TIKVAH-ETHIOPIA
#PurposeBlack ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ምን አለ ? - የቢጂአይ ኢትዮጵያ የዋናው መሥሪያ ቤት ሽያጭ ውልን በውልና ማስረጃ በኩል ለመፈጸም ዝግጁ ነን። - ቢጂአይ ኢትዮጵያ የመንግስትን ግዴታ ቀድሞ ባለመወጣቱ በውል እና ማስረጃ መፈራረም አልተቻለም። ከታክስ ጋር በተያያዘ ክሊራንስ አልጨረሱም። - ቢጂአይ ብዙ ማሟላት ያለበትን ዶክመንት አላሟላም። በዚህ ምክንያት በውል እና ማስረጃ ለመፈራረም…
#PurposeBlack

የፐርፐርዝ ብላክ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አፈፃሚ ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ በአሁን ሰዓት #አሜሪካ ሀገር እንደሚገኙ ተነግሯል።

" አሜሪካ የሚገኙት ለስራ ነው " ያለው ድርጅቱ የፊታችን ሀሙስ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱና መግለጫም እንደሚሰጡ አመልክቷል።

ዛሬ መግለጫ ሰጥተው የነበረው የድርጅቱ የቦርድ አባል እና የህግ አማካሪ ዶ/ር ኤርሚያስ ብርሃኑ ናቸው።

ፐርፐዝ ብላክ ከቤቶቹ ግንባታ እና ከአክሲዮን ባለቤቶች ጋር በተያያዘ ምን አለ ?

- ለቤቶች ግንባታ ሌላም መሬት መግዛቱን ገልጿል።

- አሁን በገባው ቃል መሰረት ቤቶቹን በሚቀጥሉት 5 አመታት ሰርቶ እንደሚያስረክብ አመልክቷል። 

- " #ወሰን " አካባቢ ለቤቶች ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ተጥሏል ብሏል።

- የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያን አክሲዮኖች የገዙ ዜጎች ብራቸው #እንደማይመለስ ገልጿል። ነገር ግን ባለ አክሲዮኖች አክሲዮናቸውን መሸጥ ይችላሉ ብሏል።

- በአሁኑ ሰዓት ድርጅቱ ለ1 ሺ ባለ አክሲዮኖች የአክሲዮን ሽያጭ ካደረገ በኋላ የአክሲዮን ሽያጭ ማቆሙን ገልጿል።

- በተለዩ ቦታዎች መሬት እና ንብረትን ከግለሰቦች በመግዛት ፣ መሬት እና ንብረቱን አፍርሶ በመስራት እና ከባለሃብት ጋር አብሮ በማልማት በ3 አማራጮች ግንባታ ለመጀመር የሚጠቀማቸው አማራጮች መሆናቸውን አሳውቋል።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia