TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የሰላም_ዋጋው_ውድ_ነው!!!
#የሰላም_ዋጋው_ውድ_ነው!!!
#የሰላም_ዋጋው_ውድ_ነው!!!

ይህ ተረት ተረት አይደለም!

በሩዋንዳ በ100 ቀናት ብቻ 800,000 የሩዋንዳ ዜጎች በዘር ግጭት ሳቢያ ሙተዋል!!

#ሩዋንዳ_ምሳሌ_ትሁነን!!

ዘረኝነት እና የዘረኝነት ቅስቀሳዎች ያስከተሉትን ጉዳት ለመረዳት ከጉረቤታችን ሩዋንዳ በቀላሉ ልንማር እንችላለን!!

በሁቱና ቱትሲ ዘሮች ብቻ ዘርን ማዕከል ተደርጎ ፅንፈኛ #ሚዲያዎች በሰሩት #ግደለው #አቃጥለው #አውድመው የተሰኘ ቅስቀሳ በ100 ቀናት ብቻ ለማመን በሚከብድ ሁናቴ 800,000 የሩዋንዳ ዜጎች በአሰቃቂ ሁኔታ ሂወታቸውን አጠዋል፡፡

እኛ ከሩዋንዳ ምን እንማር?

በሩዋንዳ የሆነው ተረት ተረት አይደለም ዛሬ ከታሪካቸው የተማሩበት ከባድ ጠባሳ እንጂ አሁን እኛ ጋር የምናየው የዘረኝነት #እብደት ሩዋንዳም ያኔ ሲጀማምራቸው የገጠማቸው ችግር ነው፡፡

ዛሬ ሀላፊነት በጎደለው መንገድ የምትተኮስ #የጥላቻ ጥይት ጥላቻውን በስሜት ለሚተኩሳት የጥፊት ሀይልም የምትዳረስ ናት፡፡

እናማ በዚህም አልን በዚያ ሩዋንዳ ምሳሌ ትሁነን!!
#ሰላም ሰላም ሰላም ሁሌም ለሰላም ቅድሚያ እንስጥ!!

#ሞገደኛው_ብዕር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከዘር ማጥፋት እልቂት ለማምለጥ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተሸሸጉ 2 ሺህ ቱትሲዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ በመስጠት የተጠረጠረው ግለሰብ ተያዘ።

እ.አ.አ በ1994 በሩዋንዳ በነበረው የዘር ማጥፋት እልቂት፣ ከጥቃት ለማምለጥ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተሸሸጉ ሁለት ሺሕ #ቱትሲዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፏል በሚል የተጠረጠረው ግለሰብ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ መያዙን የሩዋንዳውን የዘር ማጥፋት የሚከታተለው፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጦር ወንጀል ችሎት አስታውቋል።

የቀድሞው የፖሊስ አባል፣ ፉልጌንሴ ካይሼማ፣ ፍ/ቤቱ በይፋ ክሥ ከመሠረተበት ካለፉት 22 ዓመታት ጀምሮ በሽሽት ላይ ነበር።

በተመድ የተቋቋመው ችሎት፣ ሥራውን ለሩዋንዳ በማስረከቡ፣ ካይሼማ፥ ለሩዋንዳ ተላልፎ እንደሚሰጥ የሮይተርስ ዘገባ አመልክቷል።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ካይሼማ ያለበትን ለሚጠቁም፣ የአምስት ሚሊዮን ዶላር ጉርሻ እንደሚሰጥ አስታውቆ ነበር።

ሌላው የዘር ማጥፋቱ ጠንሳሽ የተባለው ፌሊሲን ካቡጋ፣ ከ26 ዓመታት ሽሽት በኋላ ከሦስት ዓመት በፊት በፈረንሳይ ውስጥ መያዙ ይታወቃል።

እ.አ.አ በ1994 በሩዋንዳ፣ በአክራሪ ሁቱዎች በተፈጸመ የዘር ማጥፋት፣ 800ሺሕ የሚሆኑ ቱትሲዎች መገደላቸው ይታወሳል።

#ቪኦኤ #ሩዋንዳ #Genocide

@tikvahethiopia
#UK

" ማንም ሰው ወደ #ሩዋንዳ ለመሄድ 3 ሺህ ፓውንድ ለማግኘት ብቻ ወደዚህ ለመምጣት የሚሞክር አይመስለኝም " - የገንዘብ ሚኒስትር ኬቨን ሆሊንራክ

ዩናይትድ ኪንግደም  (ዩኬ) በአገሯ የጥገኝነት ጥያቄያቸው ተቀባይነት ያላገኙ ስደተኞችን እስከ 3 ሺህ ፓውንድ በመክፈል ወደ ሩዋንዳ ልትልክ መሆኑን እንዳስታወቀች ቢቢሲ ዘግቧል።

ይህ አዲስ የስደተኞች ዕቅድ የጥገኝነት ጥያቄያቸው ያልተሳካላቸው ስደተኞች በበጎ ፈቃደኝነት ወደ አገራቸው እንዲመለሱና ለዚህም የሚሆን ገንዘብ ይሰጣቸዋል ተብሏል።

የጥገኝነት ጥያቄያቸው በዩናይትድ ኪንግደም ውድቅ ለተደረገባቸው ለማንኛውም ስደተኞች ክፍት ይሆናል ተብሏል።

ይህ ዕቅድ በተለይም ወደ አገራቸው መመለስ በማይችሉ ስደተኞች ላይ ያነጣጠረ ነው።

የዩናትድ ኪንግደም የገንዘብ ሚኒስትር ኬቨን ሆሊንራክ ምን አሉ ?

- ወደ ሩዋንዳ ለመሄድ ለተስማሙ ስደተኞች የሚከፈለው ክፍያ የህዝብን ገንዘብ በአግባቡ መጠቀም ይሆናል።

- እነዚህን ሰዎች ያለ ምንም ጥቅም እዚህ ማቆየት ከዚያ የበለጠ ገንዘብ ያስወጣናል።

- " እዚህ በህገወጥ መንገድ ከመጣችሁ በዚህች አገር መቆየት አትችሉም " የሚለውን መልዕክት ያስተላልፋል። መሰረታዊ ነጥብ ይህ ነው።

- ማንም ሰው ወደ ሩዋንዳ ለመሄድ 3 ሺህ ፓውንድ ለማግኘት ብቻ ወደዚህ ለመምጣት የሚሞክር አይመስለኝም።

የዩናይትድ ኪንግደም መንግሥት " በህገወጥ መንገድ ገብተዋል " የተባሉ ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ ተልከው ጥያቄያቸው ከዚያ የሚታይበትን የተለየ እቅድም ለመተግበር መንግሥት እየሞከረ ይገኛል ተብሏል።

ይህ እቅድ ከሩዋንዳ የደህንንት ስጋት ጋር በተገናኘ በፍርድ ቤቶች ታግዶ ነበር።

እነዚህን ሙግቶች ለማሸነፍ መንግሥት የምስራቅ አፍሪካዊቷን አገር አስተማማኝ አድርጎ የሚፈርጃት ‘የሩዋንዳ ሴፍቲ ቢል’ (የሩዋንዳ የደህንነት ረቂቅን) ለማጽደቅ እየሞከረ ይገኛል።

አዲሱ ዕቅድ ከዚህ ከነበረው የተለየ እንዲሁም በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ እና በፓርላማው በሚጸድቀው ረቂቅ ላይ የተመሰረተ አለመሆኑንም ቢቢሲ ዘግቧል።

መረጃው የቢቢሲ እና ታይምስ ሬድዮ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#April6RWANDA "...እ.ኤ.አ ሚያዝያ 6/1994 በጊዜው የሩዋንዳ ፕሬዝዳንት የነበሩትን ጁቬናል ሃብያሪማናንና የቡሩንዲውን አቻቸውን ሲፕሬን ንታርያሚራን የያዘ አውሮፕላን ተመትቶ 2ቱን ፕሬዚዳንቶች ጨምሮ በአውሮፕላኑ ውስጥ የተሳፈሩት ሁሉም ሰዎች አለቁ፡፡ ፕሬዚዳንት ሃብያሪማና የሁቱ ጎሳ ተወላጅ መሆናቸው በወቅቱ ስልጣን ይዘው የነበሩት ሁቱዎች ለረጅም ዓመታት በሩዋንዳ የመንግሥትን ስልጣን…
#ሩዋንዳ

ዛሬ የሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ (ጄኖሳይድ) 30ኛ ዓመት መታሰቢያ ነው።

በ1994 እ.አ.አ ሩዋንዳ ውስጥ በቱትሲ ጎሣ ላይ የደረሰው የዘር ማጥፋት ዘመቻ በሰው ልጆች ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከደረሱት አሰቃቂ የዘር ጭፍጨፋዎች አንዱ ነው።

በ100 ቀናት ገደማ ውስጥ ብቻ ከ800,000 እስከ 1,000,000 የሚሆኑ ሰዎች እንዳለቁ ይገመታል።

ከተገደሉት ሰዎች መካከል አብዛኞቹ ቱትሲዎች ናቸው፤ ሆኖም በጭፍጨፋው ለመካፈል ፈቃደኛ ያልሆኑ የሁቱ ጎሣ አባላትም የግድያው ሰለባ ሆነዋል።

በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች ተደፍረዋል።

የሩዋንዳ ጄኖሳይድ እንዴት ተፈፀመ ?

- በ10 ሚሊዮን የሚቆጠሩ የሩዋንዳ ዜጎች ለዘመናት እራሳቸውን እንደ #አንድ ነው ሲያዩ የኖሩት።

- በ1916 (እ.አ.አ) ቤንጂየም ሩዋንዳን በቅኝ ግዛት ትይዛታለች። በኃላም በቁጥር የሚበዙትን ሁቱዎች በቁጥር ከሚያንሱት ቱትሲዎች የሚለዩበትን አዲስ ሲስተም የመታወቂያ ወረቀት በመስጠት ዘረጋች። (የብሄር መታወቂያ አከፋፈለች)

- ቱትሲዎቹ በቤልጂየምዎቹ ፦
° በትምህርት ፣
° በስራ፣
° በስልጣን ከፍ ያለ ቦታ እንዲሰጣቸው ተደረገ። ሁቱዎቹ ግን ብዙ ቁጥር ኖሯቸው የትምህርት ፣ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ተነፈጋቸው።

- ቤንጂየሞቹ ቱትሲዎቹ ከብዙሃኑ ሁቱዎቹ የተሻሉ አድርገው እንዲሳሉ አደረጉ።

- በ1959 ሩዋንዳ ነጻነቷን ስታገኝ ሁቱዎች በማመፅ እና የመንግሥትን ስልጣን በመያዝ #ቱትሲዎችን ገደሉ ፣ ከሀገር እንዲሰደዱ አደረጉ። በዚህ ወቅት በመቶ ሺዎች ወደ ጎረቤት ሀገር ተሰደዋል።

- በ1990 በቱትሲ የሚመራው የRwanda Patriotic Front (RPF) ከኡጋንዳ በመሆን በሁቱ በሚመራው መንግሥት ላይ ጥቃት ከፈተ። ይህም የእርስ በእርስ ጦርነት መጀመሪያ ሆነ። በዚህ ወቅት ፈረንሳይ የሩዋንዳን መንግሥት ታስታጥቅ፣ ታሰለጥን ፣ ትደግፍ ነበር። ሩዋንዳም በፕሬዜዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ አማካኝነት በፖል ካጋሚ የሚመራውን ኃይል ትደግፍ ነበር።

- በሩዋንዳ መንግሥትና በRPF ኃይል መካከል የነበረው ጦርነት በ1993 የሰላም ስምምነት እንዲቆም ተደረገ። የUN ኃይልም ስምምነቱ እንዲከበር ለማመቻቸት ዘንድ ወታደራዊ ኃይሉን ላከ።

- በዚህ ሁሉ ጊዜ ውስጥ በሁቱ እና በቱስቲዎች መካከል ያለው ውጥረት እጅግ በጣም እየከፋ ነበር የሄደው። የጥላቻ ፕሮፖጋንዳውን ከፍ ብሎ ነበር። በእርስ በእርስ ጦርነቱ ወቅት የሩዋንዳ መንግሥት RPFን እንደ ጠላት፣ እንደ ሀገር ካጅ፣ ባንዳ፣ እያደረገ ፕሮፖጋንዳ ሲሰራ ነበር።

-  ሚያዚያ 6 ቀን 1994 የሁቱ ጎሳው ፕሬዜዳንት ጁቬናል ሃብያሪማና ተሳፍረውበት የነበረው አውሮፕላን ኪጋሊ በሚገኝ ኤፖርት አካባቢ ተመትቶ ወደቀ። ፕሬዜዳንቱም ህይወታቸው አለፈ። በወቅቱ የቡሩንዲው ፕሬዝዳንት ሳይፕሪን ንታያሚራ አብረዋቸው ነበሩ እሳቸውም ሞቱ።

- ፕሬዚዳንቱን የገደላቸው ማን እንደሆነ በግልጽ ባይታወቅም ሁቱዎቹ የቱትሲ አማፂ ቡድን ነው የፈፀመው ብለው በሚዲያ አስወሩ። ሁቱዎች እየወጡ ቱትሲዎችን እንዲገድሉ በሚዲያ ጥሪ አቀረቡ።

... በቃ #ግድያው ተጀመረ። ከ800 ሺህ እስከ 1,000,000 ቱትሲዎች እና ለዘብተኛ ሁቱዎች አለቁ። ከ100 ቀን በኃላ የRPF ኃይል ወደ ኪጋሊ ሲቃረብ ግድያው አቆመ ሁቱዎቹም መሸሽ ጀመሩ፣ በተለይ ሲገድሉ ሲያስተባብሩ የነበሩት ሀገር ጥለው ወጡ።

ሚዲያዎች ? የውጭ ሀገር ኃይሎች ? ተመድ በዚህ ውስጥ ምን ሚና ነበራቸው ? በቀጣይ  ፅሁፍ እንዳስሳለን።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
Rwandan genocide
Apr 7, 1994 – Jul 15, 1994

@tikvahethiopia
#Rwanda #UK

ዩናይትድ ኪንግደም (UK) ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ #ሩዋንዳ ለማዛወር የያዘችው እና ከፍ ያለ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የታመነው ዕቅድ የሃገሪቱ ሕግ ሊሆን እንደተቃረበ ቪኦኤ ዘግቧል።

የዕቅዱ ተቃዋሚዎች ደግሞ ስደተኞቹን #በኃይል ከአገር የማስወጣቱን ውጥን ማገድ የሚችል አዲስ የሕግ መቋቋሚያ ለማበጀት እየሰሩ እንደሆነ ተነግሯል።

የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን እገዳ ተጽዕኖ ለማስቀረት እና በላይኛው ምክር የቀረበውን ተቃውሞ ለመቋቋም የታለመው ይህ ሕግ በዚህ ሳምንት በሃገሪቱ ፓርላማ ይድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

‘ የሩዋንዳ ዕቅድ ’ የሚል ቅጽል የተሰጠው ይህ ውጥን ጠቅላይ ሚንስትር ሪሺ ሱናክ ‘ሕገ ወጥ ስደተኞችን ወደዚያች አገር የሚያጓጉዙ ጀልባዎች እንቅስቃሴ’ ለማስቆም ለገቡት ቃል ‘ወሳኝ እርምጃ ነው’ ተብሏል።

የሱናክ ቃል አቀባይ ዴቭ ፓሬስ ምን አሉ ?

" የእንግሊዝ ፓርላማ በያዝነው ሳምንት በሕገ ወጥ አስተላላፊዎች ከፍተኛ እንግልት እና ብዝበዛ የሚፈጽምባቸውን ሰዎች ህይወት የሚታደግ ህግ የማጽደቅ እድል ያገኛል።

አሁን ባለው አካሄድ መቀጠል እንደማንችል ግልፅ ነው። በመሆኑም ይህ ሁኔታ የሚለወጥበት ጊዜው አሁን ነው። " ብለዋል።


በአነስተኛ ጀልባዎች ተጓጉዘው የእንግሊዝ ቻናልን በማቋረጥ ከዚያ የሚደርሱትን ጥገኝነት ጠያቂዎች ወደ ምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ሩዋንዳ ለማዛወር እና በቋሚነትም ኑሯቸውን በዚያ እንዲያደርጉ በማቀድ ሁለቱ አገሮች የተፈራረሙት ስምምነት 2 ዓመታት አስቆጥሯል።

በፍርድ ቤት የታገደው ዕቅድ እንግሊዝን በትንሹ 470 ሚሊዮን ዶላር ሊያስወጣት እንደሚችል ቪኦኤ በዘገባው አስፍሯል። #VOA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Rwanda #UK ዩናይትድ ኪንግደም (UK) ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ #ሩዋንዳ ለማዛወር የያዘችው እና ከፍ ያለ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የታመነው ዕቅድ የሃገሪቱ ሕግ ሊሆን እንደተቃረበ ቪኦኤ ዘግቧል። የዕቅዱ ተቃዋሚዎች ደግሞ ስደተኞቹን #በኃይል ከአገር የማስወጣቱን ውጥን ማገድ የሚችል አዲስ የሕግ መቋቋሚያ ለማበጀት እየሰሩ እንደሆነ ተነግሯል። የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን እገዳ ተጽዕኖ ለማስቀረት እና…
" ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ መላክ እንጀምራለን፤ ... የንግድ ቻርተር አውሮፕላኖችንም ተከራይተናል " - ጠ/ሚር ሪሺ ሱናክ

ዩናይትድ ኪንግደም በቁጣዮቹ ከ10 እስከ 12 ሳምንታት ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ #ሩዋንዳ መላክ ትጀምራለች።

የዩናይትድ ኪንግደም ፓርላማ ስደተኞች/ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ ለመመለስ የተያዘውን እቅድ መጀመር የሚያስችለውን " የሩዋንዳ እቅድ " የተሰኘውን ረቂቅ ሕግ ትላንት አጽድቋል።

ጠ/ሚር ሪሺ ሱናክ፥ " በቀጣዮቹ ከ10 እስከ 12 ሳምንታት ባለው ጊዜ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ መላክ እንጀምራለን " ብለዋል።

ለዚህም ፤ የንግድ ቻርተር አውሮፕላኖች ኪራይ መፈጸሙና ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ የሚወስዱ ሰራተኞችም መሰልጠናቸው ተነግሯል።

52,000 ጥገኝነት ጠያቂዎች ወደ ምስራቅ አፍሪካዋ ሩዋንዳ ይዘዋወራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በቅርብ አመታት ፦
- #ከአፍሪካ
- ከመካከለኛው ምስራቅ
- ከኢስያ ጦርነት እና ድህነት የሚሸሹ በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ዩናይትድ ኪንግደም ገብተዋል።

እነኚህ ስደተኞች በህገ ወጥ የሰው አዘዋዋሪዎች አማካኝነት በትንንሽ ጀልባዎች ተጉዘው ነው ዩናይትድ ኪንግደም የሚገቡት። #ሮይተርስ

@tikvahethiopia