TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጥቆማ

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ( #INSA ) የ2016 ዓ/ም " National Cyber Talent Challenge Program " ማዘጋጀቱን ገልጿል።

በሳይበር ደህንነትና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ እና ፍላጎት ያላቸው በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ወጣቶች በሙሉ በዚህ ቻሌንጅ ላይ መሳተፍ ይችላሉ ተብሏል።

የታለንት መስኮች፦

- Cyber Security
- Cyber Development
- Embedded Systems
- Aerospace ናቸው።

ስልጠናው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለአንድ ወር ይሰጣል።

አመልካቾች በዌብሳይት  https://talent.Insa.gov.et በመግባት ከዛሬ ጀምሮ እስከ ግንቦት 30/ 2016 ዓ/ም መመዝገብ እንደሚችሉ ተገልጿል።

ለበለጠ መረጃ ደግሞ +251904311833 ፣ +251943579970፣ +251904311837 ላይ ስልክ መደወል ይችላል።

@Tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥቆማ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ( #INSA ) የ2016 ዓ/ም " National Cyber Talent Challenge Program " ማዘጋጀቱን ገልጿል። በሳይበር ደህንነትና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ እና ፍላጎት ያላቸው በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ወጣቶች በሙሉ በዚህ ቻሌንጅ ላይ መሳተፍ ይችላሉ ተብሏል። የታለንት መስኮች፦ - Cyber Security …
#INSA #ጥቆማ

የብሔራዊ የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ምዝገባ መካሄድ ጀምሯል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በ2014 ዓ/ም እና በ2015 ዓ/ም ለሁለት ተከታታይ አመታት በሳይበር ደህንነት እና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ታዳጊ ወጣቶች በክረምት ፕሮግራም (Summer Program) አሰልጥኖ ማስመረቁን ገልጿል።

ተመራቂዎችንም ፦

° #እንደየችሎታቸው እና #እንደስራዎቻቸው ከተለያዩ ባለሀብቶች ጋር የማስተሳሰር፤

° ኢመደአን (INSA) ጨምሮ በተለያዩ ተቋማት #ተቀጥረው መስራት የሚችሉበት ሁኔታ እንዳመቻቸ አመልክቷል።

ባለፉት ሁለት አመታት የተከናወኑ የሳይበር ታለንት ልማት ፕሮግራሞችን መነሻ በማድረግ በ2016 በጀት አመት “ብሄራዊ የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ” ፕሮግራም መዘጋጀቱ ተገልጿል።

የዚህ ቻሌንጅ ዋና ዓላማ በሳይበር ደህንነት እና ተያያዥ መስኮች ልዩ ተሰጥዖ ያላቸዉን ሰዎች በመመልመል በዘርፉ ላይ ተጨባጭ ተጽዕኖ መፍጠር የሚችል ብሄራዊ የሳይበር ሰራዊት (National Cyber Army) መገንባት ነው ተብሏል።

በሳይበር ደህንነት እና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ እና ፍላጎት ያላቸው እና እድሜያቸው ከ11 አመት ጀምሮ ያሉ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በዚህ ቻሌንጅ ላይ መሳተፍ ይችላሉ ተብሏል።

መመዝገቢያ ጊዜ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ግንቦት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ነው።

መመዝገቢያ አድራሻው https://talent.insa.gov.et ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#USA #kenya

የጎረቤታችን ሀገር ኬንያን ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶን ተቀብለው እያስተናገዱ ያሉት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ኬንያን ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል የመጀመሪያዋ #የNATO_አባል_ያልሆነች (non-NATO) ዋና አጋር ሀገር እንደምታደርጋት ቃል መግባታቸው ተነግሯል።

@tikvahethiopia
#Ethiotelecom

iPhone 15 Pro Max is now available, offering you the ultimate smartphone experience!

Prepare to be fully immersed in a realm of advanced technology and unparalleled convenience.

Choose from an amazing selection of packages to get everything you need.

📱 iPhone 15 Pro Max +
🔌 Charger Head
🌐 100/50 GB Mobile Data and
🎧 AirPods 3rd Generation

You can get the devices from our premium business centers, Churchill avenue next to Lycée Gebre Mariam School.

#iPhone15ProMax
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
#ADHD

የስዊድን መንግሥት ፦
° ጥንቃቄ የጎደለው ትኩረት የማጣት፣
° ከፍተኛ የመቅበጥበጥ፣ 
° ብዙ የማውራት፣
° ግትርነት
° እራስን የመግዛት ቀውስ (ADHD -attention deficit hyperactivity disorder) ችግር በብዛት የሚታይባቸው ልጆች በሀገሪቱ ቁጥራቸው መጨመሩን ዛሬ አስታወቀ።

የሀገሪቱ የማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው ቃል የስዊድን የጤና እና ደህንነት ቦርድ መረጃ ADHD ተብሎ የሚገለጸው #የአእምሮ_ጤና_ችግር እ.ኤ.አ. ከ2022 ጀምሮ 10 በመቶ በሚሆኑ ወንዶች ልጆች ላይ እንዲሁም 6 በመቶ በሚሆኑት አዳጊ ሴት ልጆች ላይ በምርመራ መታየቱን ይፋ አድርጓል።

የችግሩ ተጋላጭ ልጆች ቁጥር ሊጨምርም ይችላል ተብሏል።

በመላው ዓለምም ከ5 እስከ 7 በመቶ የሚሆኑ ልጆች ለዚህ ችግር የተጋለጡ ናቸው።

ለዚህ ችግር የሚያጋልጡ ምክንያቶች ፦
- የተለያዩ እንደ ሊድ ወይም እርሳስ ባሉ ማዕድናት የተበከለ አካባቢ መኖር፣
- በእርግዝና ወቅት መድኃኒቶች፣ አልኮል ወይም ሲጋራ / ትንባሆ ማጨስ ማዘውተር ሊሆኑ እንደሚችሉ ይገመታል።

ከዚህም በተጨማሪ በደም አማካኝነት በዘር የአእምሮ ህመሞችም ሊተላለፉ እንደሚችሉ ነው የተገለጸው።

ይህ የአእምሮ ችግር (ADHD) ያለባቸው ልጆች ቁጥር ለምን እንደጨመረ መንስኤውን ለማወቅ ጥናቶች እየተካሄዱ ነው።

#DeutscheWelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥንቃቄ🚨 " በተጣሉ ተተኳሾች እና ፈንጂዎች 103 ሰዎች #ሞተዋል ፤ አካላቸው ጎድሏል " - የቆላ ተምቤን ወረዳ በትግራይ ማእከላይ ዞን የቆላ ተምቤን ወረዳ በጦርነቱ ምክንያት በርካታ ተተካሾች እና ፍንጂዎች ይገኛሉ። እጅግ አስከፊውና ደም አፋሳሹን ጦርነት ተከትሎ በአከባቢው የተቀበሩትና የተጣሉት ተተካሾችና ፈንጂዎች በበርካታ ሰዎችና እንስሳት ላይ የሞትና የአካል ጉዳት አደጋ በማድረስ ላይ እንደሆኑ…
#Tigray

በትግራዩ ጦርነት ምክንያት በየቦታው የተቀበሩ እና የተጣሉ ተተኳሾች፣ ፈንጂዎች አሁንም በሰው ህይወት ላይ አደጋ ማድረሳቸው ቀጥሏል።

ዛሬ ዓርብ ግንቦት 16 / 2016 በተጣለ ተተኳሽ ባል እና ሚስት ህይወታቸው አልፏል።

አደጋው ያጋጠመው በትግራይ ክልል ፣ በማእከላዊ ዞን ቆላ ተምቤን ምረረ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ሲሆን በተተኳሹ ምክንያት የባል ህይወት ወድያው አልፏል።

የሟች ሚስት ወደ ሆስፒታል ብትወሰድም ህይወቷን ማዳን አልተቻለም።

የቆላ ተምቤን ወረዳ በአስከፊው እና በደም አፋሳሹ የትግራይ ጦርነት በርካታ ውግያ ያስተናገደ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በአከባቢው ላይ የተቀበሩና የተጣሉ ተተኳሾችና ፈንጂዎች የማፅዳ ጉዳይ ትኩረት ይሻል ብለዋል የአከባቢው ነዋሪዎች።

ከፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በኋላ በቆላ ተምቤን ወረዳ ብቻ በተጣሉ ተተኳሾችና  ፈንጂዎች 103 ሰዎች ላይ የሞት የአካል መጉደል አደጋ መድረሱ በሚያዝያ ወር 2016 ዓ/ም የመጨረሻ ሳምንት ላይ መዘገባችን ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
                                       
@tikvahethiopia            
የአሜሪካ ኤምባሲ ሁለት ቀን ተዘግቶ ይውላል።

በአዲስ አበባ የሚገኘው የኤሜሪካ ኤምባሲ ሰኞ እና ማክሰኞ ዝግ ሆኖ እንደሚውል አስታውቋል።

ኤምባሲው ፥ ሰኞ ግንቦት 19/2016 ' ሚሞሪያል ዴይ 'ን ወይም በግዳጅ ላይ የተሰዉ የአሜሪካ አርበኞች መታሰቢያ በዓልን ምክንያት በማድረግ እንደሚዘጋ አመልክቷል።

በነጋተው ማክሰኞ ግንቦት 20 የ #ደረግ_መንግሥት የወደቀበትን ቀን ምክንያት በማድረግ ሙሉ ቀን ተዘግቶ እንደሚውል ገልጿል።

ኤምባሲው ዳግም የሚከፈተው #ረቡዕ_ግንቦት_21 መሆኑን አሳውቋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Tecno #Camon30Pro5G

Tecno Camon 30 pro 5G እያንዳንዱ ፎቶ እና ቪድዮ ከፍተኛ ጥራት እንዲላበሱ የSony IMX890 ካሜራ ሴንሰር ገጥሞ ቀርቧል!

#Camon30Et #Camon30Pro5GEt #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
#ሰከላ

" ባለፈው ሳምንት ውስጥ ብቻ 47 ሰዎች ናቸው የተገደሉት " - ነዋሪዎች

" በተጨባጭ የሞተ አንድም ሲቪል የለም። ይህ ነው ትክክለኛው እውነት " - የኮማንድ ፖስት ምክትል ሰብሰቢ

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ላይ ግንቦት 4 ቀን 2016 ዓ/ም በ " ፋኖ " እና በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች መካከል የተኩስ ልውውጥ እንደነበር ፣ ከዚያ በኋላ ባሉት ቀናት " በጸጥታ ኃይሎች " ንጹሐን መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ቃላቸውም የሰጡ ነዋሪዎች ምን አሉ ?

° #ሰርገኞች ሳይቀሩ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ተገድለዋል። ሰርግ ላይ የነበሩ የሙሽራው ወንድም፣ አጃቢዎች ሰኞ ግንቦት 5 ቀን 2016 ዓ/ም መንገድ ላይ ተረሽነዋል።

° ሴቶች ተገድለዋል።

° 3 ካህናት ከቤተክርስቲያን እየተመለሱ በነበረበት ወቅት ተገድለዋል።

° ባለፈው ሳምንት ብቻ 47 ሰዎች ናቸው የተገደሉት።

° እውነት የተናገሩ ሰዎች ተጨፍጭፈዋል።

° ግንቦት 15/2016 ዓ/ም ከሰከላ 4 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ቦታ 6 ሰዓት የተጀመረ ተኩስ እስከ ምሽቱ 12 ቆይቷል።

° ተራው ህዝብ ወደ ገጠራማው አካባቢ፣ ባለሃብቶች ወደ ባሕር ዳር ከተማ ለመፈናቀል  ተገደዋል።

አንድ አሽከርካሪ አባትም ልጃቸው ሱቅ ብሎ እንደወጣ እንደተገደለባቸው በሀዘን ስሜት ሆነው ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ተኩስ ያለው ሰሞኑን ብቻ ነው ከዚህ በፊትም ነበር ?  ተብሎ ጥያቄ የቀረበላቸው ነዋሪዎች ፣  የካቲት 20 ቀን 2016 ዓ/ም ነበር። ከየካቲት 2016 ዓ/ም ጀምሮ በሰከላ ብቻ 107 ሰዎች ተገድለዋል " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ሰላም እንዲያሰፍንላቸው የጠየቁ ሲሆን  " ሰላም ይውረድልን ግጭት በመጣ ቁጥር እየሞተ ያለው ንጹሃን እንጂ የታጠቀ ኃይል አይደለም " ብለዋል።

የምዕራብ ጎጃም ኮማንድ ፖስት ምክትል ሰብሳቢ እና የዞን ዋና አስተዳዳሪ እድሜአለም አንተነህ ከሰሞኑን ለ ' አሻም ቴሌቪዥን ' በሰጡት ቃል ፥ " አንድም ንጹሃን አልተገደለም " ብለዋል።

ዋና አስተዳዳሪው ምን አሉ ?

- ከሳምንት በፊት ሰከላ ላይ ሌሎች ቦታዎች አልፎ አልፎ እንደሚደረገው ግጭት ነበር። ግጭት የነበረው ከከተማው 18 ኪሎ ሜትር ቦታ ላይ ነበር። ግጭቱ የነበረው በታጠቁ ኃይሎች እና በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች መካከል ነው። ሁለቱም መሳሪያ የያዙ ናቸው።

- እዛ የነበረውን ክፍተት መነሻ አድርጎ ሌላው የታጠቀ ኃይል እኛ ' ፅንፈኛው ኃይል ' የምንለው  ሾልኮ ገብቶ ባንኮችን እና የግለሰብ ድርጅቶች ላይ ከፍተኛ ዝርፊያ ነው የፈጸመው። በቦታው ላይ በሁኔታው ላይ የተሳተፈ በተጨባጭ የሞተ አንድም ሲቪል የለም።

- በተጨባጭ የሞተ አንድም ሲቪል የለም። ይህ ነው ትክክለኛው እውነት።

- ሲቪሊያን ሰዎች የሚኖሩበት አካባቢ ላይ ግጭት መተንኮስ አግባብ አይደለም። የተፈናቀለ ሰው የለም፣ የወጣ ሲቪልም የለም። በግጭቱ የተሳተፈ ሲቪል የለም። ከተማው ላይ ያችግር ሲፈጠር ሰዎች ቤታቸው ውስጥ ነበሩ።

- አሁን የገጠሩ ህዝብ ዘር እየዘራ ነው። የአካባቢው ኑሮም መደበኛው ነው። የተፈናቀለም የለም፤ እንደዛ የሚባል ስጋት የለም።

በሰከላ ተፈጸሟል የተባለውን ግድያ ሰምቶ እንደሆን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበለት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ፣ ሰሞኑን በአማራ ክልል ስላለው ጥቃት ሪፓርት ይፋ እንደሚያደርግ፣ የሰከላውም በዚሁ ሪፖርት ውስጥ ተካቶ ሊሆን እንደሚችል ገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Tigray

" በአላማጣ ዙሪያ የነበረው ኃይል አከባቢውን ለቆ ወጥቷል " - የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ትላንትና ከምሸቱ 4:00 ባወጣው መግለጫ ፥ " በአላማጣ በቅሎ ማነቂያና ገርጃለ የነበረው #የተወስነ የትግራይ ተዋጊ ኃይል አከባቢውን ለቆ ወጥቷል " ብሏል።

የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነትን በማስመልከት በአዲስ አበባ በወጣው የአተገባበር ኦፕሬሽን ፕላን መሰረት በማድረግ ተዋጊ ኃይሉ አከባቢውን እንዲለቅ መደረጉን ገልጿል።

ለአላማጣ ህዝብ ደህንነት ተብሎ የተወሰነ ተዋጊ ኃይሉ ከቦታው ለቆ ቀድሞ ወደ ነበረበት ቦታ መመለሱን አመልክቷል።

የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንትም አቶ ጌታቸው ረዳም ይህኑን አረጋግጠዋል።

አቶ ጌታቸው ራዳ ፤ " የፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት ትግበራ አካል ሆኖ የትግራይ ተፈናቃዮች በቀላሉ ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ ከፌዴራል መንግስት እና ከአማራ አስተዳደር ጋር ያለውን መግባባት ለማክበር በአላማጣ አቅራቢያ ከሚገኙት ገርጀለ እና በቅሎማናቂያ አካባቢዎች የትግራይ ሃይሎች እንዲወጡ ተወስኗል " ብለዋል።

ተጨማሪ የትግራይ ተፈናቃዮችን ለመመለስ ተመሳሳይ አይነት እርምጃ ለመውሰድ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

የጊዚያዊ አስተዳደሩ ም/ፕሬዝዳንት ሌ/ ጀነራል ታደሰ ወረደ ባለፈው እሁድ በሰጡት መግለጫ የትግራይ አስተዳደር ወደ አላማጣ እንደሚገባና በአከባቢው  የሚገኘው የትግራይ ታጣቂ ኃይል ይወጣል በማለት ተናግረው ነበር።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
                                       
@tikvahethiopia            
159_በመንደር_የንግድ_ቁጥጥር_የአሠራር_ሥርዓት_መመሪያ_ቁጥር_159_2016.pdf
436.8 KB
#AddisAbaba

አዲሱን " በመንደር ንግድ ቁጥጥር አሰራር ስርዓት መመሪያ 159/2016 " የተያያዘውን ፋይል ከፍተው በዝርዝር ያንብቡ።

#አዲስ_አበባ_ንግድ_ቢሮ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
159_በመንደር_የንግድ_ቁጥጥር_የአሠራር_ሥርዓት_መመሪያ_ቁጥር_159_2016.pdf
#AddisAbaba #ንግድ

የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ማህበረሰብ ያለወከባ በተረጋጋ መንፈስ የንግድ ተግባሩን ለማከናወን እንዲያስችል ዕድል ይፈጥርለታል የተባለ አዲስ መመሪያ ስራ ላይ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል።

አዲሱ መመሪያ  " በመንደር ንግድ ቁጥጥር አሰራር ስርዓት መመሪያ 159/2016 " እንደሚባል ከአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

መመሪያው በየትኛው አስተዳደር እርከን የትኛው አይነት እርምጃ እንደሚወሰድ በግልጽ ያስቀመጠ ሲሆን ይህም ሲታይ የነበረውን ግልጽ እና ፍትሃዊ ያልሆነ አሰራር ያስቀራል ተብሏል።

በአዲሱ የመንደር ንግድ መመሪያ መሰረት የወረዳ የንግድ ቁጥጥር ባለሙያ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወስድ ህጉ የሚፈቅድለት በተመደበበት መንደር ላይ ፦
ያለ ንግድ ፍቃድ
ባልታደሰ ፍቃድ
በታገደ አልያም በተሰረዘ ንግድ ፈቃድ የሚነግድ የንግድ ድርጅት ላይ #ብቻ_ነው። ይህን ሲያደርግም ለቅርብ ኃላፊ ማሳወቅ አለበት።

ከዚህ ወጪ ያሉት ጥፋቶች #በሙሉ እርምጃ ሳይወስድ ለቅርብ ኃላፊው በፅሁፍ በማሳወቅ ለውሳኔ ወደ ንግድ ቢሮ መላክ ይጠበቅበታል ፤ የተወሰነውን ውሳኔ የማስፈፀም ኃላፊነትም አለበት።

መመሪያው ፦ https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/87886

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ብሔራዊ_ፈተና

" በበይነ መረብ የሳይበር ጥቃት በመፈጸም ፈተናውን ለመስረቅ ጥረት አያደርጉም ብለን እንጠብቅም ፤ ያንን ለመከላከል ዝግጅት ተደርጓል  " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

በበይነ መረብ / #በኦንላይን የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሳይበር ጥቃት እንዳይሰረቅ ዝግጅት መደረጉን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር እሸቱ ከበደ ለኢቢሲ በሰጡት ቃል ፤ " በዚህ ዓለም ምንም አይነት ችግር የሌለበት ነገር የለም። ሁሉም ነገር የራሱ የሆነ ችግር / ጉድለት ይኖረዋል ያለን ምርጫች ግን ችግሩን የመከላከል አቅም ጎን ለጎን መገንባት ነው " ብለዋል።

" በበይነ መረብ የሳይበር ጥቃት በመፈጸም ፈተናውን ለመስረቅ ጥረት አያደርጉም ብለን እንጠብቅም " ያሉት ዋና ዳይሬክቲ ፥ " የሳይበር ደህንነት (ሴክዩሪቲ) ስራዎች ፦
° ሞያው ባላቸው ፣
° መሳሪያዎች ባሏቸው
° አቅም ባላቸው ተቋማት በኩል ተገቢ የሆነ ዝግጅት አድርገን እየሰራን ነው " ሲሉ አሳውቀዋል።

" በማህበራዊ ሚዲያ ስለ ፈተናው ብዥታ ለመፍጠር የሚፈልጉ ፣ ፈተናው ላይ ጥቃት ለመፍጠር የሚያስቡ አካላት ማወቅ ያለባቸው ይሄ #የፖለቲካ#የሃይማኖት ጉዳይ አይደለም ማንም ወላጅ ልጁን አስተምሮ የሚያደርስበት ስለሆነ ሁለት ሶስቴ ማሰብ አለባቸው ፤ ተማሪዎቹ ነገ ለሀገር እዳ እንዳይሆኑ ማሰብ ይገባል " ሲሉ አሳስበዋል።

ከኦንላይን ፈተናው ጋር በተያያዘ ማንም አካል ወላጆችን " ኮምፒዩተር አቅርቡ " አላለም ፤ ሊጠየቁም አይገባም ከተጠየቅም ስህተት ነው ተብሏል።

ፈተና የሚሰጠው መንግሥት በሚያቀርበው አቅርቦት / ኮምፒየተር እንደሆነ ተመላክቷል።

ይህ ማለት የኮምፒዩተር አቅም ኖሯቸው ት/ቤታቸውን ማገዝ የሚፈልጉ ዜጎችን አይችሉም ማለት አይደለም ተብሏል።

የወረቅት ፈተናን በተመለከተ አሁን ላይ ህትመት ወደ መጠናቀቁ ሲሆን ፈተናው ልክ እንዳለፉት ፈተናዎች ደህንነቱ እንዲጠበቅ በቂ ዝግጅት መደረጉ፣ በክፍል ውስጥም ኩረጃ እንዳይኖርና ተማሪዎች በራሳቸውን ሰርተው እንዲያልፉ ካለፈው #በጠነከረ ሁኔታ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግ ተገልጿል።

#Ethiopia
#NationalExam
#Grade12

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ለ Big 5 ኮንስትራክት ኢትዮጵያ ይዘጋጁ! በሃገሪቱ ግንባታ ዘርፍ ትልቁ ዝግጅት፤ ከግንቦት 22 እስከ ግንቦት 24፣ 2016 በሚሊኒየም አዳራሽ ይዘጋጃል።

- ከ 150 በላይ ከሚሆኑ ተሳታፊዎች የሚቀርቡ አዳዲስ ምርቶችንና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ይጎብኙ!

- ከ 15 በላይ ሃገራት ከሚመጡ ተሳታፊዎች ጋር ይገናኙ!

- በግንባታው ዘርፍ ከበቁ 9000 ባለሙያዎች ጋር ትስስር ይፍጠሩ!

- ከ 20 በላይ በሚሆኑ፣ በዋጋ በማይተመኑ መረጃ ሰጪ መድረኮች ላይ የመሳተፍና የ Continuous professional development ነጥብዎን የማሳደግ ዕድሉን ያግኙ!

በሁነቱ ላይ ልናገኝዎ በጉጉት እንጠብቃልን !

በነጻ ለመጎብኘት አሁኑኑ ይመዝገቡ 👇 https://bit.ly/3UsrL5I
TIKVAH-ETHIOPIA
#Axum የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰኔ 2016 ዓ/ም ወደ ትግራይ አክሱም ከተማ በረራ እንደሚጀመር መግለጹን ትግራይ ቴሌቪዥን ዘግቧል። የአክሱም ሃፀይ ዮውሃንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፍያ በትግራይ በነበረው ደም አፋሳሽ ጦርነት በደረሰበት ወድመት ምክንያት ከበረራ አገልግሎት ውጪ ሆኖ መቆየቱ ይታወሳል። በቅርቡ ግን አውሮፕላን ማረፊያው መልሶ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር የኢትዮጵያ አየር መንገድ…
#Ethiopia

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጪው #ሰኔ_ወር 2016 ዓ/ም ወደ ሁለት የሀገር ውስጥ የበረራ መዳረሻዎች በረራ ይጀምራል።

አየር መንገዱ #ከሰኔ_10_ጀምሮ ወደ ወለጋ ፣ ነቀምቴ በረራ እንደሚጀምር አሳውቋል።

በረራው በሳምንት 4 ጊዜ እንደሚካሄድ ተገልጿል።

ከዚህም ባለፈ ፥ በትግራይ ጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየው ወደ አክሱም የሚደረገው በረራ ከሰኔ 1 ጀምሮ ዳግም እንደሚጀምር ታውቋል።

የአክሱም ሃፀይ ዮውሃንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፍያ በጦርነቱ በደረሰበት የከፋ ወድመት ምክንያት ከበረራ አገልግሎት ውጪ ሆኖ መቆየቱ ይታወሳል።

ከሰኔ 1 ጀምሮ ግን የመንገደኞች በረራ ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል።

#Ethiopia #OromiaRegion #TigrayRegion #Wollega #Axum
 
@tikvahethiopia
#Tecno #Camon30Pro5G

ልዩ ዲዛይን እና ቴክኖሎጂ አጣምሮ የቀረበዉ Tecno Camon30 Pro 5G ምርጫዎ ያድርጉ!

#Camon30Et #Camon30Pro5GEt #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt