TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዋግኽምራ " ድርቁ በጣም እየባሰ ነው። መታከም ያለባቸው ህፃናት ለተከታታይ 2 ወራት ምንም አልተደረገላቸውም" - ዋግኽምራ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ በአማራ ክልል የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ ኃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ በዞኑ ስላሉ አሳሳቢ ጉዳዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ? - ድርቁ በጣም #እየባሰ ነው። ባለፈው ጥናት ካጠናን በኋላ ሊደረግ የሚገባው ግን ያልተደረገ በጣም በስፋት…
#አማራ #ዋግኽምራ

በአማራ ክልል በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ሰሃላ ሰየምትን ጨምሮ ድርቅ በተከሰተባቸው ሌሎችም ወረዳዎች ላይ እንስሳት በመኖ እጥረት #እየሞቱ ፣ አካባቢያቸውን ለቀው #እየተፈናቀሉ መሆኑን አስተዳደሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።

የአስተዳደሩ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምህረት መላኩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፣ ከ10,000 በላይ የተለያዬ እንስሳት በውሃና በመኖ እጥረት ሞተዋል።

በአበርገሌ፣ በሮቢና፣ በበለቃ በላይኛው ተከዜ ተፋሰስ በተለይ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ነጻ ያልወጡ፣ መንግሥት የማይቆጣጠራቸው ቀበሌዎች ላይ ሰፋ ያለ ችግር እንዳለ ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ በድርቁ ቀጥተኛ ጉዳት እየደረሰባቸው ያሉ እንስሳትን በሚመለከት ኃላፊው ፤ በሦስቱም ወረዳዎች ፦
* ሰሃላ ሰየምት፣
* ዝቋላ፣
* አበርገሌ በጣም የቅድሚያ ቅድሚያ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ተብለው የለተለዩ ወደ 791,000 አካባቢ እንደሆኑ አስረድተዋል።

ከ791,000ዎቹ ውስጥ በተለይ ሰሃላ ሰየምት ወረዳ ላይ ያሉት ክርቲካሊ የዕለትም አቅርቦት ስላጡ 171,000 ወደ ደሃና ወረዳ ተፈናቅለው እንዲሄዱና ተጠግተው ለጊዜው እንዲቆዩ መደረጉን ተናግረዋል።

" ይህን ይህል ተፈናቅሎ ከሄደ ቀሪው 620,000 ደግሞ ከዚያው #እየተላወሰ ነው ያለው " ሲሉ አክለዋል።

ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-24

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ   ዛሬ ጥር 13/2016 ዓ.ም በትግራይ በርካታ ከተሞች  ሰላማዊ ሰልፎች መካሄዳቸው ተሰምቷል። ሰልፎቹን ያካሄዱት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ናቸው ተብሏል። ሰላማዊ ሰልፈኞቹ የተደረጉት ፦ * በሸራሮ * በሽረ * በአክሱም * በዓድዋ * በተምቤን * በዓዲግራት * በጉሎመኸዳ * በኢሮብ * በመቐለና ልሎች ከተሞች ሰሆን ከጠዋት ጀምሮ በተካሄደ ሰልፍ የተለያዩ መፈክሮች ሲሰሙ ነበር።…
#ትግራይ

" ... እዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የወደቃችሁት ሥራችንን መሥራት ስላልቻልን ነው " - አቶ ጌታቸው ረዳ

ዛሬም የትግራይ ተፈናቃዮች ሰልፍ መቀጠሉ ተሰምቷል።

ከተለያዩ የትግራይ አከባቢዎች ተፈናቅለው በመቐለ የተለያዩ የመጠለያ ጣብያዎች የሚኖሩ ተፈናቃዮች ካለፈው የቀጠለ ሰልፍ ማካሄዳቸው ተነግሯል።

ሰልፈኞቹ ዛሬ ጥር 15/2016 ዓ.ም በመቐለ ዋና መንገዶችና አደባባዮች ባካሄዱት የተፈቀደ ሰልፍ ፤ " መሶባችንና ሆዳችን ባዶ ሆኖ ኬሻና ፕላስቲክ ለብሰን የመከራ ህይወት መኖር ይብቃን። ድምፃችን ይሰማ ወደ ቤታችን መልሱን " ሲሉ ድምፅ አሰምተዋል።

በተጨማሪ ሰልፈኞቹ ፤
* ሰርተው መኖር እንዲችሉ ወደ መሬታቸው እንዲመለሱ፣
* የፕሪቶሪያ ውል ሙሉ በሙሉ እንዲተገበት ፣
* በትግራይ ውስጥ ያሉ ኃይሎች ከመሬታቸው እንዲወጡ፣
* በተፈናቃዮች ላይ የሚፈፀመው በደል እንዲቆም
* ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ጠይቀዋል።

" የሚታረስ መሬት እያለን በረሃብ እያለቅን ነው " ያሉት ሰልፈኞቹ ፤ " በእርዳታ እጦት እያለቅን ነው፤ ምግባረሰናይ ድርጅቶች ድረሱልን " ብለዋል።

የተፈናቃዮቹ ጥያቄ በፅ/ቤታቸው ደጃፍ ደረስ በመምጣት ያዳመጡትና የተቀበሉት የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ እንዳሉት ፤ " ስቃይችሁ ስቃያችን ነው። ወደ መሬታችሁ እንድትመለሱ ከሁሉም ስራዎቻችን በላይ ትኩረት ሰጥተን እንሰራለን " ብለዋል።
 
ተፈናቃዮቹ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ላለመለሳቸው አንዱ ተጠያቂ አስተዳደራቸው እንደሆነ አምነዋል።

" እዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የወደቃችሁት ሥራችንን መሥራት ስላልቻልን ነው " ያሉት አቶ ጌታቸው አስተዳደራቸው የበኩሉን ኃላፊነት እንደሚወስድ ተናግረዋል።

አቶ ጌታቸው የፌዴራል መንግሥትም ስራውን እንዳልሰራ ሳይናገሩ አላለፉም።

ጥር 13/2016 ዓ.ም በሸራሮ ፣ ሽረ፣  አክሱም ፣ ዓድዋ ፣ ተምቤን ፣ ዓዲግራት ፣ ጉሎመኸዳ ፣ ኢሮብ ጨምሮ በበርካታ ከተሞች ተመሳሳይ ሰልፍ መካሄዱ ይታወሳል።

መረጃው የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
                                       
@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Grade12NationalExam

በ2016 የ12ኛ ክፍል ፈተና የሥነዜጋ እና ሥነምግባር ትምህርት የማይሰጥ ሲሆን ባለፉት ዓመታት ሳይሰጥ የቆየው ኢኮኖሚክስ ዘንድሮ ይመለሳል።

የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር እሸቱ ከበደ ከቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ጋር በነበራቸው ቆይታ ምን አሉ ?

" በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ምክንያት 12ተኛ ክፍል ፈተና ላይ የሚሰጡ የትምህርት ዓይነቶች ተማሪዎቹ እንዲይዙት የሚፈለገውን ፦
* እውቀት፣
* ክህሎት
* ባህሪያት መቅሰማቸው የሚፈተኑበት ይሆናል።

የሥነ ዜጋ እና ሥነ ምግባር ትምህርት በ12ተኛ ክፍል ፈተና ላይ እንዳይሰጥ የተደረገው በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ምክንያት ትምህርቱ ከ10ኛ ክፍል በኋላ ስለማይሰጥ ነው።

ኢኮኖሚክስ ከዚህ ቀደምም ይሰጥ ነበር። መሃል ላይ የሆኑ የጥናት ሃሳቦች ተነስተው ከፈተና እንደወጣ እናውቃለን፤ አሁን ግን ወደ ሥርዓተ ትምህርቱ ተመልሷል፤ መጽሐፍ ታትሞለታል። እንዲማሩ እየተደረገ ካለው ጥረት አንጻር ወደ ፈተና ቢገባ የሚሉ ሀሳቦች ተነስተዋል።

የዘንድሮ ፈተና መቼ ይሰጣል ? ለሚለው ፤ ከክልሎች ጋር ምክክር እያደረግን ነው። በቅርቡ እናሳውቃለን። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም በሚሰጡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የትምህርት አይነቶች ላይ አስመልክቶ ጥር 9/2016 ዓ.ም ያስተላለፈው ውሳኔ ለትግራይ ተፈታኞች አይመለከትም " - የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ

የትምህርት ሚኒስቴር ከሰሞኑን ባስተላለፈው ውሳኔና ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች በላከው ደብዳቤ ዘንድሮ የሚሰጡ ፈተናዎችን ማሳወቁ ይታወሳል።

በዚህም ፦

- የተፈጥሮ ሣይንስ ተማሪዎች እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ፊዚክስ፣ ኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት እንደሚፈተኑ ገልጿል።

- የማኅበራዊ ሣይንስ ተማሪዎች ደግሞ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊ፣ ኢኮኖሚክስ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት እንደሚፈተኑ ገልጿል።

የፈተናው አወጣጥም ፤ ከኢኮኖሚክስ ትምህርት ውጪ ሁሉን የትምህርት አይነቶች ከ9-11ኛ ክፍሎች በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት እንዲሁም የ12ኛ ክፍል በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ፈተናው ይዘጋጃል። 

የኢኮኖሚክስ ፈተና ለ2016 ከ12ኛ ክፍል ብቻ ይዘጋጃል ማለቱ ይታወሳል።

ዛሬ ጥር 15/2016 የትግራይ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ኪሮስ ጉዕሽ ፤ " ትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም በሚሰጡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የትምህርት አይነቶች ላይ  በቅርቡ ያሳተላለፈው ውሳኔ ለትግራይ ተፈታኞች አይመለከትም "ብለዋል።

ሃላፊው አያይዘው " መምህራንና ተማሪዎች ፈተናው በነባሩ ሰርዓተ ትምህርትና መፃሕፍት የሚዘጋጅ መሆኑን እንድታውቁ " ሲሉ ገልጸዋል።

በፈተናው የሚሰጡ የትምህርት አይነቶችንም  ይፋ አድርገዋል።

የተፈጥሮ ሳይንስ ፦
እንግሊዝኛ፣
ሒሳብ፣
ፊዚክስ፣
ኬሚስትሪ፣
ባዮሎጂ
ስነዜጋና ስነምግባር እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት፤

የማኅበራዊ ሣይንስ፦
እንግሊዝኛ፣
ሒሳብ፣
ታሪክ፣
ጂኦግራፊ፣
ስነዜጋና ስነ-ምግባር እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት መሆናቸውን አስረድተዋል።

" የፈተናው ጥያቄም ከነባሩ መፅሐፍ እንደሚዘጋጅ ለማሳወቅ እንወዳለን " ማለታቸው የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።

#TikvahEthFamilyMekelle
                                     
@tikvahethiopia            
#EOTC

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፤ ከዚህ ቀደም አውግዛ የለየቻቸው ግለሰቦች አሁንም በሕገወጥ እንቅስቃሴያቸው እንደገፉበት አመልክታ ግለሰቦቹን በፍርድ እንደምትጠይቅ አስታወቀች።

ግለሰቦቹን አሁንም አውግዛ ፤ ድርጊታቸውን ተቃውማለች።

የለበሱት ልብስም የቤተክርስቲያን በመሆኑ #እንዲያወልቁት እንደምታደርግ ገልጻለች።

ባለፈው ዓመት በዚህ ወቅት ቤተክርስቲያን " ሕገወጥ " ባለችው መንገድ በጵጵስና ተሹመናል ካሉት እና በኃላም በእርቅ ወደቤተክርስቲያን ሳይመለሱ ከቀሩት መካከል አባ ገብረማርያም ነጋሳን ጨምሮ 4 አባቶች ትላንት በሰጡት መግለጫ " የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ቤተክህነት መንበረ ጴጥሮስ " አቋቁመናል ብለዋል።

ይህ በ2015 ዓ/ም ተቋቁሟል ላሉት የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ መንበር መሰየም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ይህንን ጉዳይ በተመለከተ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቋሚና ጊዜያዊ ፕሮጀክት መምሪያ ኃላፊ መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ወ/ኢየሱስ ሰይፉ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በዚህ መግለጫ ፤ " ግለሰቦቹ በሌላቸው ክህነት ነው መግለጫ እየሰጡ ያሉት " ብለዋል።

እነዚህን አካላት ያደረጉት ከቀኖና ውጭ ስለሆነ ዛሬም ቤተክርስቲያን አጥብቃ ታወግዛለች ሲሉ ተናግረዋል።

" ቤተክርስቲያን በሕግ በፍርድ ቤት ትጠይቃችለች ፤ በፍትህ መንፈሳዊ ከዚህ ቀደም እንዳወገዘችው አሁንም ህጌ፣ ስርዓቴ፣ ልብሴ ፣ ዶግማዬ ይከበር ትላለች " ሲሉ አክለዋል።

" ከዚህ ቀደም በፍ/ቤት ከቤተክርስቲያን እውቅና ውጭ የትም እንዳይንቀሳቀሱ ፣ አገልግሎት እንዳይሰጡ ታግደው ነበር ያንን ተላልፈዋል ከዚህ በኃላ በፍርድ እንጠይቃቸዋለን፤ የለበሱት ልብስም የቤተክርስቲያን ስለሆነ እናስወልቃቸዋለን፤ ህገወጥ ናቸው " ብለዋል።

" ከዚህ ባለፈ ይህ የሕገወጥ የሹመት እንቅስቃሴ ጉዳይ ከኦሮሚያ ወገን የተነሱትን ብቻ ሳይሆን ከትግራይ ወገን የተነሱትንም የሚመለከት ነው " ያሉ ሲሆን ሲመቱ ትክክለኛ አይደለም ቅዱስ ሲኖዶስም አይቀበለውም ብለዋል።

የቤተክርስቲያንን ውሳኔ ማስፈፀም የሚችል አካል ሌላ በመሆኑ እንዲያስፈፅም በትዕግስት እየጠበቅን ነው ሲሉም ተናግረዋል።

ኃላፊው ፤ ከዚህ ቀደም በኦሮሚያ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት አባቶች በቤተክርስቲያን ጥሪ ተመልሰው መጥተው ፣ ከመንግሥት ጋር በተደረግው ውይይት ፣ ወደቀድሞ ስራቸው እንዲመለሱ ተደርጎ በስራ ላይ ናቸው ብለዋል።

አራቱ እንዳልተመለሱና በሕገወጥ እንቅስቃሴ መቀጠላቸውን ገልጸው " የቤተክርስቲያንን ስም ማንሳት አይችሉም ፣ ስሟን ማጠልሸት አይችሉም " ሲሉ አሳስበዋል።

" እራሱ ህገወጥ ቡድን የ ' 5 ኪሎ ህገወጥ ' እያለ መጥራቱ ትልቅ ድፍረት ነው " ያሉት ኃላፊው ፤ " ይህን ድፍረት የሰጣቸውም ወቅትና ጊዜውን እየዋጁ መነሳታቸው ነው ብለዋል።

" #ሃይማኖት እና #ፖለቲካም ተቀላቅሎባቸዋል " ሲሉ አክለዋል።

" የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እና ምዕመናኖቿ ይህንን ህገወጥ ተግባር አይቀበሉትም ፤ ስለተወገዛችሁም ምዕመኑንም ከእናተ መስቀል አይባረክም " ሲሉ አሳውቀዋል።

ከዚህ ባለፈ ቤተክርስቲያኗ አውግዤ የለየኋቸውን አካላት መግለጫ ልክ እንደ ህጋዊ እያደረጉ ያቀርባሉ ያለቻቸውን #ሚዲያዎች ' ከቤተክርስቲያን ላይ እጃችሁን ፣ ሚዲያችሁን አንሱ ' ስትል አስጠንቅቃለች።

@tikvahethiopia
የተሽከርካሪ አደጋ የ14 ሰዎች ህይወት ቀጠፈ።

ዛሬ ከቀኑ 6 ሰዓት ተኩል አካባቢ በደቡብ ወሎ ዞን ፤ ደሴ ዙሪያ ወረዳ 013 ቀበሌ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የ14 ሰዎች ህይወት ማለፉን የወረዳው ፖሊስ ፅ/ቤት አሳውቋል።

ከደሴ ወደ አቀስታ ከተማ 20 ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ " ኮድ3-46660 አማ " የሆነ አነስተኛ የህዝብ ማመላለኛ ተሽከርካሪ ገደል ውስጥ በመግባቱ ነው የ14 ሰዎች ህይወት ያለፈው።

ከሟቾቹ መካከል የ12ቱ ሰዎች ህይወታቸው ወዲያውኑ ሲያልፍ አንዱ ወደ ሆስፒታል እየተወሰደ ባለበት ወቅትና ሌላው ተሳፋሪ ደግሞ ደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከደረሰ በኋላ ህይወቱ አልፏል።

ከአጠቃላይ ሟቾች ውስጥም ስድስቱ #ሴቶች ናቸው።

አሽከርካሪውን ጨምሮ ሌሎች በአደጋው ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸው 6 ሰዎች በደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ነው።

የሟቾች አስከሬን ለቤተሰቦቻቸው ተሰጥቷል።

ፖሊስ የአደጋውን መንስኤ እያጣራ መሆኑን ፅ/ቤቱ መግለፁን ኢዜአ ዘግቧል።

ከዚህ አደጋ ጋር በተያያዘ አንድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል በላከችው መልዕክት ፤ ከሟቾቹ ሁለቱ የቅርብ ጓደኞቿ እንደሆኑ ተናግራለች።

ሌሎች ሁለቱ ደግሞ እህትማማቾች እንደሆኑ ገልጻለች።

" በጣም ከባድ ሀዘን ላይ ነን ፤ መላው የአቀስታ ህዝብም ከባድ ሃዘን ላይ ነው " ብላለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ጵጥሮስ " አቋቁመናል ካሉት ውስጥ ሶስቱ #መታሰራቸውን የእንቅስቃሴው አስተባባሪ ነኝ ያሉ ዲያቆን አክሊሉ ዓለሙ የተባሉ ግስለሰብ ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።

ሶስቱ አባቶች የታሰሩት " መንበረ ጴጥሮስ " አቋቁመናል የሚል መግለጫ ከሰጡ በኃላ ሸገር ከተማ አስተዳደር በሚገኘው ቢሯቸው እንደሆነ እኚሁ አስተባባሪ ተናግረዋል።

የታሰሩት ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማዕረጋቸውን ገፍፌዋለሁ ያለቻቸው አባ ገብረማርያም ነጋሳ፣ አባ ወልደ ኢያሱስ ኢፋ እንዲሁም አባ ወልደኢየሱስ ተስፋዬ እንደሆኑ ለመረዳት ተችሏል።

ሌሎችም አብረው የነበሩ ግለሰቦች መያዛቸውም ተነግሯል።

የሸገር ከተማ አስታዳደር ፖሊስ ስለጉዳዩ ምንም ያለው ነገር የለውም።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትላንት ተቋቁሟል የተባለውን " መንበረ ጴጥሮስ " አውግዛ ፤ አሁን በሕገወጥ ድርጊታቸው የቀጠሉትን ቡድኖች በፍርድ እንደምትጠይቅ አሳውቃለች።

በኦሮሚያ ክልል ባለፈው ዓመት በዚህ ወቅት በእነ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የተመራ የ26 የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ተሰጥቶ እንደነበር ይታወሳል።

ይህንን ሹመት ተከትሎም ቤተክርስቲያኗ በከፍተኛ ሁኔታ ያወገዘችና ግለሰቦቹንም የለየች ሲሆን ህገወጥ ባለችው ሹመት ላይ የተሳተፉ አካላትም ላይ እገዳ እና ማዕረጋቸውን የማንሳት ውሳኔ አሳልፋ ነበር።

እነ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በወቅቱ ቤተክርስቲያን " ህገወጥ ነው ! " ላለችው የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ያደረሳቸው ፤ " ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረው 85% ከአንድ ወገን በመሆኑ፣ ያለው የውስጥ አሰራር ችግር፣ አባቶችን ከየአካባቢው ከማፍራት ይልቅ ከአንድ ወገን ብቻ የመሾም ችግር ፣  የሚመደቡት አባቶች የህዝቡን ባህል እና ቋንቋ ባለማወቃቸው ለምእመናን እምነት መዳከም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳደረገ መሆኑ ... " የሚሉና ሌሎች ምክንያቶች እንደነበሩ ይታወሳል።

ረጅም ጊዜ ከፈጀ አለመግባባት በኃላ በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች፣ ምክክር እና መግባባት፣ መንግሥትም ገብቶበት በቤተክርስቲያን በቀረበ ጥሪ እነ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስን ጨምሮ ሎሎችም ብፁዓን አባቶች ወደ ቤተክርስቲያን ተመልሰው አሁን ላይ በስራ ላይ ይገኛሉ።

ከተወገዙት እና ከተለዩት ውስጥ ግን 4 አባቶች ጥሪውን ተቀብለው ያልመጡ ሲሆን አሁን 2015 ዓ/ም የተቋቋመ ነው ባሉት " የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ " መንበር መሰየም በማስፈለጉ " የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መንበረ ጴጥሮስ " አቋቁመናል ሲሉ በይፋዊ መግለጫ አሳውቀዋል።

ይህንን መግለጫ በሸገር ከተማ ከሰጡ በኃላ #መታሰራቸውን የእንቅስቃሴው አስተባባሪ ነኝ ያሉ ግለሰብ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
Tecno Spark 20 pro+ ! 

በአይነቱ ለየት ያለው አዲሱ ‘spark 20 pro+’ ስልክ ምርጫዎ ሲያደርጉ 256 ጂቢ ሚሞሪ ከ 16ጂቢ ኤክቴንድድ ራም ጋር በማጣመር፣ የፈለጉትን መተግበሪያ ወይም አፕ መጫን የሚያስችል ሲሆን (G99 ultimate processor) የተገጠመለት በመሆኑ የመረጡትን ጌም ሳይሳቀቁ መጫወት ያስችሎታል።

ቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ
#Spark20pro+ #TecnoMobile #TecnoEthiopia
Addis Ababa University- Cisco Networking Academy,
@CiscoExams www.netacad.com www.cisco.com

Online Live class - Cisco CCNA Professional Networking Course Training & Certification Preparation.

Registration Date: Jan 12 to Feb.09, 2024
Class start date: Feb. 10, 2024.

Course Recognitions: CCNA trainees will receive 3 Certificate of Completion, 3 Letter of Merit, 3 Digital Badge that recognized and accepted in USA, Canada, and Europe, and you will award 58% CCNA certification exam discount voucher.

Mobile #: 0902-340070/0935-602563/ 0945-039478/
Office : 011-1-260194

Follow our telegram channel: @CiscoExams
#ቅሬታ #ምላሽ

“ ... ባለ 3 መኝታ ቤት ዕድለኞች ተብለው የወጡት ተመዝጋቢዎች አብዛኛዎቹ የባለ 2 መኝታ ቤት ተመዝጋቢዎች ናቸው ” - የኪ ሃውሲንግ የቤት ዕጣ ቆጠቢ

“ ... ጥቂት ቁጥሮች ባለ 2 ብለን እኛ ሲስተም ላይ ጽፈናቸው ‘አይ እኔ የተመዘገብኩት ባለ 3 ነው’ ሊሉ ይችላሉ” - አቶ ቸርነት መንግስቱ (ከድርጅቱ)

ከሰሞኑን " Key Housing Finance Solution " የተሰኘ ተቋም የቤት ባለቤት ለመሆን ሲቆጥቡ ለነበሩ ሰዎች ዕጣ አውጥቶ ነበር።

ከተለያዩ ሴክተሮች በሚገኙ ልምድ ባላቸው አካላት ተዋቅሯል የተባለው " Key Housing Finance Solution " ከ15,000 በላይ ለሆኑ የቤት ቆጣቢ ተመዝጋቢዎች መካከል ለ60 ቆጣቢዎች / የቤት ዕድለኞች የመጀመሪያ ዙር ዕጣ አውጥቶላቸዋል።

ድርጅቱ በ77,280 ብር ቅድመ ቁጠባ ሰዎች የቤት ባለቤት የሚሆኑበት ሞዴል ፕሮጀክት እንዳለው በገለጸው እና በተለያዩ መንገዶች ባስተዋወቀው መሰረት ነው ከ15,000 በላይ ቤት ፈላጊ ቆጣቢዎች ውስጥ #ለ60_ቆጣቢዎች / #ባለዕድለኞች ዕጣ ያወጣላቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከ “Key housing Finanance Solution” የቤት ዕጣ ቆጣቢ፣ “ኪ ሃውሲንግን በተመለከተ እጣ አወጣጡ ላይ ስህተቶች የተሰሩ በመሆኑ ማብራሪያና እርማት ብንጠይቅም በሶሻል ሚድያም ሆነ በሌላ ምላሽ ልናገኝ አልቻልንም” የሚል ቅሬታ ደርሶታል።

ከተመዝጋቢዎቹ መካከል አንዷ በሰጡን ቃል፣ “ ባለ 3 መኝታ ቤት ዕድለኛ ተብለው የወጡት ተመዝጋቢዎች አብዛኛዎቹ ባለ 2 ተመዝጋቢዎች ናቸው ” ብለዋል።

አክለውም ፣ “ ለዚሁም ብለን ' አትላስ ' በሚገኘው ዋና ቢሯቸው ማብራሪያ ለማግኘት ከአንዴም ሁለቴ ብንሄድም #በsystem ምክንያት ዕጣ አወጣጡ ላይ ችግር ያለበት መሆኑን ከማመን የዘለለ በቂ ምላሽ አልሰጡንም ” ሲሉ ድርጅቱን ወቅሰዋል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የቀረቡ ቅሬታዎች በዝርዝር ምን ይላሉ ?

- ዕጣው የደረሳቸውን ሰዎች ስም ዝርዝር ይፋ ካደረጉ በኋላ ቼክ በምናደርግበት ጊዜ ልዩነት አለው። 

- ልዩነት የተፈጠረው ባለ 3 ፣ ባለ 2 እና ባለ 1 መኝታ ቤት ነው ያዘጋጁት። ዕጣው ከመውጣቱ በፊት ካለው ዝርዝር ጋር ስናስተያየው ባለ 3 መኝታ ቤት ዕድለኛ ተብለው የወጡት ተመዝጋቢዎች አብኞቹ ባለ 2 መኝታ ቤት ተመዝጋቢዎች ናቸው።

- ከተመዝጋቢዎች ብዛት አንፃር #ባለ_3_መኝታ_ቤት ለ30 ሰዎች (50%)፣ ባለ 2 መኝታ ቤት ለ21 ሰዎች (35%)፣ ባለ 1 መኝታ ቤት ለዘጠኝ ሰዎች (15%) እንደሚወጣ ነበር ዕጣውን ከማውጣታቸው በፊት ሲገልጹ የነበረው።

- ባለ 3 መኝታ #ለ30_ሰዎች ብለው ካሰቡት ውስጥ ለ21 ሰዎች ነው የወጣው። የባለ 2 ደግሞ ለ21 ሰዎች ብለው ከገለጹት ለ29 ሰዎች ነው የወጣው። ባለ 1 መኝታ ቤት ደግሞ ለ9 ሰዎች ብለው ካሰቡት ለ10 ሰዎች ነው የወጣው። ይህ ማለት ይፋ ካደረጉት ፐርሰንቴጂ ጋር ግልፅ የሆነ ልዩነት አለው።

- በተጨማሪም ፤ ዕጣው ከመውጣቱ በፊት የታቀደው ፕላን በፐርሰት 50 በመቶ ባለ 3 መኝታ ቤት ፣ 35 በመቶ ባለ 2 መኝታ ቤት እንዲሁም ፣ 15 በመቶ ለባለ 1 መኝታ ቤት ብለው ነበር ያስቀመጡት። አክቹአል ሲወጣ ግን ወደ 35፣ 48፣ እና 17 ፐርሰቶች ተቀያይሯል።

- ከ15,000 በላይ ተመዝጋቢዎች 60 እደለኞች ብቻ መመረጣቸው ሳያንስ ይኸውም የ60 ሰዎች ዕጣ አወጣጥ ትክክል ያልሆነና ተዓማኒነት የጎደለው ነው።

- ሌላ ያስተዋልው የተመዝጋቢዎች ስም ዝርዝር ተብሎ የተመዘገበው ላይ እስከ አያት ድረስ በተመሳሳይ ደብል የሆኑ ስሞች አሉ” የሚሉ ናቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፤ የተነሳውን #ቅሬታ በተመለከተ ምላሽ እንዲሰጡ የብሉዞን ማርኬቲንግ ማናጀርና የኪ ሃውሲነሰግ ቦርድ ሜምበር አቶ ቸርነት መንግስቴን አነጋግሯቸዋል።

እሳቸው ምን አሉ ?

ወደ ሲስተም ሲሞላ የታይኘ ኢረር ይኖረዋል። ባለ 2 የተመዘገበን ሰው ባለ 1 ብለህ ልትጽፍ ትችላለህ፣ ባለ 1 የተመዘገበን ባለ 3 ትላለህ። 

ይኼ ከሆነ ምናልባት ደንበኛው ራሱ ደግሞ ዕጣ ውስጥ ' መካተት ፤ አለመካተቱን ' እንዲያረጋግጥ ፣ እንዲህ አይነት የታይፕ ስህተቶች ተፈጥረው ከሆነ ታይቶ እንዲነገረን ፖስት አድርገንላቸዋል። 

በቴሌግራም ላይ ፖስት ካደረግን በኋላ ጥቂት ቁጥሮች ባለ 2 ብለን እኛ ሲስተም ላይ ፅፈናቸው ‘አይ እኔ የተመዘገብኩት ባለ 3 ነው’ ሊሉ ይችላሉ። እሱን ከውሉ ጋር ወዲያው ከሀርድ ኮፒው እናመሳክራለን። ሲስተሙ ላይ ይስተካከልላቸዋል። ምክንያቱም አዲስ ሲስተም ነው። መሞከሪያም ነው መስተካከል አለበት።

ፓስት ያደረግነው ቁጥር ሁሉም ማለት አይደለም የተወሰኑ ሰዎች ‘እንዲህ አስተካክሉልን’ ብለውናል። አስተካክለንላቸዋል። ‘አስተካክሉልን’ ያሉን ሰዎች ከተስተካከለላቸው በኋላ በቀጥታ ሰነዱን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነው ያስረክብነው የተስተካከለውን። 

ቴሌግራም ላይ ፖስት የተደረገው ያልተስተካከለው የመጀመሪያው (አስተያዬት ለመሰብሰብ ፓስት የተደረገው) ነው። ዕጣ ከወጣ በኋላ ሰዎች ሂደው ሲያመሳክሩ ያን ያዩታል። ግን እነዛ ሰዎች እዚጋ እንዲስተካከልላቸው ሆኗል። ራሳቸው ባቀረቡት መሠረት ማለት ነው።

እንዲህ ካደረጋችሁ ፥ በተመዝጋቢዎች በኩል ብዥታ እንዳይፈጠር ለምን የተስተካከለውን በድጋሚ ፖስት አላደረጋችሁላቸውም ? ብሎ ቲክቫህ ጠይቋቸዋል።

ምላሻቸውም ፤ " ካለፈ በኋላ ፓስት ማድረግ እንችል ነበረ " ብለዋል።

ዕጣው ከመውጣቱ በፊት #የተስተካከለውን ሰነድ ፓስት ያላደረጉበትን ምክንያት ሲያስረዱ ፤ " የተጣራው ለአዲስ አበባ የምንሰጠው ሰነድ ነው። የአዲስ አበባን ዩኒቨርሲቲ Soft ware ከሰራበት በኋላ ነው እንጂ ኦዲት የምናደርገው ቀድመን ምን ይደረግ የሚለውን አናውቅም። ዜሮ፣ ዜሮ መሆኑን ብቻ ነው የምናየው " ሲሉ ተናግርዋል።

በተጨማሪ ...

ባለ 3 መኝታ ቤት ዕድለኛ ተብለው ዕጣ የወጣላቸው ተመዝጋቢዎች አብዛኛዎቹ ባለ 2 ተመዝጋቢዎች ናቸው ፤ ተብሎ ለቀረበው ቅሬታ ፦

° " ይህ #እውነት_አይደለም። ምክንያቱም ባለ 2 ተመዝግበው ባለ 3 እንዴት ይደርሳቸዋል ? የደረሰውስ እንዴት ይቀበላል ? የማይሆን ነገር ነው " ሲሉ መልሰዋል።

ዕጣ ከማውጣቱ በፊት ለባለ 3 ፣ ለባለ 2 እንዲሁም ለባለ 1 የቤት ዕድለኞች ያቀዱት ፐርሰንቴጂ ዕጣው ከወጣ በኋላ ተቀያይሯል ተብሎ ለተነሳው ቅሬታ ፦

° “ ቤቱን ገና አላስተላለፍንላቸውም። ገና በ18 ነው ቤቱን የሚረከቡት።

የሚረከቡትም በተባለው መሠረት ባለ 1 መኝታ ቤት ዘጠኝ ሰዎች፣ ባለ 2 መኝታ ቤት 21 ሰዎች፣ ባለ 3 መኝታ ቤት 30 ሰዎች ናቸው። ባልተዘጋጁ ቤቶች ዕጣ አናወጣም። ከየትስ እናመጣዋለን " ከሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ድርጅቱ ማብራሪያ ሊሰጥ ፈቃደኛ አልሆነም ተብሎ ለተነሳው ቅሬታ ፦

° “ ተወካይ ነን ብለው ለመጡ አባላቶች (የምር ተወካይ አይደሉም፤ የተወካይ ህጋዊ ሰነድ የላቸውም) ፤ ግን ነገሩ መልካም ስለሆነ ቢሮ ለእያንዳዱ ሰነድ ጭምር እያሳዬን ማብራሪያ ሰጥተናል ” ሲሉ መልሰዋል።

በተመሳሳይ ስም የተጠቀሱ " ዳብል " ተመዝጋቢዎች መኖራቸው ተከትሎ ለቀረበው ቅሬታ ፦

° " ... እንድ ተመዝጋቢ #ለብዙ_ሰዎች መመዝገብ ይችላል፣ ኮዱም ቢሆን ተመሳሳይ ሊሆን ይችላል " ሲሉ መልሰዋል።

በአዲስ አበባ ቲክቫህ ቤተሰብ አባል የተዘጋጀ።

@tikvahethiopia