TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ማስታወሻ

ለአዲስ አበባ ከተማ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ፦

1ኛ. የሞተር ባለንብረቶች እንዲሁም በሞተር እየተንቀሳቀሳችሁ ስራችሁን ለምትሰሩ አባላቶች ከነገ አርብ የካቲት 8 /2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ እስከ ሰኞ የካቲት 11/2016 ዓ.ም ጠዋት 2:00 ሰአት ድረስ ሞተር ማሽከርከር ፍፁም ተከልክሏል። የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ ክልከላውን በሚተላለፉ ላይ " ጥብቅ እርምጃ እወስዳለሁ " ብሏል።

                                 __

2ኛ. ለአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ #መሪዎች ወደ አዲስ አበባ እየመጡ ይገኛሉ። በዚህ ምክንያት መሪዎች እስኪያልፉ ድረስ መንገዶች ለሌሎች ተሽከርካሪዎች ሊዘጉ ይችላሉ።

ፖሊስ አማራጭ / ተለዋጭ መንገዶችን ተጠቀሙ ብሏል።

ከፓርላማ መብራት-በውጭ ጉዳይ ሚ/ር - መስቀል አደባባይ   ፍላሚንጎ  - ኦምሎፒያ  -  ወሎ ሰፈር - ጃፓን ኤምባሲ - ፍሬንድ ሺፕ -ቦሌ ቀለበት መንገድ - ኤርፖርት

ከፓርላማ መብራት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር - በብሔራዊ ቤተ - መንግስት - በፍልውሃ - በብሔራዊ ቴአትር- ሜክሲኮ አደባባይ - አፍሪካ ህብረት አዳራሽ ዙሪያ

ከፓርላማ መብራት -ብሔራዊ ቤተ-መንግስት - ወዳጅነት ፓርክ - ንግድ ማተሚያ ቤት - ሞናርክ ሆቴል-ቴዎድሮስ አደባባይ-ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል- ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን- ብሔራዊ ቴአትር - ሜክሲኮ አደባባይ - አፍሪካ ህብረት መንገዶች እንግዶች የሚያልፉባቸው ናቸው።

ከዚህ ባለፈ ፦

ከፓርላማ መብራት-በሸራተን ሆቴል ቁልቁለቱን-ፍልውሃና አምባሳደር ቴአትር ዙሪያውን

ከንግድ ምክር ቤት ጀምሮ በሱዳን ኤምባሲ - አፍሪካ ህብረት ዋናው በር - ሳርቤት ድረስ በሁለቱም አቅጣጫዎች እንግዶች ተጠቃለው እስኪመለሱ ግራና ቀ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ተከልክሏል።
  
                                __

3ኛ. 37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2016 ዓ.ም ይካሄዳል። የ2024 መሪ ቃል ፤ " ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን አፍሪካዊ ማስተማር፤ የማይበገሩ የትምህርት ስርዓቶች በመገንባት በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ፣ የሕይወት ዘመን፣ ጥራትና አግባብነት ያለው የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋት " የሚል ነው።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BGI #PurposeBlack " ነገ ጥዋት መግለጫ እንሰጣለን "- ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያን አ/ማ በቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መካከል ሲካሄድ የቆየው አ/አ #ሜክሲኮ የሚገኘው የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ድርድር ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ ተቋርጧል። ቢጂአይ-ኢትዮጵያ በባከልን ኢሜል የሽያጩ ውል የተቋረጠው ፤ በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትሬዲንግ አ/ማ በኩል…
#PurposeBlack

ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ምን አለ ?

- የቢጂአይ ኢትዮጵያ የዋናው መሥሪያ ቤት ሽያጭ ውልን በውልና ማስረጃ በኩል ለመፈጸም ዝግጁ ነን።

- ቢጂአይ ኢትዮጵያ የመንግስትን ግዴታ ቀድሞ ባለመወጣቱ በውል እና ማስረጃ መፈራረም አልተቻለም። ከታክስ ጋር በተያያዘ ክሊራንስ አልጨረሱም።

- ቢጂአይ ብዙ ማሟላት ያለበትን ዶክመንት አላሟላም። በዚህ ምክንያት በውል እና ማስረጃ ለመፈራረም አልፈለጉም።

- ለቢጂአይ 1 ቢሊዮን 150 ሚሊዮን ብር ክፍያ ፈፅመናል። ቀሪውን ገንዘብ በውልና ማስረጃ ስንፈራረም ለመክፈል ዝግጁ ነን።

- ክፍያው በ3 ዙር የሚፈፀም ሲሆን 2ኛው ዙር ክፍያ የሚፈጸመው በውልና ማስረጃ ስንፈራረም ነው። ይህ ቀድሞ በፈጸመው ውል ላይ ተቀምጧል።

- ከታክስ ነፃ የሆኑበት ወረቀት ከቀረበ በውልና ማስረጃ እንፈራረማለን። እኛ ተገቢውን ዶክመት ካሟሉ በሁለተኛ ዙር የሚጠበቅብንን 2.5 ቢልየን ብር ለመክፈል ዝግጁ ነን።

- ቅዳሜ የካቲት 23 /2016 ዓ.ም በውልና ማስረጃ እንዋዋል የሚል ደብዳቤ ልከንላቸው ነበር። እነሱ ሕጋዊ  መስፈርቶችን ማሟላት ባለመቻላቸው ውሉን አቋርጠናል የሚል መግለጫ ትናንት አውጥተዋል።

- እኛ ብሩን ለመክፈል ዝግጁ ነን በውልና ማስረጃ የማይፈራረሙ ከሆነ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት እንወስዳለን።

- ኃላፊነቱን እየተወጣ ያልሆነው በውልና ማስረጃ እንዲፈፀም ኃላፊነቱን ያልተወጣው ቢጂአይ ኢትዮጵያ እንጂ እኛ አይደለንም።

- አሁንም ግዢውን ለመፈፀም ዝግጁ ነን።

- ሌላ አማራጭ መሬቶችን ገዝተናል። መሰረት እየጣልን ነው። በገባነው ቃል ቤቶቹን በሚቀጥሉት 5 አመታት ሰርተን እናስረክባለን።

- ከመንግስት በሊዝ ስምምነት እንዲሁም 30/70 በሚል ስምምነት በግዢ ሂደት ላይ ያሉ መሬቶችም አሉ።

- ቤት ለመሸጥ ቃል ለገባንላቸው ደንበኞች ቤቱን እናስረክባለን።

በትላንትናው ዕለት ቢጂአይ-ኢትዮጵያ በላከልን ኢሜል አ/አ #ሜክሲኮ የሚገኘው የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ድርድር ውል ለማሰር ባለመቻሉ መቋረጡን ማሳወቁ ይታወሳል።

የሽያጩ ውል የተቋረጠው ፤ በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትሬዲንግ አ/ማ በኩል ግብይቱን ለማጠናቀቅ እና የሽያጭ ውሉን ለመፈረም ፍላጎትና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ እንደሆነ መግለፁ አይዘነጋም።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#PurposeBlack ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ምን አለ ? - የቢጂአይ ኢትዮጵያ የዋናው መሥሪያ ቤት ሽያጭ ውልን በውልና ማስረጃ በኩል ለመፈጸም ዝግጁ ነን። - ቢጂአይ ኢትዮጵያ የመንግስትን ግዴታ ቀድሞ ባለመወጣቱ በውል እና ማስረጃ መፈራረም አልተቻለም። ከታክስ ጋር በተያያዘ ክሊራንስ አልጨረሱም። - ቢጂአይ ብዙ ማሟላት ያለበትን ዶክመንት አላሟላም። በዚህ ምክንያት በውል እና ማስረጃ ለመፈራረም…
#PurposeBlack

የፐርፐርዝ ብላክ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አፈፃሚ ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ በአሁን ሰዓት #አሜሪካ ሀገር እንደሚገኙ ተነግሯል።

" አሜሪካ የሚገኙት ለስራ ነው " ያለው ድርጅቱ የፊታችን ሀሙስ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱና መግለጫም እንደሚሰጡ አመልክቷል።

ዛሬ መግለጫ ሰጥተው የነበረው የድርጅቱ የቦርድ አባል እና የህግ አማካሪ ዶ/ር ኤርሚያስ ብርሃኑ ናቸው።

ፐርፐዝ ብላክ ከቤቶቹ ግንባታ እና ከአክሲዮን ባለቤቶች ጋር በተያያዘ ምን አለ ?

- ለቤቶች ግንባታ ሌላም መሬት መግዛቱን ገልጿል።

- አሁን በገባው ቃል መሰረት ቤቶቹን በሚቀጥሉት 5 አመታት ሰርቶ እንደሚያስረክብ አመልክቷል። 

- " #ወሰን " አካባቢ ለቤቶች ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ተጥሏል ብሏል።

- የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያን አክሲዮኖች የገዙ ዜጎች ብራቸው #እንደማይመለስ ገልጿል። ነገር ግን ባለ አክሲዮኖች አክሲዮናቸውን መሸጥ ይችላሉ ብሏል።

- በአሁኑ ሰዓት ድርጅቱ ለ1 ሺ ባለ አክሲዮኖች የአክሲዮን ሽያጭ ካደረገ በኋላ የአክሲዮን ሽያጭ ማቆሙን ገልጿል።

- በተለዩ ቦታዎች መሬት እና ንብረትን ከግለሰቦች በመግዛት ፣ መሬት እና ንብረቱን አፍርሶ በመስራት እና ከባለሃብት ጋር አብሮ በማልማት በ3 አማራጮች ግንባታ ለመጀመር የሚጠቀማቸው አማራጮች መሆናቸውን አሳውቋል።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#PurposeBlack የፐርፐርዝ ብላክ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አፈፃሚ ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ በአሁን ሰዓት #አሜሪካ ሀገር እንደሚገኙ ተነግሯል። " አሜሪካ የሚገኙት ለስራ ነው " ያለው ድርጅቱ የፊታችን ሀሙስ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱና መግለጫም እንደሚሰጡ አመልክቷል። ዛሬ መግለጫ ሰጥተው የነበረው የድርጅቱ የቦርድ አባል እና የህግ አማካሪ ዶ/ር ኤርሚያስ ብርሃኑ ናቸው። ፐርፐዝ ብላክ ከቤቶቹ ግንባታ…
ቢጂአይ-ኢትዮጵያ መግለጫ ሰጠ።

በቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መካከል ሲካሄድ የቆየው አ/አ #ሜክሲኮ የሚገኘው የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ድርድር ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ መቋረጡን ተከትሎ ከሁለቱም ወገን መግለጫዎች መውጣታቸው ይታወሳል።

ቢጂአይ ኢትዮጵያ ውሉ ስለመቋረጡ ከገለጸ በኋላ ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ በሰጠው መግለጫ ላይ በተነሱ ጉዳዮች ዙሪያ የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ህግ ክፍሉ ዳይሬክተር አቶ ነጋ ምህረቴ እንዲሁም የህግ አማካሪ የሆነው "ምህረታብ እና ጌቱ አድቮኬትስ ኤል ኤል ፒ" መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫው ላይ የተነሱ ጉዳዮች ምንድናቸው ?

- የድርድር ሂደቱ 8 ወራት ፈጅቷል። ቀድመን የተፈራረምነው የቀብድ ውል ነው። የቀብድ ውሉ የጊዜ ገደቡ ሦስት ወር ቢሆንም በእኛ በኩል በቅንነት 8 ወራት ጠብቀናል።

- ቀብድ ውሉን ከተፈራረምን በኋላ በእኛ በድርጅታችን ኃላፊ ጭምር እንዲሁም የመክፈል አቅም እንዳላቸው በተደጋጋሚ ማስረጃ እንዲሰጡን ብንጠይቅም እንከፍላለን ከሚል ደብዳቤ በስተቀር የሚጠበቅባቸውን ብር ለመክፈል አቅም እንዳላቸው ማስረጃ ማቅረብ አልቻሉም።

- ግብር ለመክፈል ወደኋላ የምንል አይደለንም። የሚሸጠውም ህንጻ እዳ ያለበት አይደለም ቢጂአይ እዳ ያለበት ንብረት ለሽያጭ አያቀርብም።

- ካፒታል ጌን ኪሊራንስ ለማውጣት በቅድሚያ የሽያጭ ውል መሟላት አለበት። ይህ በሌለበት ሁኔታ ክሊራንስ ማውጣት አንችልም። ይህ በህጉ የተቀመጠ የታወቀ አሰራር ነው። ቢጂአይ ክሊራንስ ለማምጣት ዝግጁ ቢሆንም ነን በቀብድ ውሉ በተጠቀሰው መሰረት በቅደም ተከተል በተቀመጠው መሰረት የሽያጭ ውሉ ላይ መስማማት ያስፈልጋል። የተለያዩ ውይይቶች ቢደረግም እሱን መፈረም አልቻሉም።

- በቀብድ ውሉ መሰረት የተከፈለው 1 ቢሊዮን ብር +15 VAT ሲሆን ቀጣዩን ክፍያ ለመክፈል የሽያጭ ውሉን መፈረም እንዲሁም በውልና ማስረጃ ሌሎች የሚያስፈልጉ ዶክመንቶች ቀርቦ እንዲጸድቅ ይጠበቃል። ይህንን ለማድረግ ከሚያስፈልገው አንዱ የሽያጭ ውል ሲሆን ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ይህንን መፈረም ባለመቻሉ ውሉን ለማቋረጥ ተገደናል።

- ከፐርፐዝ ብላክ ጋር ያለን ውል ተቋርጧል። ዳግም ተመልሰን የምንደራደርበት ነገር የለም። ይህ ውል ከተጠናቀቀ በኋላ ህንጻውን የመሸጥ አሁንም ፍላጎት አለን።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ቢጂአይ-ኢትዮጵያ መግለጫ ሰጠ። በቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መካከል ሲካሄድ የቆየው አ/አ #ሜክሲኮ የሚገኘው የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ድርድር ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ መቋረጡን ተከትሎ ከሁለቱም ወገን መግለጫዎች መውጣታቸው ይታወሳል። ቢጂአይ ኢትዮጵያ ውሉ ስለመቋረጡ ከገለጸ በኋላ ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ በሰጠው መግለጫ ላይ በተነሱ ጉዳዮች ዙሪያ የቢጂአይ…
ቢጂአይ-ኢትዮጵያ ፤ " ውሉ የተቋረጠው ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ የሽያጭ ውሉን ለመፈረም ፈቃደኛ ባለመሆኑ ነው " ሲል ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

" የመክፈል አቅም እንዳላቸው በተደጋጋሚ ማስረጃ እንዲሰጡን ብንጠይቅም ' እንከፍላለን ' ከሚል ደብዳቤ በስተቀር የሚጠበቅባቸውን ብር ለመክፈል አቅም እንዳላቸው ማስረጃ ማቅረብ አልቻሉም " ሲልም ገልጿል።

ቢጂአይ-ኢትዮጵያ ግብር ለመክፈል ወደኋላ የሚል እንዳልሆነና የሚሸጠውም ሜክሲኮ የሚገኘው የዋናው መስሪያ ቤት ህንጻ እዳ እንደሌለበት አስገንዝቧል።

እዳ ያለበት ንብረት ለሽያጭ እንደማያቀርብም ገልጿል።

" ከፐርፐዝ ብላክ ጋር ያለን ውል ተቋርጧል። " ያለው ቢጂአይ-ኢትዮጵያ " ዳግም ተመልሰን የምንደራደርበት ነገር የለም። ይህ ውል ከተጠናቀቀ በኋላ ህንጻውን የመሸጥ አሁንም ፍላጎት አለን " ብሏል።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray

የትግራይ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ጥያቄ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ ምን ነበር ?

ከትግራይ ወደ አ/አ የመጡ የማህበረሰቡ ተወካዮችና እዚህም ያሉ ተወላጆች ከጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር በነበራቸው ቆይታ ፤ የትግራይ ህዝብ ከማንም ህዝብ ጋር  መጋጨት እንደማይፈልግ ገልጸው ፓለቲከኞችም ልጓም ማበጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

በአፅንኦት በጦርነቱ ከቄያቸው የተፈናቀሉ ወደ ቦታቸው እንዲመለሱና የክልሉ አስተዳደራዊ ወሰን እንዲከበር ጠይቀዋል።

በጥቅሉ ያነሷቸው ጥያቄዎች  ምንድናቸው ?

- የመከላከያ አባላት የነበሩት ጨምሮ ሌሎች የፓለቲካ እስረኞች ይፈቱ፤
- የትግራይ ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት የወሰዱት የብድር ወለድና ቅጣት ይነሳ፤
- የመንግስት ሰራተኞችና የጡረተኞች ውዙፍ ደመወዝና አበል ይከፈል፤
- ከትግራይ ሰራዊት (TDF) ለተሰናበቱ ታጣቃዊች ማቋቋምያ ይከፈል፤
- ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ይመለሱ የትግራይ ሉአላዊ ግዛት ይከበር፤
- ከረሃብ ጋር በተያያዘ እርዳታ ይደረግ ፤
- የህወሓት የህጋዊነት ጥያቄ ለምን ዘገየ ?
የሚሉና ሌሎች ይገኙባቸዋል።

ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ምን መለሱ ?

ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኃላ ብዙ ስኬቶች እንዳሉ አሁንም ግን የሚቀር ብዙ እንዳለ ገልጸዋል። ከሰላም ስምምነቱ በኃላ በጥይት ሰው እንዳልሞተ ተናግረዋል። በትግራይ መረጋጋት ፤ መንግሥት መመስረት ፣ ህወሓት (TPLF) ከሽብርተኝነት መፋቅ የስምምነቱ ውጤት ነው ብለዋል።

ከስምምነቱ በኃላ በርካታ ቢሊዮን ብሮች በካሽም በቁሳቁስም ወደ ትግራይ ክልል መላኩን ገልጸዋል።

እስረኞችን መፍታት በተመለከተ ፦

" ስብሃትን ፈትቼው የለም እንዴ ? ፣ አልፈልግም እንዲታሰሩ።

የመከላከያን በተመለከተ እራሱ ይነግራችኋል (ዶ/ር አብርሃምን ማለታቸው ነው) አላውቅም በእኔ እውቀት #አንድም_የታሰረ_ሰው_የለም።  ከስራ ያቆምናቸው ታጋዮች ነበሩ እርቁ ሲፈፀም መፍታት እኮ አይደለም ወደቦታቸው ነው የመለስናቸው። አሃዱ አለቃ ናቸው ሁሉም በየቦታው በየደረጃው ኃላፊዎች ናቸው መከላከያ ውስጥ ...

እስረኛ በሌብነት ምክንያት ካለ አላውቅም ፤ እስረኛ ሰው ገድሎ የታሰረ ወንጀለኛ ካለ አላውቅም። ከግጭቱ ጋር የሚያያዝ ግን በመከላከያ ወጥተው የነበሩት ተመልሰው መከላከያ ውስጥ ገብተዋል።

እኛ እንደዚህ አይነት ፍላጎት የለንም። የምናውቀውም የለም። እኛ እስረኛ ፈተን ስራ አስፈፃሚ ፈተን ጌታቸው ጋር የቀሩ እስረኞች ነበሩ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ያልፈታቸው ። "

ትግራዋይ ተፈናቃዮችን በሚመለከት ፤ ተፈናቃዮች በስምምነቱ መሰረት ቤታቸው መመለስ አለባቸው ብለዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ፣ የአማራ ክልሉ አቶ አረጋ ፣ ዶ/ር አብርሃም ያሉበት ኮሚቴ ተቋቁሞ ሰሞኑን ንግግር ይደረጋል ሲሉ ገልጸዋል።

የፌዴራል መንግሥት ፍላጎት መጀመሪያ የተፈናቀሉ ሰዎች በሙሉ ቤታቸው እንዲመለሱ ነው ያሉ ሲሆን " በማንኛውም ሰዓት ነገ ሁመራ ያለው ቤቴ መመለስ እፈልጋለሁ የሚል ካለ እኛ ለመመለስ ዝግጁ ነን " ብለዋል።

#መከላከያ በአካባቢው የትግራይም ይሁን የአማራ ፀጥታ ኃይል እንዳይኖር ኃላፊነት እንደተሰጠው ገልጸዋል።

ሁሉም ሰዎች ወደ ቤታቸው #ከተመለሱ_በኃላ እራሱ ህዝቡ አስተዳዳሪውን እንዲመርጥ እንደሚደረግና ከተረጋጋ በኃላ ህዝቡ ሪፈረንደም በማድረግ " እኔ አማራ ነኝ ፤ እኔ ትግራይ ነኝ " የሚለውን እንደሚወስን ተናግረዋል።

ጠ/ሚኒስትሩ ተፈናቃዮች መቐለ ፣ ሽረ መቀመጥ እንደማያስፈልጋቸውና ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል። በዚህ ረገድ ፌዴራል መንግሥት የሚጠበቅበትን እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

በነበረው ሁኔታ ውጭ ሀገር የሄደ ባለሃብት ካለ መመለስ ይችላል ፣ ከባላሃብቶች ጋር በተያያዘ ችግር ካለም ይፈታል ብለዋል።

#ረሃብን በተመለከተ ጉዳዩን ፖለቲካዊ ማድረግ እንደማይገባና ትግራይ ተርባ ሌላው የኢትዮጵያ ክፍል በልቶ ጠግቦ እንደማያድርግ ገልጸዋል። " ጌታቸውንም ወቅሼዋለሁ ረሃብ ካለ መደወል ነው እኔ ጋር ያለ አምጡ አግዙ ማለት ነው ቀላል ነው በትዊተር ከሆነ ግን እኛ በትዊተር አንነጋገርም ብሄዋለሁ ለሌሎች ነው የነገርከው እንጂ እኔ አልሰማሁም " ሲሉ ገልጸዋል። " ረሃብ ረሃብ ችግር ችግር አለ የሚል ፖለቲካ " ማድረግ ተገቢ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኮሚቴ ተቋቁሟል ሄዶ ጥናት አድርጎ መደረግ ያለበት ይደረጋል ሲሉ ገልጸዋል።

የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ/TPLF እውቅናን በተመለከተ ጉዳዩ የምርጫ ቦርድ ቢሆንም " በእኛ በኩል መሰጠት አለበት ብለን እናምናል ፤ በቅርብም #አነጋግረናቸዋል የሚፈታ ይመስለኛል ፤ ብዙም ከባድ አይደለም " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

#ከባንክ ጋር በተያየዝ ጉዳዩ ውስብስብ መሆኑን በማስረዳት መናገር ያልፈለጉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቢሯቸው አማካሪዎች እና ጉዳዩን በቀጥታ የሚያዩ የሚመለከታቸው አካላት ተነጋገረው የሚቻል ነገር ካመጡ ለማገዝ ፍላጎት እንዳላቸው ጠቁመዋል።

ከባንክ ብድር ጋር በተያያዘ " ብድር ተከለከልን " የሚሉ ባላሃብቶች ካሉ ከዶ/ር አብርሃም እና ከሌሎች የሚመደቡ ሰዎች ጋር እንዲነጋገሩ አቅጣጫ ሰጥተው አልፈዋል። በመንግሥት ፖሊሲ ሊፈታ የሚችል ካለ ግን እንደሚታይ ገልጸዋል።

በኤርታራ መንግሥት (በሻዕብያ ኃይል) ስለተያዙ መሬቶች በተመለከተ ፤  የፌዴራል እና ከትግራይ የጋራ ኮሚቴ መቋቋሙን በዚህም የሀገር መከላከያ ከትግራይ ጓዶች ጋር በመሆን ቦታዎችን እንዲያዩ እንደሚደረግ ገልጸዋል። " #ከአልጀርስ_ስምምነት ውጭ የሆነ ካለ ሪፖርቱ ሲመጣ እናያለን ፤ ማንም የማንንም ቦታ በኃይል ይዞ ለዘላለም መኖር አይችልም እንዳንዋጋ፣ ዳግም ግጭት እንዳይፈጠር ትርፍ ነገር የተካሄደ ካለ አይተን ቦታውን ለይተን ኦፊሻሊ እነዚህ ነገሮች ይስተካከሉ ብለን በንግግር መልክ ልናበጅ እንችላለልን " ብለዋል። ውጤቱ ታይቶ ለህዝብ ይፋ ይደረጋል ሲሉ ተግረዋል።

➡️ የጡረተኞችን ውዝፍ ክፍያን በተመለከተ ምንም ሳይሉ አልፈው በአቶ ጌታቸው በኩል ያለውን ነገር እንደሚያሳውቁ ገልጸዋል።

ሌሎችም አንዳንድ በተነሱ ጥያቄዎች ላይ በቀጥታ አስተያየት ባይሰጡም በጥቅሉ በክልሉ ካሉ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ በውይይት በምክክር እንደሚፈቱ ቃል ገብተዋል።

#TikvahFamilyMekelle
#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

➡️ " የቀብር ስርዓቱ ተፈጽሟል " - የዶክተር በሀይሉ ቤተሰብ 

➡️ " ይቅርታ መረጃው የለኝም " - የአዲስ አበባ ፓሊስ

እውቁና እጅግ የተዋጣላቸው የቀዶ ጥገና ሐኪም ዶ/ር በኃይሉ ኃይሉ መገደላቸውን የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ዶ/ር በኃይሉ ከቀናት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ ለጥዋት ሩጫ በሚል በወጡበት በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው ነው የተገለጸው።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ አንድ የሟች ቅርብ ቤተሰብ፣ " ቤተሰብ ጠቅላላ ' ወጥቶ ሞተ ' ነው የምናውቀው። ሚዲያ ላይ ካለው ውጪ አዲስ የሰማነው ነገር የለም " ብለዋል።

ስርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል ? ቤታቸው የት አካባቢ ነው ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ " ቀብሩ ተፈጽሟል፣ ከትላንት ወዲያ ሰዓሊተ ምህረት " ብለው፣ ቤታቸውን በተመለከተም፣ " ቦሌ ሚካኤል ነው። ሞተ ያሉት ደግሞ ወደ ሳሪስ በሚወስደው ድልድይ ጠዋት ወክ ሲያደርግ ነው። ዞሮ ዞሮ አስከሬኑን ፓሊስ ነው ያነሳው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስን ለመጠየቅ ጥረት አድርጓል።

የኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ በሰጡት አጭር የፅሑፍ  ምላሽ፤  " ይቅርታ መረጃው የለኝም " ሲሉ ለጊዜው አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

በቀጣይም የአዲስ አበባ ፖሊስን ስለ ጉዳዩ የምጠይቅ ይሆናል።

በተጨማሪም ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፣ የቀድ ጥገና ሀኪሙን ግድያ በተመለከተ የደረሰው መረጃ እንዳለ ለኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኀበር ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፣ አንድ የማኀበሩ ባለስልጣን በሰጡት ቃል፣ " እኔም በማኀበራዊ ድረገፅ ነው የሰማሁት በጣም ያሳዝናል " ብለዋል።

አክለውም፣ " ሦስት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ነው ተመሳሳይ ነገር የተፈጸመው። ዶክተር እስራኤል ጥላሁን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገሏል። እየሆነ ያለዉ ነገር ልብ ይሰብራል። ሁኔታውን አጣርተን መግለጫ እናወጣለን። ለአሁኑ ግን በቂ መረጃ የለንም በጉዳዩ ዙርያ " ሲሉ አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ሕክምና ማኀበር በበኩሉ በዶክተር በሀይሉ ሀይሉ ሞት የተሰማውን ሀዘን በመግለጽ መግለጫ አውጥቷል።

ለዶክተሩ ቤተሰቦች፣ ወዳጆች፣ የስራ ባልደረቦች መፅናናትን ተመኝቷል።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
“ሹፌሩን፣ ጋቢና የነበሩ 2 ሰዎችን ጭንቅላታቸውን በሰደፍ መቷቸው። በገመድ አስረው፣ አፋቸውን በፕላስተር አስይዘው መኪናውን ይዘው ሄዱ ” - የተሽከርካሪው ባለቤት

“ እንዲህ አይነት ወንጀሎች ከዕለት ዕለት እየጨመሩ ነው ” - የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበር

#ከአዲስ_አበባ ተነስቶ ወደ #ወላይታ_ሶዶ 70 ኩንታል ዱቄት ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ተሽከርካሪ በሻሸመኔ እና ሀዋሳ መካከል ከቶጋ ካምፕ አለፍ ብሎ ቢሻን ጉራቻ (ጥቁር ውሃ) መግቢያ ላይ በሚገኝ ቦታ ማክሰኞ መጋቢት 3 ቀን 2016 ዓ/ም ከምሽቱ 3 ሰዓት ገደማ ላይ በታጠቁ ኃይሎች እንደተወሰደና እንዳልተመለሰላቸው የተሽከርካሪው ባለቤት፣ ሌላ እማኝና የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የተሽከርካሪው ባለቤት በሰጡት ቃል፣ “ ሹፌሩን፣ ጋቢና የነበሩ 2 ሰዎችን ጭንቅላታቸውን በሰደፍ መቷቸው። በገመድ አስረው፣ አፋቸውን በፕላስተር አስይዘው መኪናውን ይዘው ሄዱ ” ሲሉ ገልጸዋል።

እንዲህ ያደረጉ አካላት ማን እንደሆኑ ሲያስረዱ ፣ “ ደብል ጋቢና በሆነ መኪና (አሮጌ ነገር ነው) እርሱ ላይ ሰዎች ነበሩ፣ 3 ክላሽ 1 ሽጉጥ የያዙ። ‘ኬላ ጥሳችሁ ነው የመጣችሁት አሉ’። ኬላ አልጣስንም ያው ደረሰኙ ቢላቸውም ‘አይ ውረድ ውረድ’ ብለው ሹፌሩን በሰደፍ መቱት ጭንቅላቱ ላይ፣ ጋቢና ላይ የነበሩ ሁለት ሰዎችንም አስወረዱ እነርሱንም ጭንቅላታቸውን በሰደፍ መቷቸው ” ነው ያሉት።

በገመድ አስረው ፣ አፋቸውንም በፕላስተር አስይዘው እንደነበር በኃላም አላሙዲን እርሻ ፊት ለፊት ባለው አቅጣጫ መኪናውን ይዘው እንደሄዱ ተናግረዋል።

የተሽከርካሪው ባለቤት ፤ በሰደፍ ተመቱ የተባሉት ሰዎች ቢለቀቁም ቁስሉ እንዳልተሻላቸው ገልጸዋል።

“ ዱቄቱ 70 ኩንታል ነው። 210 ሺሕ ብር ይገመታል። መኪናው  አዲስ ነው 2022 ሞዴል ቢ 24 ነው። መኪናውን ይመልሱልኝ ” ሲሉ የመኪናው ባለቤት ተማጽነዋል።

ሌላኛው ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ አካል በበኩላቸው፣ “ ሹፌሩንና ረዳቱን ደበደቡ። የኤሌክትሪክ ፓል ጋ ሹፌሩን አሰሩ። ከዚያ መኪናውን ይዘው ሄዱ። እስከዛሬ ፋይዳ የለም ” ሲሉ አረጋግጠዋል።

ተፈፀመ የተባለውን ድርጊት አስመልክቶ ምላሽ እንዲሰጥ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበለት ጣና የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበር ቡኩሉ ፣  70 ኩንታል ዱቄት ጭኖ የነበረው ተሽከርካሪ በሻሸመኔ ቢሻን ጉራቻ (ጥቁር ውሃ) መግቢያ ላይ እንዲቆም ተደርጎ እንደተወሰደ፣ ሰዎቹ ተደብደብዋል መባሉም እውነት ነው እንደሆነ ገልጿል።

አንድ የማኀበሩ ኃላፊ ፤ ሌላም እዚህም ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ ከድሬዳዋ ዘይት ጭኖ የቆመ መኪና ሰሞኑን ጠፍቶ እንደነበር፣ መጨረሻም ጭነቱ ተራግፎ ቆሞ እንደተገኘ አስታውሰው፣ " ትክክል ነው የሻሸመኔውም። እንዲህ አይነት ወንጀሎች ከዕለት ዕለት እየጨመሩ ነው " ብለዋል።

" ምክያቱም በአሽከርካሪዎችና በተሽከርካሪዎች ላይ የሚደርስን ወንጀል በወንጀልነት ቆጥሮ በጸጥታ አካል አድኖ የመያዝ ሂደት አናሳ ሆኗል። አይደለም እቃውን የሰውን ሕይወት መጥፋትም በተለይ በመንግሥት ሚዲያዎች ሲዘገብ አናይም " ሲሉ አክለዋል።

" እገታና ዝርፊያ በጣም ተበራክቷል። " ያሉት እኚህ ኃላፊ " ሜዳ ላይ አስቁመው ደብድበው የሚፈልጉትን ይዘው ነው የሚሄዱት " ሲሉ የሁኔታውን አስከፊነት አስረድተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለጉዳዩ ምላሽ ለማግኘት ወደ ሻሸመኔ ከተማ ፓሊስ ያደረገው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም። #TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ቅዳሜ የመጨረሻው ገንዘቡን የመመለሻ ቀን ነው " - ንግድ ባንክ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ የወሰዱ ወይም ወደተለያየ ሂሳቦች ያስተላለፉ ግለሰቦች እስከ መጪው ቅዳሜ መጋቢት 14 ድረስ በፈቃዳቸው እንዲመልሱ አሳስቧል። ይህ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ነውም ብሏል። በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ተጠቅመው አላግባብ የወሰዱትን ገንዘብ ተመላሽ የማያደርጉ ግለሰቦች ላይ…
የኢትዮጵያ ባንኮች ማኅበር ምን አለ ?

የኢትዮጵያ ባንኮች ማኅበር መጋቢት 6 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ ተፈጥሮ የነበረውን የሲስተም ችግር ተገን በማድረግ #ተመዝብሯል ያለውን " የህዝብ ገንዘብ " አስመልክቶ መግለጫ አወጣ።

ማኅበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቴክኖሎጂ ሥርዓት ላይ ችግር በተፈጠረበት ቅፅበት የነበረውን ክፍተት እንዴት እንዳገኙ ለጊዜው ባልተረጋገጠ ሁኔታ መረጃ የደረሳቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ሌሊቱን በሙሉ በመደዋወል ከአውቶማቲክ ገንዘብ መክፈያ ማሽኖች (ATM) ገንዘብ በመውሰድና ልዩ ልዩ ገንዘብ መክፈያና ማስተላለፊያ ማዕቀፎችን በመጠቀም የራሳቸው ያልሆነውንና በሂሳባቸው ውስጥ ያልነበረን ገንዘብ " ዘርፈዋል " ብሏል።

ከዚህ ባለፈ ደግሞ ፤ " የተፈጸመውን #ምዝበራ እንደ በጎ ተግባር ሁሉ በሁሉም የማኅበራዊ መገናኛ አውታሮች በጀብድ መልክ ሲዘዋወር መመልከታችን ከፍተኛ ኃዘን አሳድሮብናል " ሲል ገልጿል።

የባንኮች ማህበሩ ፤ " ከማኅበረሰቡ በተሰበሰበ አንጡራ ገንዘብ በመንግሥት ከፍተኛ ወጪ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ወደ ከፍተኛ ተቋማት /ዩኒቨርስቲ/ የተላኩ አፍላ #ወጣቶች ኢትዮጵያዊ ከሆነው ነባር ዕምነት እና ባህል ባፈነገጠ ሥነምግባር ላይ ወድቀው መገኘታቸው ልብ የሚሰብርና አገራችን ካለባት ጊዜያዊ ችግሮች በላይ የሚያሳስብ አሳዛኝ ድርጊት ሁኖ አግኝተነዋል  " ብሏል።

ድርጊቱንና የድርጊቱን ፈጻሚ እና ተባባሪ የሆኑትን አካላት ሁሉ ማኅበሩ በጽኑ #እንደሚያወግዝው ገልጾ ፤ እነዚህን መሠል ወጣቶች በተመሳሳይ ውድቀት ውስጥ እንዳይገኙ ለመከላከል ሁሉም አካላት የሚጠበቅባቸውን ሁሉ ትኩረት ሰጥተው እንዲፈጽሙ ጥሪ አቅርቧል።

በንግድ ባንክ ላይ የተፈጠረው ችግር እና ችግሩን ተገን አድርገው በባንኩ፣ በባንኩ ደንበኞችና በኅብረተሰቡ ላይ ጉዳት ባደረሱ አካላት ላይ እየተደረገ ባለው ሕጋዊ ማጣራት እና በቀጣይነት ወደ ህግ በማቅረብ በቂ ተመጣጣኝና አስተማሪ የሆነ እርምጃ እንዲወሰድ በማድረግ ረገድ ፤ ሁሉም አባል ባንኮች አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ የኢትዮጵያ ባንኮች ማኅበር ጠቁሟል።

ሁሉ አቀፍ ትብብር ለህግና ጉዳዩ ለሚመለከታው ተባባሪ አካላት ለመስጥትም ዝግጁ መሆናቸውን አሳውቀዋል።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ደሴ ከደሴ ሪፈራል ሆስፒታል ጀርባ የሚኖሩ ነዋሪዎች ህዝብ መኃል በሚገኘው በሆስፒታሉ የቆሻሻ ማስወገጃ ምክንያት እየተሰቃቁ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ቆሻሻው በሚወገድበት ጊዜ እስከ ቤታቸው እንደሚገባ ጠቁመዋል። ይህ ሁኔታ የህፃናት ልጆቻቸውን ጤና እንዲሁም የራሳቸውን ጤና አደጋ ላይ እንደጣለውና እስከ ዛሬ ድረስ በተደጋጋሚ ቅሬታቸውን ለሆስፒታሉ ቢያቀርቡም መፍትሄ እንዳላገኙ ገልጸዋል።…
#ደሴ

“ አንድ ቀን ውሳኔ ተሰጥቶባቸው ከአካባቢ ብክለት ነጻ እንዲሆኑ ፣ ከቦታው እንዲነሱ የከተማ አስተዳደርን ውሳኔ ነው የምንጠብቀው ” - ደሴ ሆስፒታል

በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ሆስፒታል ጀርባ የሚኖሩ ነዋሪዎች ፣ በሆስፒታሉ በኩል የሚቃጠለው ቆሻሻ ወደ ቤታቸው እየገባ እንደተቸገሩ ፣ መጀመሪያ ዝም ብሎ ሜዳ ላይ ሲቃጠል እንደነበር ፣ ዘመናዊ ማስወገጃ ከተሰራ በኋላ ግን ሙሉ ወደ ግቢዎች ውስጥ እንደሚገባ ፣ በተደጋጋሚ ለችግሩ መፍትሄ ቢጠይቁም መፍትሄ እንዳላገኙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አማረዋል።

መንደሮቹ በተለይም ህፃናት ልጆች ያሉባቸው እንደሆኑ የገለጹት ቅሬታ አቅራቢዎቹ ፣ አሁን ባሉበት ሁኔታ ከመኖር ለቤታቸው የሚመጥን ካሳ ከተከፈላቸው ቦታውን ለቀው መሄድም እንደሚሻላቸው ገልጸዋል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩት #ቪዲዮም በቃጠሎው ወቅት ቆሻሻው ወደ ቤት እንደሚገባ ያስገነዝባል።

ነዋሪዎቹ ላነሱት ቅሬታ ምን ምላሽ እንዳላቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው  የሆስፒታሉ ባለስልጣን ፤ “ አሁን ያ ሁሉ አልፎ በዘመናዊ መንገድ ተሰርቶ፣ ሕጋዊ ማስወገጃ ተሰርቶለት፣ ድሮ ከነበረው ችግር የወጣበት ቀን ነው ” ብለው፣ “ ከነበረው ችግር ወጣ ነው እንጂ ችግሩ ብሶ ቀጥሏል አልልም ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ በእርግጥ #ከሕዝብ_መኖሪያ ሊወጣ ተቋሙ ግድ ነው። አሁን ግን ያለው የቆሻሻ አወጋገድ በአዎሮፓ ህብረት እና በፈረንሳይ መንግሥት ተደግፎ Almost ሰባት ወሩ ከነሐሴ መጨረሻ ጀምሮ ዘመናዊ የሆነ፣ ስታንዳርዱን የጠበቀ ማቃጠያ ተሰርቶለታል ” ነው ያሉት።

እኚሁ ባለስልጣን አክለውም ፣ “ ግን ከሰው መሀል ነው። ያ በሕጋዊ መንገድ ሲቃጠል እንደድሮው እንኳ ብናኝ እንኳ አያርፍባቸውም። ጭሱ ግን ሊሸት ይችላል ” ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ ዘመናዊ ማቀጠያ ቢሰራም ቆሻሻው እየገባ መሆኑን ቅሬታ አቅራቢዎቹ ባቀረቡት መሠረት ማብራሪያ እንዲሰጡ ለባለስልጣኗ ጥያቄ አቅርቧል።

እሳቸውም ፤ “ ጭሱ ታካሚንም ይረብሻል፣ ከሕዝብ መሀል መሆናችን ነውና ዋናው ትልቁ ችግር። ጭሱማ እንዴት ይቀራል ? ተኔሬተር ነውኮ ግን የሚጨሰው ” ነው ያሉት።

“ እነዚህ አሁን የሚጨስባቸው ጠቅላላ በካዳስከርና በከተማ ማስተር ፕላን የሆስፒታሉ ቦታዎች ናቸው ” ብለው ፣ “ አንድ ቀን ውሳኔ ተሰጥቶባቸው ከአካባቢ ብክለት ነጻ እንዲሆኑ፣ ከቦታው እንዲነሱ የከተማ አስተዳደርን ውሳኔ ነው የምንጠብቀው ፣ እንጂ አሁን ላይ እጅግ የተሻለ ነገር ነው ያለው ” ሲሉ ገልጸዋል።

አክለውም፣ “ ለምን ብትል በጣም ብዙ ተሰቃይተው አልፈዋል፣ ከዚህ አሁን ካለው በላይ። ግን ከጎኑ ያለው ሰው አይሸተውም አልልህም። ግን ከፍታው ከአራት ሜትር በላይ ሆኖ፣ ከአምስት፣ ከስድስት ሜትር በላይ ከፍ ብሎ የሚጨስ የተሰራበት ዘመን ላይ ነው ያለነው ” ብለዋል። 

“ አሁን ላይ ራሱ ሞዲፋይ አለው ተነሬተሩ። የተሰራው ማቃጠያ #ሞዲፋይ አድርገው አሁንም እዛው ላይ የሰሩት ከፍታውን ካለው ጨምረው ሊሰሩት እያሰቡ ነው። በቅርብ ቀንም ይሰራል። ሁለተኛ ደግሞ ከውጪ ያልገባ ጭስ አልባ ማቃጠያ ማሽን አለን። በቅርብ ጊዜ (ከወር በኋላ) ይደርሳል። ብዙ ነገሮችን የሚቀንስልን ” ሲሉም ተናግረዋል።

ደሴ ሆስፒታል ጀርባ የሚኖሩ በርካታ ነዋሪዎች ግን ፤ በሆስፒታሉ የቆሻሻ ማስወገጃ በየዕለቱ ስቃያቸውን እያዩ እንደሆነ ፣ ከምንም በላይ ደግሞ የትንንሽ ልጆቻቸው ጤና አደጋ ላይ በመሆኑ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጥሪ አቅርቧል።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" እኔ የማውቃቸው ብቻ 6 ሰዎች ተገድለዋል " -  የዕድሜ ባለፀጋ

በአጣዬ ከተማ እና በሰንበቴ ዙሪያ የታጠቁ ኃይሎች ሰሞኑን ከፈተቱት በተባለ ተኩስ ንጹሐን መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

አንድ የአካባቢው ነዋሪ የእድሜ ባለፀጋ ፤  “እኔ የማውቃቸው ብቻ 6 ሰዎች ተገድለዋል። ወደ ደብረ ብርሃን የተላከ ቁስለኛም አለ ” ብለዋል።

ይህ መረጃ የአንድ አካባቢ ብቻ እንደሆነ ነው ያስገነዘቡት።

“ ካራ ለጉማ አዲስ አበባ መርካቶን ነው የሚመስለው ከአጣዬ በመጡ ተፈናቃዮች። ከዛፍ ስር፣ ት/ቤት ነው የተጠለሉት ” ብለዋል።

" አጣዬ 01 ቀበሌ ዘረፋ ነበር ፤ ሰንበቴም በተመሳሳይ ፤ አጣዬ ከተማ በጣም ወድሟል” ሲሉ አስረድተዋል።

ከኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር አንድ የሰንበቴ ነዋሪ በበኩላቸው ሰሞኑን የተኩስ ጥቃት እንደነበር ተናግረው  “ የኦሮሞ ተወላጆችም በ ' ፋኖ ' ታጣቂዎች ተገድለዋል። በእኛ አካባቢ ከ5 በላይ ሰዎች ተገድለዋል ” ሲሉ ተናገረዋል።

“ በተለይ ከሳምንታት ጀምሮ ግድያ፣ ቃጠሎ ነው የሚስተዋለው። በርካታ ንጹሐን ቆስለዋል” ሲሉ ተናግረዋል።

ነዋሪዎቹ በአካባቢው ያለውን ሁኔታ በተመለከተ " ህዝቡ አለቀ፣ ወደ ማን አቤት እንበል ? " ሲሉ  ጠይቀዋል።

የአጣዬ ከተማ ከንቲባ አቶ ተመስገን ተስፋ ከቀናት በፊት ለቪኦኤ በሰጡት ቃል፣ " ሰውም አልቋል፣ ሚሊሻውም የሚችለውን ያህል ሞከረ አለቀ " ብለው ለጥቃቱ " ሸኔ" ን ተጠያቂ ሲያደርጉ፣ የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ደግሞ ለጥቃቱ " ፋኖ " ን ተጠያቂ ሲያደርግ ተስተውሏል።

ስለጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ መካሻው፣ ስልክ ባያነሱም “ ስብሰባ ላይ ሆኘ ነው ” ያሉ ሲሆን፣ የሚመቻቸውን ወቅት ስንጠይቃቸው “ አሚኮ  ላይ መግለጫ ስለሰጠን ከዛ ማግኘት ይችላሉ ” ከማለት ውጪ በድጋሚ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም።

በሰሜን ሸዋ ዞንና ኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር አጎራባች ስፍራዎች በሚገኙ የአማራና የኦሮሚያ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ነው የተባለውን ጥቃት በተመለከተ ምላሽ እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው በበኩላቸው፣ “ ስብሰባ ላይ ነኝ ” ብለዋል።

የኢፌደሪ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ፣ የኦሮሚያ ክልል ሰላምና ጸጥታና ኮሚዩኒኬሽን ቢሮዎች በተመሳሳይ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም።

በማንኛውም ሰዓት ማብራሪያ ከተገኘ ይቀርባል።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ምዕመናን #ክርስቲያናዊ_አለባበስ ለብሳችሁ እንድትገኙ እና የአቅማችሁን ያህል እድትለግሱ ጥሪ እናቀርባለን " - ማህበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን " ኑ ቸርነትን  እናድርግ " በሚል መሪ ቃል ነገ እሁድ ከቀኑ 7:00 ላይ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር በሚሊኒየም አዳራሽ ያካሂዳል። ገቢ ማሰባሰቢያው…
#Update

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን " ኑ ቸርነትን  እናድርግ " በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ይገኛል።

ገቢ ማሰባሰቢያው በሀገራችን ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ባጋጠመው ማኅበራዊ ቀውስና ድርቅ የተጎዱ ወገኖቻችንን ፣ ገዳማትና አብነት ት/ቤቶችን ለመደገፍ የሚውል እንደሆነ ተገልጿል።

በመርሃግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት  የማኅበሩ ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ስዩም ፤ " የመርሃ ግብሩ ዋነኛ ዓላማ ባለን አቅም ሁሉ ለወገን መድረስ ነው " ብለዋል።

" ረሃብ ጊዜ አይሰጥም " ያሉት የማህበሩ ሰብሳቢ " በውጭ ድርጅቶች ፣ በመንግስትና በሌሎችም የተለያዩ አካላት ብዙ እርዳታዎች ይደረጋሉ (የምግብም የአይነትም) በተለይ ግን ገዳማትና አብነት ት/ቤቶች ብዙ ጊዜ ትኩረት አያገኙም " ብለዋል።

" እነዚህን ክፍተቶች እና ጉድለቶች መሙላት አለብን " ሲሉ አስገንዝበዋል።

" አሁን ላይ በየቦታው ያሉት መፈናቀሎች ፣ በየቦታው ያሉ የረሃብ ችግሮችን በማሰብ ማህበረ ቅዱሳን ሌሎች አገልግሎቶችን ገቶ መጀመሪያ ነፍስን የማዳን፤ ህይወትን የመታደግ ስራ ይቀድማል ብሎ እየሰራ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ሁሉን ማድረግ የምንችለው ስንኖር ነው " ያሉት ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ " እኛ በልተን እያደርን ሌሎች ወገኖቻችን በረሃብ እና ጥማት መሞት ስለሌለባቸው ' ኑ ቸርነትን እናድርግ ! ' በሚል በዚህ በታላቁ ዐብይ ጾም ወቅት ዝግጅቱ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።

ዛሬ ሚሊኒየም አዳራሽ መገኘት ያልቻሉ ምዕመናን በየቤታቸው ሆነው በማህበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም የሂሳብ ቁጥሮች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648 ፣ አሃዱ ባንክ 0025393810901 ፣ ወጋገን ባንክ 0837331610101 ፣ አቢሲንያ ባንክ 37235458 ፣ አዋሽ ባንክ 01329817420400 ድጋፍ ማድረግ ይቻላሉ ተብሏል።

ፎቶ ፦ ከማኅበረ ቅዱሳ ቴሌቪዥን

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሊዝ #አዲስአበባ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ መሬትን በሊዝ ለማስተላለፍ 2ኛ ዙር ጨረታ አውጥቷል። መሬትን በሊዝ የማስተላለፍ ተግባር ለአራት ዓመታት ከተቋረጠ በኋላ ግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ.ም መጀመሩ ይታወሳል፡፡ 2ኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታም ረቡዕ ሚያዝያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም መውጣቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቢሮና ከአዲስ ልሳን ጋዜጣ መረጃውን አግኝቷል። …
በአዲስ_አበባ_2ኛው_ዙር_የመሬት_ሊዝ_ጨረታ.pdf
5.3 MB
በአዲስ አበባ ከተማ የ2ኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ

የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በአራዳ ክ/ ከተማ (ፒያሳ) በዓድዋ ድል መታሰቢያ አካባቢ በኮሪደር ልማት ምክንያት የፀዱ ቦታዎችን ጨምሮ ፦
- በንፋስ ስልክ ላፍቶ፣
- በኮልፌ ቀራንዮ፣
- በአራዳ፣
- በአቃቂ ቃሊቲ፣
- በየካ፣
- በቦሌ፣
- በአዲስ ከተማ፣
- በቂርቆስ፣
- በጉለሌ
- በልደታ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ለተለያዩ አገልግሎቶች የተዘጋጁ የልማት ቦታዎችን በጨረታ አወዳድሮ በሊዝ ማስተላለፍ እንደሚፈልግ አሳውቋል።

(ዝርዝር የጨረታው መረጃ በPDF ተያይዟል - ይመልከቱ)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ የጨረታ መረጃ ባለቤት አዲስ ልሳን መሆኑን ያሳውቃል።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia