TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ወጋገን_ባንክ

በአምስት የተለያዩ ቋንቋዎች የቀረበውን ደህንነቱ የተጠበቀ ፈጣን እና አስተማማኝ የወጋገን ሞባይል መተግበሪያ አሁኑኑ ከአፕስቶር ወይም ፕሌይስቶር በማውረድ ስልክዎ ላይ ይጫኑ፣ በቀልጣፋ አገልግሎታችን ህይወትዎን ያቅልሉ!

ስልክዎ ባንክዎ

ለተጨማሪ መረጃ በ866 ነፃ የስልክ መስመር ወደ ደንበኞች ግንኙነት ማዕከል ይደውሉ፣ ይስተናገዱ::

Download now:

Android:https://play.google.com/store/apps/details?id=com.act.wegagen&hl

IOS:https://apps.apple.com/in/app/wegagen-mobile/id6472656143

#WegagenBank #WegagenMobile #MobileBanking

Follow us and get more information...

https://linktr.ee/WegagenBank
#ነእፓ

በሀገሪቱ ያሉ የእርስ በርስ ግጭቶችን ለማስቆም “ ኢትዮጵያ በልጆቿ ትታረቅ ! ” በሚል የነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ የእርቅ እና የሰላም ሀሳብ ይዞ መቅረቡን አሳውቋል።

ፓርቲው በላከልን መግለጫ ፤ ሀገራችን በታሪኳ በርካታ በእርስ በእርስ ግጭቶችን ማስተናጓን ገልጿን።

ለ2 አመታት በትግራይ፣ በአማራ እና አፋር ክልሎች የተካሄደው ጦርነት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወገኖቻችንን ህይወት መቅጠፉን አመልክቷል።

አሁንም በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች የቀጠለው የወንድማማቾች ጦርነት የወገኖቻችንን ህይወት እየቀጠፈ እንደሚገኝ ገልጿል።

በየአካባቢው በተለኮሱ ጦርነቶች ሳቢያ ፦

- በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ውድ ህይወታቸውን እንዳጡ፣ አካላቸው እንደጎደለ፤

- እድሜ ልካቸውን ያፈሩት ንብረት እና የሀገራችን ኢትዮጵያ አንጡራ ሀብትም እንደወደመና እየወደመም እንደሚገኝ ገልጿል።

በእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ህጻናት ያለ አሳዳጊ፣ አረጋውያን ያለ ጧሪ ፣ አያሌ ኢትዮጵያውያን ለርሀብ፣ ለእንግልት፣ ለስደት እና ለሞት መዳረጋቸውን ገልጿል።

በየአካባቢው የተከሰቱ ግጭቶች ማህበራዊ ግንኙነታች እንዲበጣጠስ፣ በዜጎች መካከል ጥርጣሬ እንዲነግስ፣ ማህበራዊ ትስስራችን እንዲላላ፣ ጥላቻ፣ እልህ፣ በቀል እንዲስፋፋ፣ ስጋት እና ጭንቀት በዜጎች ልቦና እንዲሰፍን ማድረጋቸውንም አመልክቷል።

ነእፓ፤ ጦርነት መቼም ቢሆን የፖለቲካ ልዩነቶችን ለመፍታት የተሻለ አማራጭ አይሆንም ፤ የእርስ በእርስ ጦርነት አሸናፊና ተሸናፊ የሌለው የመጨረሻ ውጤቱ ሞት፣ ስደት፣ ስቃይ፣ ሀዘን ፣ የሀገር ድቀትና መፍረስ ነው ብሏል።

ላለፉት ዓመታት ሰላም እንዲሰፍን በተለያዩ መንገዶች ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን የሚገልጸው ነእፓ ሀገራችንን ለክፉ ችግር፣ ህዝባችንን ማባሪያ ለሌለው ሰቆቃ የዳረጉ ጦርነቶች እንዲቆሙ “ #ኢትዮጵያ_በልጆቿ_ትታረቅ ” በሚል ስያሜ አዲስ የእርቅ እና የሰላም ሀሳብ መንደፉን ይፋ አድርጓል።

ዋናው ዓላማ በመንግስት እና ከመንግስት ጋር ነፍጥ አንግበው በሚፋለሙ ማናቸውም ኃይሎች መካከል በሀገር ሽማግሌዎች፣ በኃይማኖት አባቶች እና በሌሎች ታዋቂ ስብእናዎች አማካኝነት እርቅ ማውረድ እንደሆነ ገልጿል።

በቀጣይ ሂደቱን በተመለከተ ዝርዝር መረጃዎች ይሰጣሉ ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፑቲን ቭላድሚር ፑቲን ለቀጣይ 6 ዓመታት ሩስያን መምራት የሚያስችላቸውን የምርጫ ውጤት ማስመዝገባቸው ተነገረ። ሩስያን በፕሬዜዳንትነት እየመሩ የሚገኙት የቀድሞው የKGB ሰላይ ቭላድሚር ፑቲን በሀገራቸው የተካሄደውን የፕሬዜዳንታዊ ምርጫ በከፍተኛ ብልጫ ማሸነፋቸውን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ባለፉት 3 ቀናት በመላ ሩስያ ህዝቡ ድምፅ ሲሰጥ ቆይቷል። የ71 ዓመቱ ፑቲን " ጠንካራ ተቀናቃኝ…
#ፑቲን

አሜሪካ ዛሬ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤቷ በኩል በሰጠችው መግለጫ ፤ የሩስያ ምርጫን " ኢ-ዲሞክራሲያዊ ነው " ስትል አጣጥላለች።

በከፍተኛ ልዩነት አሸንፈዋል የተባሉትን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንንም " እንኳን ደስ አልዎት " አንላቸውም ብላለች።

ሩስያን እስከ 2030 ለመምራት በበላይነት ፕሬዜዳንታዊ ምርጫውን ያሸነፉት ቭላድሚር ፑቲ ትላንት ድላቸውን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ የአሜሪካን ዴሞክራሲ ወርፈዋል።

ምን አሉ ?

ቭላድሚፕ ፑቲን ፦

" ያካሄድነው ምርጫ ከአሜሪካ በላይ ተዓማኒ እና ግልጽ የሆነ ዓላማ ያለው ነው።

በአሜሪካ በፖስታ አማካይነት ድምጽ እንደሚሰጡት አይደለም። እዛ (አሜሪካ) ድምጽ በ10 ዶላር መግዛት ይቻላል።

የምርጫ ስርዓታቸው ኢ-ዴሞክራሲያዊ ነው።

ዓለም ሁሉ እዚያ እየሆነ ባለው ነገር ይስቃል (በአሜሪካ ዴሞክራሲ) " ብለዋል።

ፕሬዚዳንት ፑቲን ፕሬዜዳንታዊ ምርጫውን በከፍተኛ ብልጫ ማሸነፋቸው ተከትሎ ፦
- ቻይና
- ህንድ
- ኢራን
- ሰሜን ኮሪያ
- ቬንዙዌላ #የደስታ መልዕክት ሲያስተላልፉ እነ አሜሪካ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ዩክሬን፣ ዩናይትድ ኪንግደም እና ሌሎች አጋሮቻቸው ምርጫውን ኢ-ዴሞክራሲያዊ ሲሉ እያጣጣሉት ይገኛሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ሲቢኢ #ዩኒቨርሲቲዎች #ኦዲት

" ባንኩ ላይ የሳይበር ጥቃት ደርሷል፤ ዝውውሩም አይታወቅም ብለው አስበው ነው ያደረጉት " - አቶ አቤ ሳኖ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዜዳንት አቶ አቤ ሳኖ በዩኒቨርሲቲዎች አካባቢ ስለነበረው የመጋቢት 6 ለሊት የገንዘብ ዝውውር እና አጠቃላይ ወጭ ስለተደረገው / አሁን ስለተመለሰው የገንዘብ መጠን ምን አሉ ?

አቶ አቤ ሳኖ ፦

" የተቋረጠውን አገልግሎት ካስጀመርን በኃላ ወደ ግብይቶች ምርመራ ነው የገባነው።

በዛ ያለ ግብይት ያደረጉትን ለይተናቸው የፍትሕ አካላት እንዲያውቁት አድርገናል። በብዛት በዛ ያለ ቁጥር ያለው እጅግ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ #በዩኒቨርሲቲዎች አካባቢ ነው።

ተማሪዎቹ (የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ) ያሰቡት ባንኩ ላይ የሳይበር ጥቃት ደርሷል ብለው ነው። ስለዚህ የሚደረገው ግብይት (ወጭ / ዝውውር) አይታወቅም ብለው ነው ያደረጉት።

አሁን ላይ ግን ግብይቱ እንደሚታወቅ ሲያውቁ የወሰዱትን ገንዘብ እየመለሱ ነው ያሉት። አሁንም እንዲመልሱ ነው የምንፈልገው።

የወሰዱትን ገንዘብ ከመለሱ ወደ ክስ አንሄድም። የማይመልሱ ከሆነ ግን የህግ እርምጃ እንወስዳለን።

ዝርዝር ጉዳዩ (ከገንዘብ ዝውውር/ወጭ የተደረገ/የተመለሰ) ኦዲት ተደርጎ ሲያልቅ ይቀርባል።

የኦዲት ሂደቱ ስላላለቀ በዚህ መካከል ሌሎች ነገሮችን ማንሳት ከፋይናንሻል ኦዲት አካሄድ ጋር የሚሄድ ስላልሆነ አንዳንድ የህጋዊ እርምጃዎችም ሊከተሉ ስለሚችሉ ጥንቃቄ ስለሚፈልግ ነው። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለ2016 ዓ/ም አዲስ ገቢ ተማሪዎች ጥር 21 ቀን 2016 ዓ/ም ያደረገውን ጥሪ ባላወቁት ምክንያት አራዝሞት እንደነበር፣ ይሁን እንጂ ከዚያ ወዲህም “ኑም” ሆነ “አትምጡ” ባለማለቱና የትምህርት ጊዜው እያገፋ በመሆኑ ጭንቀት ውስጥ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ " ዩኒቨርሲቲው የሚጠራም ከሆነ የማይጠራም ከሆነ አቋሙን ያሳወቀን " የሚል ጥያቄ አቅርበው ነበር። ቲክቫህ ኢትዮጵያ…
" ስለ ትውልዱ ግድ ይለናል የምትሉ ኃላፊዎች መፍትሄ ስጡን " - ተማሪዎቹ

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፤ " መፍትሄ የሚሰጠን አጥተን ያለ ትምህርት ቤታችን ቁጭ ብለናል ፤ ጊዜያችንም እየተቃጠለ ነው " ሲሉ አማረዋል።

የባህር ዳር ዩንቨርሲቲ የ2016 ዓ/ም የ1ኛ ዓመት እና የሬሚድያል ተማሪዎች ወደ ግቢ እንዲገቡ ጥሪ ተደርጎላቸው በኃላም መራዘሙ ይታወሳል። ነገር ግን እስካሁን ምንም አይነት ጥሪ አልተደረገላቸውም ፤ ተማሪዎቹም የትምህርት ገበታቸው ላይ መገኘት አልቻሉም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የነዚህን ተማሪዎች ጉዳይ እየተከታተለ ተደጋጋጋሚ የመረጃ ልውውጥ ማድረጉ ይታወሳል።

አሁንም ተማሪዎቹ በሰጡት ቃል ፤ ሌላ ቦታ ያሉ እኩዮቻቸው ትምህርታቸውን እየተከታተሉ፣ እነሱ ያለ ትምህርት እድሜያቸው እየሄደ ፣ የራሳቸው መፍትሄ እንዳይወስዱም ጊዜው እየገፋ መሄዱን በመግለፅ ቁርጥ ያለ መፍትሄ እንዲሰጣቸው በድጋሚ ጠይቀዋል።

" የሚጠሩን ከሆነ ይጥሩን ፤ የማይጠሩን ከሆነም ይንገሩን ፤ አልያም ትምህርት ሚኒስቴር ወደ ሌሎች ተቋማት ይመድበን እየደረሰብን ያለው የስነልቦና ጫና ከባድ ነው " ብለዋል።

ስለ ትውልዱ ግድ ይለናል የሚሉ ኃላፊዎች መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ያነጋገራቸው አንድ የዩኒቨርሲቲው አካል ተቋሙ ተማሪዎችን ያልጠራበት ምክንያት በአካባቢው ካለው ደህንነት ጋር በተያያዘ መሆኑን መግለፃቸው ይታወቃል።

ተቋሙ ተማሪ አልጠራም ማለት እንደማይችል ፤ ከዛ ይልቅ አንፃራዊ ሰላም ሲኖር አስገብቶ በ45 ቀን 1 ሴሚስተር አስተምሮ ሊያካክሰው እንደሚችል (ልክ ከአሁን በፊት በኮሮናና ጦርነት እንደተደረገው) ተናግረው ነበር።

ከዚህ ቀደም " በአካባቢው ተማሪዎችን ለመጥራት አስቻይ ሁኔታ ከሌለ ለምን የልጆቹ ጊዜ ይቃጠላል አመቱም እያለቀ ስለሆነ ወደ ሌላ ተቋም አይመደቡም ? " የሚል ጥያቄ ለማቅረብ በተደጋጋሚ ትምህርት ሚኒስቴርን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#SamoaAgreement ከወር በፊት ሀገራችን #ኢትዮጵያን ጨምሮ አጠቃላይ 79 የአፍሪካ እና የካረቢያንና ፓስፊክ ሀገራት / 48 ከአፍሪካ፣ 16 ከካረቢያን፣ 15 ከፓስፊክ / ሳሞአ ላይ አንድ ስምምነት ተፈራርመዋል። የተፈረመው ስምምነት " #የአፍሪካ ፣ #የካረቢያን እና #የፓስፊክ ሀገራት ከአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ጋር የሚያደርጉት የንግድ እና ኢኮኖሚ ትብብር " የሚል ነው። ስምምነቱ 22…
#Update

የሳሞአው ስምምነት ከምን ደረሰ ?

ኢትዮጵያ ከ79 ሀገራት ጋር የፈረመችው የሳሞዓ ስምምነት እስካሁን ለፓርላማ አለመቅረቡን “ ስለ ኢትዮጵያ ዝም አንልም ትውልዱን ከግብረሰዶም እንታደግ ” ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

ኢትዮጵያን ጨምሮ አጠቃላይ 79 የአፍሪካ እና የካረቢያንና ፓስፊክ ሀገራት (48 ከአፍሪካ፣ 16 ከካረቢያን፣ 15 ከፓስፊክ) ሳሞአ ላይ አንድ ስምምነት መፈራረማቸው ከወራት በፊት ተዘግቦ ነበር።

የተፈረመው ስምምነት " የአፍሪካ፣ የካረቢያን እና የፓስፊክ ሀገራት ከአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ጋር የሚያደርጉት የንግድ እና ኢኮኖሚ ትብብር " መሆኑ፣ ምስምነቱ 22 ዓመታትን የዘለቀ " የኮቶኑ ስምምነት " ቀጣይ እንደሆነ በወቅቱ መብራራቱ አይዘነጋም።

ይህንኑ ስምምነት በበርካታ ሀገራት ጥያቄ አስነስቶ ነቀፌታ ሲያስተናግድ የተስተዋለ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ የሚገኙ የዘርፉ ተቋማት በበኩሉቸው ስምምነቱን " ትውልድ ገዳይ " ሲሉ አውግዘውታል።

“ ስለ ኢትዮጵያ ዝም አንልም ትውልዱን ከግብረሰዶም እንታደግ ” የተሰኘው ማኀበር፣ ኢትዮጵያ ከ79 አገራት መካከል አንዷ ሆና የሳሞዓ ስምምነትን እንደፈረመች፣  ስምምነቱ ግብረሰዶማዊነትን ማስፋፊያ ሃሳብ መያዙን በአንክሮ በማስረዳት፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ውድቅ እንዲደረግ (እንዳይጸድቅ) ጠይቆ ነበር።

ይህን ተከትሎም ጉዳዩ ከምን ደረሰ ? ፓርላማ ላይ ቀርቦ እንዳይጸድቅ ተደረገ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለማኀበሩ ፕሬዚዳንት ሊቀ ትጉሃን መምህር ደረጀ ነጋሽ (ዘወይንዬ) ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፣ “ አላቀረቡትም እነርሱም ቁጭ ብለዋል። ግን ብዙዎቹን አናግረናቸዋል፣ ብዙዎቹ አልወደዱትም። እነርሱም ፈርተው ነው እስካሁን ያላቀረቡት ” ብለዋል።

ያለውን ሂደት በተመለከተ ባስረዱበት አውድ ፥ “ በዚሁ ዙሪያ እኛም የግንዛቤ ማስጨበጫ እየሰጠን ነው ለተለያዩ መ/ቤቶች። ከሃይማኖት ተቋማት ጋር አወራን፣ ከሌሎቹም የሃይማኖት አባቶች አናገርን እነርሱም አላቀረቡትም ” ሲሉ አስረድተዋል።

መምህር ደረጀ ከዚህ በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ማብራሪያ፣ የስምምነቱን ከባድ ምስጢራዊነትና እንድምታ በGender፣ በጾታ ስርዓተ ትምህርትና በሌሎች ነጥቦች እያጣቀሱ ስምምነቱ በሰብዓዊ መብት ሽፋን ግብረ ሰዶማዊነትን ማስፋፊያ መንገድ መሆኑን፣ “ ፍጹም የሆነ ትውልዱን ለ20 ዓመታት ታሳሪ የሚያደርግ የሞት ውል ነው ” ብለውታል።

ማኀበራቸው በወቅቱ በሰጠው መግለጫም
፣ “ ዘመናዊ ቅኝ ግዛትና ድምጽ አልባው ትውልድ ገዳይ የግብረሰ ዶማዊያን ድርጊትን እንቃወማለን ” ነበር ያለው።

ከዚህ ማህበር በተጨማሪ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ስምምነቱን በመቃወም በህ/ተ/ም/ቤትም ስምምነቱን ባለማፅደቅ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርቦ ነበር። ይህ መግለጫ ከወጣ በኃላ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለዶቼ ቨለ በሰጠው ቃል ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚባለውን አይነት ስምምነት አፀድቃለሁ ብሎ እንዳልፈረመ ፤ የሃይማኖት ተቋማት የስራ ኃላፊዎችም ያላቸው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ምላሽ ሰጥቶ ነበር።

መረጀው የተዘጋጀው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ጥያቄ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ ምን ነበር ? ከትግራይ ወደ አ/አ የመጡ የማህበረሰቡ ተወካዮችና እዚህም ያሉ ተወላጆች ከጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር በነበራቸው ቆይታ ፤ የትግራይ ህዝብ ከማንም ህዝብ ጋር  መጋጨት እንደማይፈልግ ገልጸው ፓለቲከኞችም ልጓም ማበጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በአፅንኦት በጦርነቱ ከቄያቸው የተፈናቀሉ ወደ ቦታቸው…
#Update

" የትግራይ ጡረተኞች ክፍያው እንዲፈፀምላቸው ተወስኗል " - ዶ/ር እዮብ ተካልኝ

በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ምክንያት የጡረታ ገንዘብ ያልተከፈላቸው ጡረተኞች፤ በፖለቲካ ውሳኔ መሰረት ደሞዝ እንዲከፈላቸው መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታና የጡረታ ፈንድ የቦርድ አባል ዶክተር እዮብ ተካልኝ ማሳወቃቸውን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።

ዶ/ር እዮብ ፤ የጡረታ መዋጮ ባልተሰበሰበበት ሁኔታ ጡረታ እንዲከፈል የሚፈቅድ አሰራር አለመኖሩን ጠቅሰው፤ ውሳኔው ፖለቲካዊ ስለመሆኑ ተናግረዋል።

በዚህም ከፕሪቶሪያው ስምምነት በፊት ክፍያ ተቋረጦባቸው የነበሩ ጡረተኞች፤ በሚቀጥሉት ሳምንታት ክፍያ ይፈፀምላቸዋል ብለዋል። አሰራሩ በመንግስት ተቋማት እና በግል ድርጅቶች ይሰሩ የነበሩ ጡረተኞችን እንደሚመለከት ጠቁመዋል።

ከትግራይ ጡረተኞች ክፍያ ጋር በተያያዘ ተደጋጋሚ ጥያቄ ሲነሳ እንደነበር ጠረተኞችም ሰላማዊ ሰልፍ እስከመውጣት መድረሳቸው ይታወሳል።

ከቀናት በፊት ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከትግራይ ክልል ከመጡ የህዝብ ተወካዮች ጋር ባደረጉት ውይይት፤ የጡረተኞች የደሞዝ ክፍያ አልተፈጸመም የሚል ቅሬታ ቀርቦ ነበር።

ጠ/ሚኒስትሩ ፤ " ከሚመለከታቸው የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር ተነጋግሬ በአጭር ጊዜ ምላሽ ይሰጣል " የሚል ምላሽ ሰጥተው እንደነበር ይታወሳል።

በተደረሰው ፖለቲካዊ ውሳኔ በጦርነቱ ምክንያት ያለተከፈለ የጡረተኞች ደሞዝ ተሰልቶ ይከፈላቸዋል ተብሏል።

@tikvahethiopia
" የዘረፋ ሙከራ እየተደረገ ነው ተጠንቀቁ " - ንግድ ባንክ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደንበኞቹ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳሰበ።

ባንኩ ፤ " አጭበርባሪዎች ሰሞኑን ከሲስተም ጋር ተያይዞ የተፈጠረውን ችግር እንደ አጋጣሚ ለመጠቀም ሙከራ እያደረጉ ነው " ብሏል።

አጭበርባሪዎች በአብዛኛው ከባንክ የደወሉ በማስመሰል “ የተዘጋ ሂሳብችሁን እንክፈትላችሁ” ፤ “ሂሳባችሁ እንዳይዘጋ የምንልክላቹሁን ኮድ አስገቡ” የሚል የማጭበርበሪያ ዘዴ በመጠቀም የዘረፋ ሙከራ እያደረጉ ነው ሲል ገልጿል።

ባንኩ ስልክ ደውሎ ስለ ሂሳብ መረጃ የሚጠይቅበት፣ ሂሳብ የሚከፍትበትም ሆነ የሚዘጋበት አሰራር እንዲሁም ደንበኞች እንዲጠቀሙበት የሚልከው  ምንም አይነት ኮድ እንደሌለ አስገንዘቧል።

ማንኛውም የባንኩ ደንበኛ መሰል ሁኔታ ሲገጥመው ምንም አይነት እርምጃ ከመውሰድ እንዲቆጠብ አሳስቧል።

በሌላ በኩል ፤ ከሰሞኑን በነበረው ሁኔታ ምንም ባላወቅንበት አካውንታችን ታግዷል  በሚል በርካታ ሰዎች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ።

ለአብነት ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ደንበኞች ፤ " በዕለቱ ምንም ዝውውር ባላደረግንበት፣ ገንዘብ ባላወጣንበት፣ ባላክንበት ሁኔታ አካውንታችን ታግዷል የሚል መልዕክት የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያችን ላይ እያየን ነው " ብለዋል።

ችግሩ ተጣርቶ በፍጥነት እንዲፈታም ጥሪ አቅርበዋል።

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

ለአሜሪካ የቪዛ ክፍያ የአቢሲንያ ሞባይል ባንኪንግ ካሉበት ሆነው ይጠቀሙ።

ሊንኩን በመጠቀም መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ!

ለአንድሮይድ ስልኮች https://play.google.com/store/apps/details?id=com.boa.boaMobileBanking&hl=en&gl=US

ለአፕል ስልኮች https://apps.apple.com/us/app/boamobile/id6463218765

ለሁዋዌ ስልኮች https://appgallery.huawei.com/app/C110106115
ይጋብዙ፤ ይሸለሙ!

ቴሌብር ሱፐርአፕ መተግበሪያ ላይ “ይጋብዙ ይሸለሙ” የሚለውን አማራጭ በመጠቀም በአጭር መልዕክት ወይም በማኅበራዊ ሚዲያ መተግበሪያውን ያጋሩ፤ ወዳጆችዎ ግብይት ሲጀምሩ እርስዎ የ10 ብር ስጦታ ያገኛሉ፡፡

የቴሌብር ሱፐርአፕ መተግበሪያ በስልክዎ ከሌለ ከ http://onelink.to/fpgu4m ያውርዱ

ቴሌብር - ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተጠንቀቁ ⚠️ ከኦንላይ ዘራፊና አጭበርባሪዎች እራሳችሁን ጠብቁ። ነገሩ እንዲህ ነው ... ገንዘባቸውን ኦንላይን ተጭበርብረው የተበሉ ግለሰቦች መጀመሪያ በማያወቁት የውጭ ሀገር ስልክ ቁጥር በ #ዋትስአፕ / በ #ቴሌግራም መልዕክት ይደርሳቸዋል። ስልካቸውን / username እንዴት እንደሚያገኙት ባይታወቅም። የሚደርሳቸው መልዕክት " ጥሩ የስራ እድል እንደሆነ ፣ በትንሽ ስራም ብዙ ትርፍ እንደሚያገኙ…
#ScamAlert

በርካታ ሰዎች አሁንም በኦንላንይን #አጭበርባሪዎች ገንዘባቸውን የተጭበረበሩ ይገኛሉ።

ዛሬ እንዲሁም ትላንትና " #ተዘረፍን " ሲሉ መልዕክት የላኩ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በዋስትስአፕ እና በቴሌግራም  ያነገሯቸው ሰዎች ፤ " ቀለል ያለ ስራ ስሩና ትርፋማ ሁኑ " በማለት ከ150,000 ብር በላይ እንዲልኩላቸው ካደረጉ በኃላ ሰዎቹ የውሃ ሽታ ሆነዋል።

" በእኛ የደረሰ በናተ እንዳይደርስ ለማንም የማታውቁት ሰው መልዕክት አትመልሱ ፤ እንዲሁ ቁጭ ተብሎ ምንም ሳይደክሙ ብቻ ትርፋማ መሆን አይቻልምና ገንዘባችሁ እንዳትበሉ " ብለዋል።

በድጋሚ ማኛውም የማታውቁት ሰው በቴሌግራም ፣ ዋትስአፕ፣ ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም ላይ " ትርፋማ ስራ እናሰራችሁ " ወይም ሌላም መልዕክት ሲልክላችሁ አትመልሱ።

ሌላው የተለያዩ ኤሌክትሮኒክስ እና ሌሎች የመገልገያ እቃዎችን " #በርካሽ እንሸጥላችኃለን ቅድሚያ የሂሳቡን ግማሽ ላኩ " ለሚሏችሁም ሰዎች መልስ አትስጧቸው / እቃውን ይላኩና ገንዘቡን ላኩላቸው።

አንድ የቤተሰባችን አባል " አዲሱን አይፎን 15 ስልክ ከአሜሪካ በርካሽ እንልክልሃለን ቅድሚያ ግን ግማሹን አስገባ " በማለት 50 ሺህ ብር ካስላኩት በኃላ አድራሻቸውን አጠፋፍተዋል።

ከዚህም ባለፈ ደግሞ ወደ ውጭ ሀገራት ለትምህርት ለስራ እንላካችሁ የሚሉም በዝተዋልና አድራሻሸውን ፣ ህጋዊናታቸውን አጣሩ። በቅድሚያ ምንም አይነት ክፍያ እንዳትከፍላቸው። " ቅድመ ክፍያ የለውም " ካሉም በኃላ በተለያየ መንገድ ጉዳይ መጨረሻ በሚል የሚበዘብዙ አሉና ተጠንቀቁ።

@tikvahethiopia