጣት በከፈተው የተኩስ እሩምታ 2 አዋቂዎችን ጨምሮ 19 ሕጻናት መገደላቸውን ተዘግቧል። ድርጊቱ የተፈፀመው በደቡብ ቴክሳስ ግዛት፣ ዩቫልዲ ከተማ ሮብ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት…
#አሜሪካ

በአሜሪካ ኦክላሆማ ግዛት ቱልሳ በተሰኘች ከተማ ሆስፒታል ውስጥ በተከፈተ ተኩስ አራት ሰዎች መገደላቸውን እና በርካቶች መቁሰላቸውን ፖሊስ ገልጿል።

ትኩስ እንደከፈተ የተጠረጠረው እና ጠመንጃ እና ሽጉጥ ታጥቆ የነበረው ግለሰብ መሞቱንም ፖሊስ አረጋግጧል።

ፖሊስ ጥቃቱ በተሰነዘረበት ቅዱስ ፍራንሲስ ሆስፒታል በሦስት ደቂቃ የደረሰ ሲሆን በጥቃቱ የሚጎዱ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስ በስፍራው በአስቸኳይ መድረሱ ተገልጿል።

ትላንት ረቡዕ በተፈጸመው በዚህ ጥቃት በርካቶች መቁሰላቸውንም ባለሥልጣናት አረጋግጠዋል።

የቱልሳ ከተማ ምክትል የፖሊስ ኃላፊ ኤሪክ ዳላግሊሽ " አሁን ላይ አራት ሲቪል ሰዎች የሞቱ ሲሆን፣ ጥቃት አድራሹም ሞቷል " ብለዋል።  

እስካሁን ማንነቱ ያልተለየው ጥቃት አድራሽ እራሱ ሳያጠፋ እንዳልቀረ ተገምቷል።

ተጠርጣሪው ሁለት መሳሪያዎችን ታጥቆ የነበረ ሲሆን " አንደኛው ረዝም ያለ፣ ሌላኛው ደግሞ የእጅ ሽጉጥ ነው በስፍራው የተገኘው " ብለዋል የፖሊስ ኃላፊው። 

#ቢቢሲ

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ #አሜሪካ #ሩስያ

በመጪዎቹ ቀናት ኢትዮጵያ የሩስያ እና የአሜሪካ ባለስልጣናትን ታስተናግድለች።

ነገ ማክሰኞ የሩስያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
ሰርጌ ላቭሮቭ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ያደርጋሉ።

ለቭሮቭ በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት ለማድረግ ነው ነገ አዲስ አበባ የሚገቡት።

በአዲስ አበባ ቆይታቸው ፦
- በኢትዮጵያ እና ሩስያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ዙሪያ ውይይት ያደርጋሉ፤
- ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ እና ሩስያ መካከል የተፈረሙ ስምምነቶች ላይ ይመክራሉ፤
- ከአፍሪካ ህብረት ኃላፊዎች ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ላቭሮቭ ኢትዮጵያ ሲመጡ የመጀመሪያቸው አይደለም። እ.ኤ.አ 2018 ላይ ኢትዮጵያን ጎብኝተው ነበር።

(ሰርጌ ላቭሮቭ ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው ቀደም ብሎ #በግብፅ የስራ ጉብኝት አድርገዋል)

#US የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር ከሐምሌ 17- ሐምሌ 25 2014 ዓ.ም ኢትዮጵያን ጨምሮ በግብፅ፣ በዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ጉብኝት ያደርጋሉ።

በኢትዮጵያ ግብኝታቸው የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት በሰላም ለመቋጨት ሊደረግ የታሰበው የሰላም ድርድር ላይ ይወያያሉ።

በተጨማሪ ፦
- የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ያለበትን ሁኔታ ይገመግማሉ።
- በጦርነቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ አካላት ተጠያቂ ማድረግን በተመለከተ ይመክራሉ።

ሐመር የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሆነው ከተሾሙ በኃላ ወደኢትዮጵያ ሲመጡ ሁለተኛቸው ይሆናል ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ መጥተው ከምክትል ጠ/ሚ እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጋር መወያየታቸው አይዘነጋም።

(ማይክ ሐመር ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው በፊት #በግብፅ ጉብኝት ያደርጋሉ)

@tikvahethiopia
#አሜሪካ #ቪዛ

" አንዳንድ ተጓዦች የቪዛ ቃለመጠይቅ ቀጠሮ ለማግኘት ከ6 ወር እስከ አንድ ዓመት ድረስ ይፈጅባቸዋል "

ለጉብኝት ፣ ለሥራ ወይም ለመኖር ወደ አሜሪካ ለመጓዝ ቪዛ የሚጠይቁ አመልካቾች ከ1994ቱ የሽብር ጥቃት ወዲህ " እጅግ የተራዘመ " ቀጠሮ እንደሚሰጣቸው ተሰምቷል።

ይህ የተሰማው ሰሞኑን ከወጡ የሃገሪቱ የውጪ ጉዳይ መሥሪያ ቤት መረጃዎች እንደሆነ የአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ዘግቧል።

አንዳንድ ዓለምአቀፍ ተጓዦች የቪዛ ቃለ መጠይቅ ቀጠሮ ለማግኘት ከስድስት ወር እስከ አንድ ዓመት እንደሚፈጅባቸው ተናግረዋል።

በካቶ ኢንስቲትዩት የስደተኞች ፖሊሲ ኃላፊ ዴቪድ ቤየር ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል፤ " በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት የአሜሪካ ኤምባሲዎች ለ2 ዓመታት መዘጋታቸውና ቪዛ ‘መስጠት ማቆማቸው የፈጠረው ችግር ነው’ " ብለዋል።

“ በወረርሽኙ ምክንያት የተከማቸ ሥራ አለ፤ ከአንድ ዓመት በላይ ቀጠሮ ያስፈለገውም ለዚሁ ነው ” ሲሉ አክለዋል።

የቀጠሮ ርዝመት ከኤምባሲ ኤምባሲ ቢለያይም ‘አሁን ያለው ሁኔታ ግን ከ1994ቱ የሽብር ጥቃት ወዲህ የከፋ ነው’ ሲሉ ቤየር ገልፀዋል።

ከጥቃቱ ሁለት ዓመታት በኋላ ጉዳይ ለማስፈፀም የሚወስደው ጊዜ ሦስት ሳምንት ያህል እንደነበር አንድ የውጪ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ኃላፊ በወቅቱ ለአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ተናግረው ነበር።

የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ሠንጠረዥ እንደሚያሳየው ለአንዳንድ ቪዛ አመልካቾች ቃለ መጠይቅ ለማደረግ ከ1 ዓመት በላይ ሲወስድ የንግድና የጉብኝት ቪዛ አመልካቾች ደግሞ ከ6 ወራት በላይ እንደሚጠብቁ ተገልጿል።

አሜሪካ ለ40 ሃገሮች ተጓዦች ያለ ቪዛ ገብተው ለዘጠና ቀናት እንዲቆዩ እንደምትፈቅድ የአሜሪካ ሬድዮ ጣቢያ መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#USAirstrike

የአሜሪካ አየር ጥቃት - በጎረቤት ሶማሊያ !

በጎረቤታችን ሶማሊያ ሂራን ክልል የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር ኃይል የፀረ ሽብር ዘመቻ እያካሄደ ሲሆን ጦሩን ለመደገፍ #አሜሪካ የአየር ጥቃት መሰንዘር መጀመሯ ተገልጿል።

አሜሪካ የአየር ላይ ጥቃቱን እንድትሰነዝር የተጠየቀችው በሶማሊያ መንግስት መሆኑን የሀገሪቱ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።

በክስተቱ ንፁሀን ዜጎች ላይ ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም የተባለ ሲሆን አሜሪካ ለሶማሊያ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል አስታውቃለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TanaForum በባሕር ዳር ከተማ ሲካሄድ የነበረው 10ኛው ጣና ፎረም ዛሬ ተጠናቋል። ፎረሙ በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የሰላምና ደኅንነት ጥናት ተቋም የተዘጋጀ ሲሆን ለ3 ቀናት ሲካሄድ ነበር። በዛሬ መርሃ ግብር " የአፍሪካ የሰላምና ደህንነት ስነ ምህዳር እና ምላሾች" በሚል ርዕስ ዙሪያ የፓናል ውይይት ተካሂዶ ነበር በውይይት አፍሪካዊያን ምሁራን ከአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ አምባሳደር አቴ…
#TanaForum

የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠ/ሚ አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በጣና ፎረም የተናገሩት ፦

" ያለፈው ታሪካችን ሊያስተምረን ይገባል፤ ስለችግሮቻችን ማንንም አንወቅስም መውቀስ ካለብን ራሳችንን ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ በአክሱም ዘመን የነበረንን ስልጣኔ ተመልከቱ፤ በግብጽ የነበረንን የቀደመ ስልጣኔ አስቡ፤ ችግራችን የነበረንን ጥንታዊ ስልጣኔ እና ታሪክ በተገቢው መንገድ ለልጆቻችን አለማስተማራችን ነበር። አሁን ግን ለልጆቻችን ከማስተማራችን በፊት ስለራሳችን የተሳሳተውን እይታችን ማረም ይገባናል።

አዎ ! ላለፉት 40 እና 50 ዓመታት #አሜሪካ ለሀገሬ ኢትዮጵያ በመቶ ሚሊየኖች የሚቆጠር ዶላር አውጥታ ምግብ እረድታ ይሆናል፤ ነገር ግን አሜሪካ የረዳችን ከችግራችን በምንወጣበት መንገድ አልነበረም።

ግብርናችን እንዲሻሻል፣ ቴክኖሎጂ እንድንጠቀም እና የተሻሻለ አሰራርን እንድንተገብር ተደጋጋሚ ድጋፍ የጠየቅናት አሜሪካ በፖሊሲ ሰበብ ፈቃደኛ አልነበረችም።

ኢትዮጵያዊቷ ንግስት ሳባ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ ተሻግራ እንደ ሀገር ንጉስ ሰለሞንን ስትጎበኝ አሜሪካ እንደ አህጉርም እንደ ሀገርም አትታወቅም ነበር።

ከኋላ እየመጡ ለሚቀድሙን ሁሉ እርግጥ ነው ኅላፊነቱን መውሰድ ያለብን ራሳችን ነን።

የጣና ፎረም መንፈስም ችግርን በግልፅ ተናግሮ በጋራ እና በትብብር መፍትሔ መፈለግ ነው። "

Credit : AMC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አሜሪካ 500 ሺህ የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎችን እየገነባች እንደሆነ ፕሬዜዳንቷ ገልፀዋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደራቸው በመላ አገሪቱ 500,000 የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎችን እየገነባ እንደሆነ አሳውቀዋል። በአሜሪካ የኤሌክትሪክ መኪና ተገልጋዮች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣ ሲሆን ሀገሪቱም ይህንን በእጅጉ እያበረታታች ነው። በአሜሪካ…
#EV

አሁን ላይ በተለያዩ የዓለማችን ሀገራት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በብዛት ጥቅም ላይ እየዋሉ ይገኛሉ።

ከዓለማችን ሀገራት መካከል #አሜሪካ በ2050 ከካርቦን-ነፃ እንድትሆን አሽከርካሪዎች በነዳጅ ኃይል ከሚሰሩ ወደ ኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች እንዲቀይሩ ማድረግ ወሳኝ እንደሆነ ታምናለች።

በ2030 ከአዳዲስ የመኪና ሽያጭ ግማሹ የኤሌክትሪክ/ ሃይብሪድ ተሽከርካሪዎች እንዲሆኑ ግብ አላት፤ እ.ኤ.አ. በ2030 ግማሹ ኤሌክትሪክ ከሆኑ፣ በ2050 በአሜሪካ ጎዳናዎች ከሚሽከረከሩት መኪኖች ከ60-70 በመቶ የኤሌክትሪክ / ሃይብሪድ ተሽከርካሪዎች ሊሸፍኑ ይችላሉ።

ለዚህም የመኪና ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች በስፋት እየተገነቡ ይገኛሉ (እስከ 2030 ደረስ 500,000 የመገባት እቅድ አላት) ።

አሁን ላይ አሜሪካ ምን ያህል ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች አሏት ?

(እንደ ኤስ ኤንድ ፒ ሞቢሊቲ መረጃ)

- 126,500 ደረጃ ሁለት (የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በ5 ሰዓት ሙሉ የሚያደርጉ) ጣቢያዎች፤

- 20,431 ደረጃ 3 (ከ15-20 ደቂቃ ውስጥ ተሽከርካሪዎችን 80% የሚያደርጉ)  ጣቢያዎች፤

- 16,822 የቴስላ ሱፐርቻርጀር እና የቴስላ ቻርጅ ማድረጊያ መዳረሻዎች አሉ።

ኤስ ኤንድ ፒ ሞቢሊቲ፤ በ2025 እስከ 7.8 ሚሊዮን በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በአሜሪካ ጎዳናዎች ላይ ሊኖሩ እንደሚችሉ ተንብዮ ለዚህም 700,000 ደረጃ ሁለት እና 70,000 ሶስት የቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች ሊኖሩ ይገባል ብሏል።

በ2030 ደግሞ 28.3 ሚሊዮን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ይኖራሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ለዚህም 2.13 ሚሊዮን የደረጃ 2 እና 170,000 ደረጃ 3 የቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች ያስፈልጋሉ።

ይሄ የመኪና ባለቤቶች በቤታቸው ከሚገጥሙት የቻርጅ ማድረጊያ ተጨማሪ ነው።

@tikvahethiopia
አሜሪካ ...

የግድያ ወንጀል ስትዘግብ የነበረችው ጋዜጠኛ ተገደለች።

አሜሪካዊቷ ጋዜጠኛ በኦርላንዶ ፍሎሪዳ አቅራቢያ ትላንት ከሰዓታት በፊት የተፈጸመን የግድያ ወንጀል እየዘገበች በነበረችበት ወቅት #በጥይት ተመታ መገደሏን ቢቢሲ አስነብቧል።

ጋዜጠኛዋ የተገደለችው እየዘገበችው በነበረው የግድያ ወንጀል #ተጠርጣሪ (ስሙ ኬዝ ሞሰስ 19 ዓመቱ) ነው።

ከጋዜጠኛዋ በተጨማሪ የዘጠኝ ዓመት ታዳጊ በተተኮሰባት ጥይት #ተገድላለች

ሌላኛዋ ጋዜጠኛ እና የታዳጊዋ እናት በተመሳሳይ ታጣቂ ተመትተው ጉዳት እንደደረሰባቸው ፖሊስ ገልጿል።

ሁለቱ ጋዜጠኞች " ስፔክትረም ኒውስ " ለተባለው የቴሌቪዥን ጣቢያ የሚሰሩ ሲሆን በአካባቢው የጣቢያው 13 ጋዜጠኞች የአንድ ሴትን ግድያ ሲዘግቡ ነበር።

ግለሰቧን (እድሜዋ በ20ዎቹ ሲሆን መኪና ውስጥ ነበረች) የገደለው ተጠርጣሪ ተመልሶ መጥቶ እንደተኮሰባቸው ፖሊስ ገልጿል። ጋዜጠኞቹ ግድያው የተፈፀመበት ቦታ ደርሰው ሲዘግቡ ነበር።

እነሱም ኢላማ ተደርጎባቸው ስለመሆኑ ግልጽ አይደለም።

ተጠርጣሪው ጋዜጠኞቹ ላይ ከተኮሰ በኋላ በአቅራቢያው ወደሚገኝ ቤት ገብቶ አንዲት ህፃን እና እናቷ ላይ ተኩስ ከፍቶ ህጻኗን ሲገድል እናትየው በአስጊ ሁኔታ ላይ ትገኛለች።

ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ወቅት የጦር መሳሪያ ይዞ እንደነበርና ከፖሊስ ጋር ባለመተባበር እምቢተኝነቱን ማሳየቱን መርማሪዎች መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

በመላው #አሜሪካ በጦር መሳሪያ በሚደርሱ ጥቃቶች በየአመቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ህይወታቸውን ያጣሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#US አሜሪካ በአስከፊው ጓንታናሞ ቤይ እስር ቤት አስራው የነበረችውን አልጄሪያዊ ወደ ሀገሩ መለሰች። አሜሪካ በሀገሯ ውስጥ የ "ቦምብ ጥቃት ለማድረስ አቅደሃል" ብላ ለ20 ዓመታት ገደማ ያሰረችውን ሱፊያን ቡርሃሚ የተባለ አልጄሪያው ወደ ሀገሩ እንዲመለስ አድርጌዋለሁ ብላለች። በአስከፊው ጓንታናሞ ቤይ እስር ቤት አሜሪካ አስራ ያቆየችው እና አሁን መልሸዋለሁ ያለችው አልጄሪያዊ በፈረንጆቹ 2002 ፓኪስታን…
#አሜሪካ

አሜሪካ ያለ አንዳች ፍርድ ለ20 ዓመታት በ " ጓንታናሞ ቤይ " በሚገኘው እስር ቤት አስራ የቆየቻቸውን ሁለት ፓኪስታናውያን ወንድማማቾችን ከእስር ስለመልቀቋ ተነግሯል።

ጓንታናሞ ቤይ ውስጥ በሚገኘው የአሜሪካ ወታደራዊ እርስ ቤት ውስጥ ለ20 ዓመታት ያህል ታስረው የቆዩት ሁለቱ ፓኪስታናውያን ወንድማማቾች ምንም ክስ ሳይቀርብባቸው ነው የተለቀቁት።

አብዱል እና ሞሐመድ አህመድ ራባኒ ፓኪስታን " ካራቺ " ውስጥ ተይዘው ከአገራቸው የተወሰዱት በአውሮፓውያኑ በ2002 ነበር።

የአሜሪካ መከላከያ መ/ቤት አብዱል ራባኒ የተባለው ግለሰብ የ " አልቃኢዳን የመደበቂያ ቤት ያስተዳድራል " እንዲሁም ወንድሙ " የቡድኑ መሪዎችን ጉዞ እና ገንዘብን ይመራል " ብሎ ነበር።

ወንድማማቾቹ ወደ ጓንታናሞ ከመሸጋገራቸው በፊት ከአገራቸው ውጪ በሲአይኤ (CIA) መኮንኖች #ማሰቃየት እንደተፈጸመባቸው ገልጸዋል።

ሁለቱ ፓኪስታናውያን ከአስፈሪው ወታደራዊው እስር ቤት ከተለቀቁ በኋላ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል ተብሏል።

ጓንታናሞ ኩባ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን የአሜሪካ ባሕር ኃይል ሰፈር ከመስከረም 11 የሽብር ጥቃት በኋላ ተጠርጣሪዎችን ለማቆያነት በቀድሞ ፕሬዝዳንት ጆርጅ ቡሽ የተቋቋመው ነው።

ካምፑ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት አሜሪካ ካካሄደችው " ፀረ ሽብር ጦርነት " ጋር በያያዘ ከተፈጸሙ መጥፎ ድርጊቶች ጋር ስሙ ይነሳል።

በተለይ ተጠርጣሪዎች በምርመራ ጊዜ #ከባድ_ሰቆቃ እንደተፈጸመባቸው እና ያለፍርድ ለረጅም ጊዜ በእስር እንዲቆዩ መደረጋቸው ይነገራል።

ከ20 ዓመት በፊት በጓንታናሞ ውስጥ 680 አስረኞች የነበሩት ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ግን 32 እስረኞች ብቻ የሚገኙበታል።

#BBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

የእስራኤል እና የፍልስጤም ሃማስ ጉዳይ ወዴት ያመራ ይሆን ?

በእስራኤል እና በፍልስጤም ሃማስ መካከል እየተካሄደ ያለው ጦርነት እየተባባሰ መጥቷል።

ሀገራት የተለያዩ አቋማቸውን እያንፀባረቁ ይገኛሉ።

#ኢራን ፍልስጤም እና እየሩሳሌም ነፃ እስኪወጡ " ከፍልስጤም ተዋጊዎች ጎን ነኝ " ብላለች። #አሜሪካ በበኩሏ ከእስራኤል ጎን እንደሆነች ገልጻ የማያወላዳ ድጋፏን እንደምታደርግ አሳውቃለች።

የሁለቱ ሀገራት ጎረቤቶች ሁኔታውን በእንክሮ እየተከታተሉ በተጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ።

ይህ ሁኔታ በዚህ ከቀጠለ ዓለም አቀፍ ይዞታን ሳይዝ እንደማይቀር ተሰግቷል።

ከመሸ የተሰሙ አዳዲስ መረጃዎች ምንድናቸው ?

- እስራኤል ጋዛ ላይ እየወሰደች ባለው የአፀፋ እርምጃ 232 ፍልስጤማውያን ሲገደሉ፣ 1697 ቆስለዋል ፤ በርካቶች ለህይወታቸውን የሚያሰጋ ጉዳት ላይ ናቸው።

- ሃማስ ባካሄደው ወታደራዊ ኦፕሬሽን የተገደሉ እስራኤላውያን ቁጥር ወደ 200 ማሻቀቡ ተሰምቷል።

- እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ውስጥ የኃይል አቅርቦት በማቋረጧ ሆስፒታሎች ተጎጂዎችን ለማከም እየተፈተኑ ይገኛሉ ተብሏል። በጋዛ ኤሌክትሪክ እንዲቋረጥ ያዘዘው የእስራኤል ኢነርጂ ሚኒስቴር ነው።

- ፍልስጤም ፤ አንድ የ13 ዓመት ልጅን ጨምሮ 4 ፍልስጤማውያን በ " ዌስት ባንክ ' በእስራኤል ወታደሮች መገደላቸውን አሳውቃለች።

- የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ ኻሚኒ አማካሪ ያህያ ራሂም ሳፋቪ " የፍልስጤም ተዋጊዎች በእስራኤል ላይ ከዓመታት በኋላ ትልቁን ጥቃት በማድረሳችሁ እንኳን ደስ አላችሁ " ብለዋል።  " የፍልስጤም ተዋጊዎችን እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን። " ያሉት አማካሪው " ፍልስጤም እና እየሩሳሌም ነፃ እስኪወጡ ድረስ ከፍልስጤም ተዋጊዎች ጎን እንቆማለን። " ብለዋል። ኢራን የሃማስን ኦፕሬሽን " የሚያኮራ " ብላለች።

- ሃማስ በእስራኤል ላይ ከፈትኩ ያለውን ኦፕሬሽን ተከትሎ ከኢራን፣ ቴህራን ከፍተኛ የሆነ ደስታን የሚገልጹ ቪድዮዎች ወጥተዋል። በቪድዮዎቹ ቴህራን ውስጥ ርችት ሲተኮስ እና ሰዎች ደስታቸውን ሲገልጹ ይታያል (ቪድዮ ከላይ ተያይዟል)።

- አሜሪካ በዚህ ወቅት ከእስራኤል መንግሥት እና ህዝብ ጋር መሆኗን በመግለፅ የማያወላዳ ድጋፏን እንደምታደርግ አሳውቃለች። የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ተኩስ እንዲቆም ጠይቃለች። ቱርክ በንፁሃን ሞት ማዘኗን ገልጻ ግጭቱ ወደ ቀጠናው ሳይስፋፋ እንዲበርድ ድጋፏን እንደምታደርግ አሳውቃለች።

- NATO አጋሬ ናት ባለው እስራኤል ላይ የተፈፀመው የአሸባሪዎች ጥቃት መሆኑን ገልጾ ከተጎጂዎች ጋር እንደሚቆም እስራኤልን እራሷን የመከላከል መብት እንዳላት ገልጿል።

- የፍልስጤም ፕሬዝዳንት ማህሙድ አባስ የፍልስጤም ህዝብ ከ " ሰፋሪዎች እና ወራሪ ወታደሮች ሽብር " እራሱን የመከላከል መብት አለው ብለዋል።

- የእስራኤል ትምህርት ሚኒስቴር ነገ በመላው ሀገሪቱ ትምህርት እንዲዘጋ መወሰኑ ታውቋል።

በእስራኤል እና ሃማስ መካከል ወታደራዊ ግጭቱ የተነሳው ሃማስ ድንገተኛ እና ባለፉት በርካታ አመታት ታይቶ የማይታወቅ የተቀናጀ ኦፕሬሽን እስራኤል ላይ ከጀመረ በኃላ ነው።

ሃማስ ጦርነቱ " ከወራሪ ጋር የሚደረግ ጦርነት ነው " ብሏል። ፍልስጤማውያን ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ለደረሰባቸው ግፍ ሁሉ ምላሽ ነው ሲልም ገልጿል።

የእስራኤል ሀገር መከላከያ ሚንስቴር " ሃማስ ከባድ ስህተት ሰርቷል ፤ ለዚህም የከፋ ዋጋ እንደሚከፍል እና ለውጤቱም ሙሉ ኃላፊነቱን ይወስዳል " ካለ በኃላ የአየር ጥቃቶችን ጨምሮ የአፀፋ እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

• የሞቱ እስራኤላውያን ከ700 በላይ ሆነዋል። ከ350 በላይ ፍልሥጤማውያንም ህይወታቸው ጠፍቷል።

#ኢራን ፍልስጤምን ደግፋ ስትቆም ፤ #አሜሪካ ከእስራኤል ጎን መሆኗን አረጋግጣ ወታደራዊ ድጋፍ ማድረግ እንደምትጀምር አሳውቃለች።

በእስራኤል ጦርና በፍልስጤሙ ሃማስ መካከል ጦርነቱ ዛሬም ተባብሶ መቀጠሉን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። በተለይም እስራኤል ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ብርቱ ውጊያ እየተካሄደ ነው ተብሏል።

በጦርነቱ እስራኤል ውስጥ ከ700 በላይ #እስራኤላውያን መገደላቸው ተሰምቷል።

እስራኤል ተከፍቶብኛል ላለችው ጦርነት እየወሰደች ባለችው የአፀፋ እርምጃ በጋዛ ሰርጥ ከ350 በላይ #ፍልጤማውያን ተገድለዋል።

በአጠቃላይ ባለፉት ሰዓታት ብቻ እስካሁን ይፋ በተደረገው ከ1 ሺህ በላይ ሰዎች ሞተዋል።

በሺዎች የሚቆጠሩ ተጎድተዋል።

ጋዛ ውስጥ መሰረተልማቶች ፣ ህንፃዎች እንዳልነበሩ ሆነዋል፣ የኤሌክትሪክ ፣ የነዳጅና የፍጆታ እቃዎች አቅርቦት ተቋርጧል ፤ ያለው ሁኔታ እጅግ የከፋ ነው ተብሏል። ሰብዓዊ እርዳታ የሚገባበት መንገድ እንኳን የለም።

ይህ በእንዲህ እንዳለ እስራኤል የሊባኖሱ ሂዝቦላህ ከፍቶብኛል ላለችው ተኩስ በሊባኖስ በከባድ መሳሪያ የታገዘ ጥቃት ፈፅማለች።

ሂዝቦላም እስራኤል ላይ ተኩስ ስለመክፈቱ ኃላፊነቱን ወስዷል።

ተኩሱ የተከፈተው እስራኤል፣ ሊባኖስ እና ሶሪያ በሚወዛገቡበት ግዛት እና ሶስቱንም ሃገራት በሚያገናኛቸው የዶቭ ተራራ አካባቢ ነው።

እስራኤል የሊባኖስ ታጣቂ ሂዝቦላህ በውጊያው ውስጥ ጣልቃ እንዳይገባ አስጠንቅቃለች።

ሃማስ ፤ እስራኤል በወረራ ከያዘቻቸው ግዛቶች ለመጠራረግ ፍልስጥኤማውያን እንዲሁም ሌሎች አረቦች ትግሉን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርቧል።

እስራኤል ያለጥርጥር በበርካታ ግንባሮች ሊከፈት የሚችል ጦርነት ሊኖር እንደሚችል ነው እየታያት ያለው ተብሏል።

ምናልባትም ጦርነቱ የከፋ የሚሆነው ከፍተኛ ኃይል ያለውን የሊባኖሱን ታጣቂ ቡድን ሂዝቦላ መሳብ ከቻለ እንደሆነ ተነግሯል።

በእስራኤል እና የፍልስጤም ሃማስ ጦርነት ሀገራት የተለያዩ አቋማቸውን እያንፀባረቁ ሲሆን ኢራን የሃማስን ጥቃት ደግፋ ቆማለች።

ኢራን " የፍልስጤምን ሕጋዊ የመከላከል መብት እደግፋለሁ " ብላለች።

አሜሪካ በበኩሏ ከእስራኤል ጎን እንደሆነች በተደጋጋሚ እያረጋገጠች ነው ፤ ወታደራዊ ድጋፍም ለማድረግ እየተዘጋጀች መሆኑ ተሰምቷል። የአሜሪካ መከላከያ ድጋፉን ከዛሬ ጀምሮ የሚልክ ሲሆን በመጪዎቹ ቀናት ይደርሳል ተብሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የእስራኤል ጦር ከፍተኛ በሆነ ሁኔታ ወታደሮቹን እያሰማራ ሲሆን በጋዛ ላይ ተከታታይ የአየር ጥቃቶችን ከማድረግ በተጨማሪ የምድር ላይ ዘመቻ ለማድረግ ማቀዱን ተሰምቷል።

መረጃው ከቢቢሲ እና አልጀዚራን ጨምሮ ከሌሎች ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የተገኘ ነው።

More - @BirlikEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
የእስራኤልና ፍልስጤሙ ሃማስ ጦርነት በቀጣይ ምን ይዞ ይመጣ ይሆን ?

ዋና ነጥቦች ፦

▪️ሃማስ ፤ " ወራሪ " ናት በሚላት #እስራኤል ላይ  ወታደራዊ ኦፕሬሽን ማካሄድ መጀመሩንይህ ኦፕሬሽንም #ፍልስጤማውያን ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ለደረሰባቸው ግፍ ሁሉ ምላሽ እንደሆነ ገልጿል።

▪️ እስራኤል ፤ " አሸባሪ " የምትለው የሃማስ ቡድን ጥቃት መክፈቱ ከባድ ስህተት መሆኑን በመግለፅ ለእያንዳንዱ ድርጊቱ የከፋ ዋጋ እንደሚከፍልበት ፤ ለሚመጣው ነገር  ሁሉ ኃላፊነቱን እንደሚወስድ ገልጻለች። ሃማስ ላይም መጠነ ሰፊ የአፀፋ እርምጃ ጀምራለች።

▪️እስካሁን ከእስራኤል ከ700 በላይ ከፍልስጤም ከ400 በላይ ሰዎች አልቀዋል።

በእስራኤል እና ሃማስ ጦርነት ሀገራት እና መሪዎች አቋማቸውን እያንፀባረቁ ናቸው።

አንዳንዶቹ በግልፅ ሃማስን " የሽብር ቡድን " እንደሆነ ገልፀው ጥቃቱን ሲያወግዙ አንዳንዶቹ ደግሞ በሁለቱም በኩል ግጭት ቆመ በእርጋታ ነገሮች እንዲፈቱ እየጠየቁ ነው።

እስራኤል አጋሮቿ ሁሉ የተከፈተባትን ጥቃት በግልፅ እንዲያወግዙ ትሻለች።

በወታደራዊና ኢኮኖሚ አቅማቸው ጠንካራ የሆነ የዓለም ሀገራት ምን አቋም ነው የያዙት ?

🇺🇸አሜሪካ - የእስራኤል ወዳጇ #አሜሪካ የ ' ሃማስን ' ጥቃት የአሸባሪዎች ጥቃት ነው በማለት በግልፅ ጥቃቱን አውግዛ ለእስራኤል ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አደርጋለሁ ብላለች። ወታደራዊ ድጋፍም ልካለች።

🇫🇷ፈረንሳይ - የሃማስን ጥቃት " የአሸባሪዎች ጥቃት " ስትል ገልጻ ከእስራኤል ጎን እንዳሆነች ገልጻለች።

🇩🇪ጀርመን -ጥቃቱን አውግዛ ከእስራኤል ጎን መሆኗን ገልጻለች። ሃማስንም አሸባሪ ስትል ጠርታለች።

🇮🇳ሕንድ-እስራኤል የተፈፀመባት ጥቃት የአሸባሪዎች ጥቃት ነው ብላ ከእስራኤል ጎን መሆኗን ገልጻለች።

🇬🇧ዩናይትድ ኪንግደም - በእስራኤል ላይ " የሽብር " ጥቃት መፈፀሙን ገልጻ ሀገሪቱ እራሷን የመከላከል መብት አላት ብላለች። ከእስራኤል ጎን እንደሆነችም ገልጻለች።

_

🇮🇷ኢራን - " የፍልስጤም ህዝብ #ራሱን_የመከላከል መብት አለው " ብላ የሃማስን ጥቃት በግልፅ " አኩሪ ተግባር " ስትል አወድሳለች።  " ፍልስጤም እና እየሩሳሌም " ነፃ እስኪወጡ ከፍልሥጤም ተዋጊዎች ጎን እንቆማለን ብላለች።
_

🇨🇳ቻይና- ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት እንዲረጋጉ ፤ ራሳቸውን እንዲቆጣጠሩ እና ጦርነቱን በአስቸኳይ እንዲያቆሙ እንዲሁም ሲቪሎች እንዲጠበቁ ፤ የሁኔታውን እንዳይባባስም እንዲሰሩ አሳስባለች።

ቤጂንግ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ የቻይና አቋምን በተመለከተ እስራኤል ሃማስ ላደረሰው ጥቃት ከቻይና ጠንካራ ውግዘት ጠብቃ ነበር ብሏል።

ቻይና የሃማስ ታጣቂ ኃይልን እንደ አሸባሪ ድርጅት ሳይሆን እንደተቃዋሚ ኃይል ነው የምታየው።

🇸🇦 ሳዑዲ አረቢያ - ሀገሪቱ በቅርቡ ከእስራኤል ጋር ያላትን ግንኙነት ለማደስ እየተንቀሳቀሰች ሲሆን አሁን የተቀሰቀሰው ጦርነት በአስቸኳይ እንዲቆም ጥሪ አቅርባለች። ሁለቱም ወገኖች ግጭት እንዲያቆሙና ሲቪሎችም እንዲጠበቁ አሳስባለች።

🇦🇪የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ (UAE) - ያለው ሁኔታ እጅግ እንዳሳሰባት በመግለፅ ግጭት እንዲቆም እና ሲቪሎች እንዲጠበቁ ስትል ጥሪ አቅርባለች።

🇹🇷ቱርክ - በእስራኤልና ፍልስጤም ሃይሎች መካከል የሚካሄደውን ጦርነት ለማረጋጋት ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንደምታደርግ አቋሟን ገልጻለች። ለሁለቱ ሀገራት መፍትሄ ቀጣናዊ ሰላም ማስፈን ብቸኛ መንገድ ነው ብላለች። አሁን ላይ ያለው ከፍተኛ ውጥረት እንዲረግብ እንደምትሰራ ነው የገለፀችው።

🇷🇺 ሩስያ - ሩስያ በአቸኳይ #ተኩስ_እንዲቆም ጥሪ አቅርባለች።

_

አፍሪካውያን ምን አሉ ?

- የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር የሆኑት ሙሣ ፋኪ ማሃማት " የእሥራዔል-ፍልስጥዔም ቋሚ ውጥረት ዋናው ምክንያት የፍልስጥዔም ህዝብ መሠረታዊ መብቶቹን፣ በተለይም ነፃና ሉዓላዊ መንግሥት መነፈጉ ነው " ብለዋል። ሁለቱ ኃይሎች ግጭት አቁመው ወደ ድርድር ጠረጴዛ ይቅርቡ ብለዋል።


- የዩጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቨኒ " በእሥራዔል እና በፍልስጤም መካከል እንዳዲስ ግጭት መቀስቀሱ የሚያሳዝን ነገር ነው። ለምን ሁለቱም ወገኖች የሁለት መንግስት መፍትሄን ተግባራዊ አያደርጉም? በተለይ ደግሞ ሰላማዊ ዜጎችን እና ተዋጊ ያልሆኑ አካላት በታጣቂዎች ዒላማ መደረጋቸው መወገዝ አለበት " ብለዋል።

- #ኬንያ በፕሬዜዳንቷ በኩል ባወጣችው መግለጫ እስራኤል ላይ የተፈፀመው የሽብር ጥቃት መሆኑን በመግለፅ ከእስራኤል ጎን እንደሆነች ገልጻለች።   በተጨማሪ ግጭቱ እንዲበርድ እና እስራኤልም ፍልስጤምም ከወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዲቆጠቡ ብላለች።

የUN ፀጥታ ም/ቤት ስብሰባ በምን ተጠናቀቀ ?

ትላንትና ምሽት የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት በእስራኤል - ጋዛ ጦርነት በዝግ አስቸኳይ ስብሰባ ቢቀመጥም አባል ሀገራቱ መስማማት ስላልቻሉ የጋራ መግለጫቸውን ማውጣት አልቻሉም።

አሜሪካ 15ቱ የፀጥታው ምክር ቤት አባላት #ሃማስን አጥብቀው እንዲያወግዙ መጠየቋ ተሰምቷል።

የአሜሪካው ከፍተኛ ዲፕሎማት የሆኑት ሮበርት ዉድ ፤ " የሃማስን ጥቃት ያወገዙ ብዙ አገሮች አሉ። ሁሉም እንዳልሆኑ ግልፅ ነው " ያሉ ሲሆን " እኔ ምንም ሳልናገር ከመካከላቸው አንዱን ማወቅ ትችላላችሁ " ሲሉ ሩስያ ጥቃቱን ካላወገዙት ውስጥ እንደሆነች ተናግረዋል።

መረጃዎቹ ከዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የተሰባሰቡ ናቸው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
ኤርዶጋን ምን አሉ ?

የቱርክ ፕሬዝዳንት ሪሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን በእስራኤል እና ፍልስጤም ግጭት ዙሪያ ይህን ብለዋል ፦

- በሲቪሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ወይም በሲቪል አካባቢዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ትክክል አይደለም፤ አንቀበለውም።

- በእስራኤል ግዛት በሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚደርሰውን ግድያ እንቃወማለን።

- በጋዛ ውስጥ ንጹሃን  ያለየ ' #ጭፍጨፋ ' በፍጹም አንቀበልም።

- አሳፋሪ ዘዴዎችን በመጠቀም የሚካሄደው ግጭት ፣ ጦርነት ሳይሆን ' ጭፍጨፋ ' ነው።

- ማንኛውም አካል ፍልስጤማውያንን 🇵🇸 ለመቅጣት ዓላማ ካላቸው ውሳኔዎች መራቅ አለበት።

- ሽምግልና እና ፍትሃዊ ዳኝነትን ጨምሮ የምንችለውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነን።

በእስራኤል እና በፍልሥጤሙ ሃማስ መካከል ቅዳሜ የጀመረው ደም አሳፋሽ ግጭት ዛሬም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን ሃማስ ወደ ቴላቪቭ እና ማዕከለኛው እስራኤል ሮኬቶችን ሲያስወነጭፍ ውሏል።

እስራኤል የምትወስደውን የአስፀፋ እርምጃ አጠናክራ ቀጥላለች። ሠራዊቷን ጋዛ ድንበር ላይ በማከማቸት ላይ እንደሆነችና የምድር ጥቃት ሊደረግ እንደሚችል እየተጠበቀ ይገኛል። የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይም ወደ " ጋዛ ለመግባት ዝግጅት ላይ ነን " ማለታቸው ተዘግቧል።

በጦርነቱ ሌሎች ኃይሎች እንዳይሳተፉበት ተሰግቷል ፣ የሊባኖሱ ሄዝቦላህ " አሜሪካ እስራኤል የምትፈፅመው ጥቃት አጋር ናት " ያለ ሲሆን ለሚፈፀመው ግድያ፣ ወንጀል እና ጋዛ ላይ ለተደረገው ከበባ ተጠናቂነት አለባት ብሏል።

#አሜሪካ እና አጋሮቿ የ " ሂዝቦላህ " የታጠቀ ኃይልን " ከእስራኤል ጋር ጦርነት ውስጥ ለመግባት አትሞክር አርፈህ ተቀመጠ " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

የየመኑ " ሁቲ ኃይል " አሜሪካ በቀጥታ ጦርነቱ ላይ ወታደራዊ ተሳትፎ ካደረገች ከወንድሞቻችን (ሃማስ) ጋር በመሆን ጦርነቱን እንቀላቀላለን በሚሳኤል እና ድሮን እንዲሁም በሌሎች አመራጮች የታገዘ ጥቃት እስራኤል ላይ እንከፍታለን ሲሉ ዝተዋል።

More 👉 @BirlikEthiopia

https://publielectoral.lat/+LM-bJ8NzZMcxMjA8
#አሜሪካ

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አንደኛ ዓመትን አስመልክተው መልዕክት አስተላልፈዋል።

አንቶኒ ብሊንከን ምን አሉ ?

- ብሊንከን በደፈናው #ኢትዮጵያ እና #ኤርትራ ጠብ ከሚያጭሩ ድርጊቶች እንዲቆጠቡና የአካባቢውን አገራት ነጻነት፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ማክበር አለባቸው ብለዋል።

- የኤርትራ ኃይሎች ከትግራይ ክልል ሙሉ ለሙሉ መውጣትን እንዳለባቸው ገልጸዋል።

- ስምምነቱን ተከትሎ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር መመሥረቱን ጨምሮ የተወሰዱ በጎ እርምጃዎችን አሜሪካ እንደምትደግፍ አሳውቀዋል።

- ህወሓት ኃይሎቹ ከባድ መሳሪያቸውን ፈትተው ተዋጊዎች ማሰናበት በተጀመረበት ጊዜ በትግራይ ውስጥ ዘላቂ ሰላም ለማስፍን ተጨማሪ እርምጃዎች መውሰድ ያስፈልጋል። ለዚህም የኤርትራ ኃይሎች ሙሉ ለሙሉ መውጣት አለባቸው ብለዋል።

- ብሊንከን አሜሪካ በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በሌሎችም አካባቢዎች ያሉት ግጭቶች እንደሚያሳስባት ገልጸዋል። ያለው ነገር  በቀላሉ ሊታወክ የሚችለውን የኢትዮጵያን ሰላም አደጋ ላይ እንደጣለው አመልክተዋል።

- በአገሪቱ በተለያዩ ወገኖች የቀጠለው የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እና ጥቃት፣ " የመርዛማ ንግግሮች " መስፋፋት በጦርነቱ ምክንያት የሳሳውን ማኅበራዊ ትስስር የበለጠ እየሸረሸረው መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ፦
🔹አስተማማኝ የሽግግር ፍትሕ፣
🔹ሐቀኛ እና አካታች ብሔራዊ ምክክር በመላዋ አገሪቱ ተግባራዊ እንዲሆን እንዲሁም በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች የሚካሄዱትን ግጭቶች ለመፍታት ውይይት እንዲደረግ አስቸኳይ ጥሪ አቅርበዋል።

#BBC
#SecretaryofStateAntonyJBlinken

@tikvahethiopia
#TOYOTA

ቶዮታ / Toyota ዓለም አቀፍ የመኪና አምራች ኩባንያ በዓለም ገበያ በዋነኝነት #በአሜሪካ የተሸጡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎቹን  ከገበያ ላይ እንዲሰበሰቡ አዟል።

ቶዮታ እንዲሰብሰቡ ያዘዘው ከ2020 እስከ 2022 ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ የተመረቱ ተሽከርካሪዎችን ሲሆን ተሽከርካሪዎቹ የ " ኤርባግ " ደህንነት ችግር አለባቸው ተብሏል።

ከ2020 እስከ 2022 ወደ ገበያ የቀረቡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎች (በዋነኝነት #አሜሪካ) ከ " ኤርባግ " ጋር በተያያዘ ችግር እንዳለባቸው ተደርሶበታል።

ችግሩ በፊት ለፊት ተሳፋሪ መቀመጫ በኩል በስህተት ከተሰራ የ " ኤርባግ ሴንሰር " ጋር የሚያያዝ ሲሆን ምናልባትም በአደጋ ጊዜ " ኤርባጉ " አገልግሎት ላይሰጥ ይችላል። ይህ አደጋ በሚፈጠር ጊዜ ኩዳቱ እንዲጨምር ያደርጋል።

ቶዮታ የትኞቹ ሞዴሎች ይሰብሰቡ አለ ?

#ቶዮታ

ኮሮላ (2020 - 2021)
ራቭ4 ፣ ራቭ4 ሃይብሪድ (2020 - 2021)
ሃይላንደር፣ ሃይላንደር ሃብሪድ (2020 - 2021)
አቫሎን ፣  አቫሎን ሃይብሪድ (2020 - 2021)
ካምሪ፣ ካምሪ ሃብሪድ (2020 - 2021)
ሴና ሀይብሪድ (2021)

#ሌክሰስ

ES250 (2021)
ES300H (2020-2022)
ES350 (2020-2021)
RX350 (2020-2021)
RX450H (2020-2021) የተሰኙ ከ2020 እስከ 2022 ላይ የተመረቱት የ " ኤርባግ " ችግር ስላለባቸው ይሰብሰቡ ብሏል።

ከላይ የተጠቀሱት ተሽከርካሪዎች ያላቸው ሰዎች ኤርባጋቸውን #እንዲያረጋግጡ እና ችግር ካጋጠማቸው እስከ ቀጣዩ የካቲት ወር ድረስ እንዲመልሱለት ቶዮታ ጥሪ አቅርቧል።

የቶዮታ ተሽከርካሪዎች ችግር እንዳለባቸው የታወቀው የጃፓን ትራንስፖርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ ተሽከርካሪ እምራች ኩባንያዎች ላይ ባደረገው #ምርመራ ላይ እንደሆነ ተገልጿል።

ይህን ተከትሎ የቶዮታ ኩባንያ አክስዮን ዋጋ ቅናሽ አሳይቷል።

ምርመራው ከቶዮታ ተሽከርካሪዎች በተጨማሪ ዳይሀትሱ በተሰኘው ኩባንያ ላይም ተመሳሳይ ችግር መታየቱን ገልጿል።

ከ87 ዓመት በፊት ኪቺሮ ቶዮታ በተባለ ግለሰብ የተመሰረተው ቶዮታ የተሽከርካሪ አምራች ኩባንያ አሁን ላይ በዓመት 10 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎችን በማምረት ላይ ይገኛል።

ከ360 ሺህ በላይ ሰራተኞች ያሉት ቶዮታ ኩባንያ 300 ቢሊዮን ዶላር የተጣራ ሀብት እንዳለው የኩባንያው ዓመታዊ ሪፖርት ያስረዳል።

#ጥቆማ ፦ ከደህንነት ጋር በተያይዘ በተለይም በአሜሪካ እንዲሰበሰቡ የታዘዙ ተሽከርካሪዎችን ቼክ ለማድረግ https://www.nhtsa.gov/recalls በዚህ አድራሻ መጠቀም ይቻላል። የመኪናውን መለያ ቁጥር (VIN) በማስገባት ማወቅ ይቻላል።

Credit - #AlAiN / #Reuters / #Toyota_News_Room

@tikvahethiopia
#አሜሪካ

" የዋሽንግተን አጠቃላይ የመሳሪያ ሽያጭ መጠን 238 ቢሊየን ዶላር ደርሷል " ተባለ።

አሜሪካ በፈረንጆቹ 2023 ከፍተኛ የጦር መሳሪያ ሽያጭ አስመዝግባለች።

" የዋሽንግተን አጠቃላይ የመሳሪያ ሽያጭ መጠን 238 ቢሊየን ዶላር ደርሷል " የተባለ ሲሆን፤  ይህም በ2022 ከነበረው የ50 በመቶ ብልጫ ማሳየቱ ተመላክቷል።

ለሽያጩ መጨመር የሩሲያ ዩክሬን #ጦርነት ከፍተኛ ድርሻ አለው የተባለ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ የአሜሪካ መከላከያ ኩባንያዎች ለውጭ ሀገራት በቀጥታ ያደረጉት ሽያጭ እንደሆነ ነው።

ፖላንድ የአሜሪካን የጦር መሳሪያ በመግዛት ቀዳሚ ሀገር እንደሆነች ለተቀናጀ የአየር እና የሚሳኤል መከላከያ የውጊያ ትዕዛዝ ስርዓትም 4 ቢሊየን ዶላር ማውጣቷ ተመላክቷል።

"አሜሪካ ለውጭ ያቀረበችው የጦር መሳሪያ ሽያጭ ባለፈው ዓመት በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል ሲል ፖለቲኮ ዘግቧል፡፡

ተጨማሪ መረጃዎችን በዚህ ይከታተሉ ፦ https://publielectoral.lat/+LM-bJ8NzZMcxMjA8

@ThiqaMediaEth
TIKVAH-ETHIOPIA
#PurposeBlack ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ምን አለ ? - የቢጂአይ ኢትዮጵያ የዋናው መሥሪያ ቤት ሽያጭ ውልን በውልና ማስረጃ በኩል ለመፈጸም ዝግጁ ነን። - ቢጂአይ ኢትዮጵያ የመንግስትን ግዴታ ቀድሞ ባለመወጣቱ በውል እና ማስረጃ መፈራረም አልተቻለም። ከታክስ ጋር በተያያዘ ክሊራንስ አልጨረሱም። - ቢጂአይ ብዙ ማሟላት ያለበትን ዶክመንት አላሟላም። በዚህ ምክንያት በውል እና ማስረጃ ለመፈራረም…
#PurposeBlack

የፐርፐርዝ ብላክ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አፈፃሚ ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ በአሁን ሰዓት #አሜሪካ ሀገር እንደሚገኙ ተነግሯል።

" አሜሪካ የሚገኙት ለስራ ነው " ያለው ድርጅቱ የፊታችን ሀሙስ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱና መግለጫም እንደሚሰጡ አመልክቷል።

ዛሬ መግለጫ ሰጥተው የነበረው የድርጅቱ የቦርድ አባል እና የህግ አማካሪ ዶ/ር ኤርሚያስ ብርሃኑ ናቸው።

ፐርፐዝ ብላክ ከቤቶቹ ግንባታ እና ከአክሲዮን ባለቤቶች ጋር በተያያዘ ምን አለ ?

- ለቤቶች ግንባታ ሌላም መሬት መግዛቱን ገልጿል።

- አሁን በገባው ቃል መሰረት ቤቶቹን በሚቀጥሉት 5 አመታት ሰርቶ እንደሚያስረክብ አመልክቷል። 

- " #ወሰን " አካባቢ ለቤቶች ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ተጥሏል ብሏል።

- የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያን አክሲዮኖች የገዙ ዜጎች ብራቸው #እንደማይመለስ ገልጿል። ነገር ግን ባለ አክሲዮኖች አክሲዮናቸውን መሸጥ ይችላሉ ብሏል።

- በአሁኑ ሰዓት ድርጅቱ ለ1 ሺ ባለ አክሲዮኖች የአክሲዮን ሽያጭ ካደረገ በኋላ የአክሲዮን ሽያጭ ማቆሙን ገልጿል።

- በተለዩ ቦታዎች መሬት እና ንብረትን ከግለሰቦች በመግዛት ፣ መሬት እና ንብረቱን አፍርሶ በመስራት እና ከባለሃብት ጋር አብሮ በማልማት በ3 አማራጮች ግንባታ ለመጀመር የሚጠቀማቸው አማራጮች መሆናቸውን አሳውቋል።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
#ኢራቅ

የኢራቅ ፓርላማ #ግብረሰዶም / የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን ከ10 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ እስር የሚቀጣ አዲስ ሕግ አርቅቋል።

በአዲሱ ሕግ መሠረት ጾታቸውን የቀየሩ ሰዎች ከ1 እስከ 3 ዓመት ሊታሰሩ ይችላሉ።

በአዲሱ ሕግ ፦

➡️ የግብረሰዶም / የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን የሚያበረታቱ፣ የሚያስተዋውቁ፤

➡️ ሴተኛ አዳሪነትን የሚያራምዱ፤

➡️ ጾታ ለመቀየር ቀዶ ህክምና የሚያደርጉ ዶክተሮችን፤

➡️ " ሆን ብለው " እንደ #ሴት የሚሆኑ ወንዶች እና " በሚስት መለዋወጥ " ላይ የተሠማሩ ሰዎች እስራት ይጠብቃቸዋል ፤ ዘብጥያም ይወርዳሉ።

የሕጉ ዓለማ ፥ " የኢራቅን ማህበረሰብ ከሞራል ዝቅጠትና ግብረ ሰዶማዊነት ከሚያደርሰው አደጋ ለመጠበቅ ነው " ተብሏል።

ረቂቁ መጀመሪያ ላይ ግብረሰዶማውያን #በሞት እንዲቀጡ የሚል የነበረው ቢሆንም በአሜሪካ እና በአውሮፓ ሀገራት ከፍተኛ ተቃውሞ መሻሻሉ ነው የተሰማው።

የኢራቅ ፓርላማ አባል የሆኑት አሚር አል-ማሙሪ ፥ " አዲሱ ሕግ #ኢስላማዊ እና ማህበረሰባዊ እሴቶችን የሚቃረኑ ልዩ ጉዳዮችን ለመዋጋት ትልቅ እርምጃ ነው " ብለዋል።

#አሜሪካ በውጭ ጉዳይ መ/ ቤቷ በኩል ሕጉን ፤ " ለሰብአዊ መብትና ነፃነት ጠንቅ ነው " በማለት ሕጉን ተቃውማለች።

" ሕጉ የኢራቅን ኢኮኖሚ የሚያቀዛቅዝ እና የውጭ ኢንቨስትመንትን የመሳብ አቅምን ያዳክማል" ብላለች።

የምዕራቡ ዓለም ሀገራት ሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችም ሕጉን ተቃውመዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመረጃው ምንጮች #ቢቢሲ እና #ሮይተርስ መሆናቸውን ይገልጸል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በኢራን የሂሊኮፕተር አደጋ የሞቱት እነማን ናችው ? - የኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ - የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሴን አሚር አብዶላሂያን - የተብሪዝ መስጂድ ኢማም አያቶላህ አልሃሸሚ - የምስራቅ አዘርባጃን ግዛት አስተዳዳሪ ማሊክ ራህማቲ - የፕሬዝዳንቱ ጥበቃ ኃላፊ ማሄዲ ሙሳቪ - የሄሊኮፕተሩ አብራሪ፣ - የሂሌኮፕተሩ ረዳት አብራሪ - ቦዲጋርድ - የበረራ አስተናጋጅ በትላንቱ የሂሊኮፕተር…
#ኢራን

" ...አሜሪካ በአቪየሽን ዘርፍ ላይ የጣለችው ማዕቀብ ለአደጋው መንስዔ ነው " - ሙሐመድ ጃቫር ዛሪፍ

የኢራን የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሃመድ ጃቫር ዛሪፍ ፣ የኢራን ፕሬዝዳንት እና ሌሎች ከፍተኛ የኢራን ባለስልጣናት ላይ ለደረሰው የሄሊኮፕተር አደጋ አሜሪካን ተጠያቂ አድርገዋል።

ሙሃመድ ጃቫር ዛሪፍ ፣ " #አሜሪካ በአቪየሽን ዘርፍ የጣለችው ማዕቀብ ለአደጋው መንስዔ ነው " ብለዋል፡፡

ከኢራን ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጋር ቆይታ ደረጉት ዛሪፍ ፣ " ማዕቀቡ ኢራን #አዳዲስ የአቪየሽን ምርቶችን መግዛት እንዳትችል አድርጓታል " ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ጥሩ የሚባል ግንኙነት እንደሌላት ይታወቃል።

ትላንት የኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ እና ሌሎች ባለልስጣናት ግድቦችን መርቀው ከከፈቱ በኋላ ወደ ታብሪዝ እያመሩ ሳሉ የነበሩበት ሂሊኮፕተር ከተራራ ጋር ተጋጭቶ ሁሉም ህይወታቸው አልፏል።

አደጋው በደረሰበት አካባቢ ላይ እጅግ አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ እንደነበርም ተገልጿል።

More ➡️ @thiqaheth
#አሜሪካ

ባለፈው ሳምንት በአሜሪካ ፤ በሉዊዚያና ግዛት ከታች አንስቶ እስከ ዩኒቨርሲቲ ባሉ በሁሉም የመማሪያ ክፍሎች ውስጥ አስርቱ ትዕዛዛት እንዲለጥፉ ታዟል።

ትላንት ደግሞ የኦክላሆማ ግዛት በአስቸኳይ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት እንዲጀመር አዟል።

የግዛቱ ትምህርት ቢሮ በግዛቱ ያሉ የሕዝብ ትምህርት ቤቶች መጽሐፍ ቅዱስን በትምህርት ስርዓታቸው በአስቸኳይ እንዲያካትቱና እንዲያስተምሩ መመሪያ አስትላልፏል።

በግዛቱ የትምህርት የበላይ ተቆጣጣሪ ሪያን ዋልተርስ የተላከ መመሪያ " አፋጣኝ እና ጥብቅ ተፈጻሚነትን " የሚፈልግ አስገዳጅ ድንብ ነው ይላል።

ዋልተርስ " መጽሐፍ ቅዱስ ታሪካዊና ባህላዊ መሠረት ነው "  ብለዋል።

" ያለ መጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ እውቀት የኦክላሆማ ተማሪዎች የአገራችንን መሠረት በትክክል መረዳት አይችሉም " በማለት ነው በአስቸኳይ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት እንዲሰጥ መታዘዙን ያመለከቱት።

በግዛቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ከ5ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ይተገበራል።

ከ5ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ እያንዳንዱ ክፍል መጽሐፍ ቅዱስ ሊኖረው ይገባል ተብሏል። ሁሉም አስተማሪዎች በክፍሉ ውስጥ ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ማስተማር እንዳለባቸው ታዟል።

የሲቪል መብት ተሟጋች ድርጅቶች ግን ይህንን ውሳኔ ተቃውመዋል።

ሃይማኖት እና መንግሥት መለያየት አለባቸው ብለዋል።

አንድ መንግሥትን ከሃይማኖት መለያየት እንዳለበት የሚሰራ ተቋም ፥ " የሕዝብ ትምህርት ቤቶች ሰንበት ትምህርት ቤቶች አይደሉም " ብሏል።

" ሪያን ዋልተርስ የተሰጠውን የመንግሥት ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም ሃይማኖታዊ እምነቱን በሌሎች ላይ ለመጫን እየተጠቀመበት ነው። ይህ እኛ ባለንበት ሊሳካ አይገባም " ብሏል ተቋሙ።

በአሜሪካ የሃይማኖት ነፃነትን ለማስጠበቅ የሚሰራው ኢንተርፌይዝ አሊያንስ ፤ " መመሪያው ግልጽ በሆነ መልኩ ሃይማኖትን መጫን ነው " ሲል ገልጾታል።

" እውነተኛ የእምነት ነፃነት ማለት የትኛውም የሃይማኖት ቡድን አመለካከቱን በሁሉም አሜሪካውያን ላይ እንዳይጭን መከላከል ነው " ብሏል።

#BBC #CNN

@tikvahethiopia