TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል!

"ጠቅላይ ሚንስትሩ(ዶ/ር አብይ አህመድ)እና ከሳቸው ጋር ያሉት አባላት በሰላም ወደ ሸገር ተመልሰዋል። የመከላከያ ሰራዊት እስከአሁን ላሰየው እርጋታ ክብር ይገባዋል። ህዝቡም በተቻለ መጠን ሰላማዊ በሆነ መልኩ ለመሪዎቹ ደስተኛ አለመሆኑን በመግለፅ ወደ ድንጋይ ውርወራ አለመግባቱ እና ያደረገውን በሙሉ #በሰላም መድረጉ ያስመሰግነዋል። በአጠቃላይ ነገሮች በሰላም እንዲሆኑ ያደረጉት በሙሉ ክብር ይገባቸዋል። ከዚህ በኃላም ሁሉም ነገር በሰላም እንዲጠናቀቅ አለመዘናጋት ጥሩ ነው።" ዶክተር ደረጄ ገረፋ ቱሉ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለውጭ ሀገር ሚዲያዎች የሰጡት መገለጫ ሲዳሰስ !

[በጋዜጠኛ ሰለሞን ሙጬ/DW]

የመግለጫው ዋነኛ ጉዳዮች የነበሩት፦

- የታላቁ ህዳሴ ግድብ ድርድር
- የሱዳን ወረራ እና ያልተገባ ጫና
- 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ

የታላቁ የህዳሴ ግድብን ግንባታ በተመለከተ ግብፅ በውሃ ላይ ምንም አበርክቶ ሳይኖራት እያሳደረች ያለው ጫና ተገቢነት እንደሌለው አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ አሁንም ድርድሩን በአፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ ማስቀጠል እንደምትቀጥል አሳውቀዋል።

አምባሳደር ዲና የሁለተኛው ዙር ሙሌት በተያዘለት ጊዜ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

ግብፅና ሱዳን በሙሌቱ ላይ ስምምነት ካልደረሱ ምን ይሆናል ተብለው የተጠየቁ አምባሳደሩ ተከታዩን ምላሽ ነው የሰጡት፦

"በ3ቱ ሀገሮች በ2015 በሱዳን ካርቱም በተፈራረሙት የመርሆች መግለጫ መሰረት የግድቡ ሙሌት የግድቡ የስራ ሂደት አካል ነው። ስለዚህ የውሃ ሙሌቱ የግድቡ አካል ነው። ግድብ ከገነባህ ውሃ መሙላትህ እርግጥ ነው፤ ያ ነው ሊሆን የሚችለው ፤ በመጀመሪያው ዙር የግድቡ ሙሌት የሆነውም ይኸው ነው። አሁንም ተስፋ የምናደርገው በአሞላሉ እና በሂደቱ ላይ እንደምንስማማ ነው።"

የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ውዝግብን አስመልክቶ ሱዳን ከሰሞኑ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ላይ የባለቤትነት ጥያቄን ማንሳቷን አውግዘዋል።

በተለይ የሱዳን ወታደራዊ ክንፍ የውክልና ተልዕኮ አስፈፃሚነት ውስጥ መግባቱን አሳይቷል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ጉዳዩ አሁንም #በሰላም እንዲፈታ ግፊት ማድረጓን ቀጥላለች ብለዋል።

ምርጫ 2013 በተመለከተ አምባሳደር ዲና ፥ ከትላንት ጀምሮ የአውሮፓ ህብረት የባለሞያዎች ቡድን ለመላክ መስማማቱን አሳውቀዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/MFA-Ethiopia-05-08

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013

በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ፦

- የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ መዘግየት ፣
- በድምፅ አሰጣጥ ላይ የሚታይ መደነጋገር፣
- ሰዓት አለማክበር፣
- የኮቪድ-19 ፕሮቶኮል አለመጠበቅ፣
- ረጃጅም ሰልፎች (በፍጥነት አለመሄድ) ፣
- የሰልፍ ተራ አለመጠበቅ፣
- የምርጫ ቁሳቁስ መቀያየር
- ቀልጥፍ ያለ መስተንግዶ ክፍተት
- መራጮች ምርጫ ካርዳቸውን የወሰዱበትን መታወቂያ ሳይዙ መሄድ
- "እከሌን ምረጡ" የሚል ቅስቀሳ ለማድረግ መሞከር የመሳሰሉት ችግሮች ከመስተዋላቸው በዘለለ የምርጫ ሂደቱ #በሰላም እየተካሄድ መሆኑን ከአዲስ አበባና ከክልል የምርጫ ጣቢያዎች የቲክቫህ አባላት አሳውቀዋል።

የ Tikvah - Ethiopia አባላት በተመለከቷቸው የምርጫ ጣቢያዎች እድሜያቸው የገፋ ዜጎች ፣ እናቶች አባቶች ድምፅ ለመስጠት ተሰልፈው ተመልከተዋል። ነፍሠ ጡሮች፣ ልጅ የታቀፉ እናቶች ተሰልፈው ድምፅ ሲሰጡ አስተውለዋል።

በአጠቃላይ እስካሁን ድረስ በፀጥታ እና በሰላም ረገድ ምንም ጥቆማ ከአባላቶቻችን አልተላከም፤ ሁሉም ሂደት #በተረጋጋ ሁኔታ እየሄደ መሆኑን ገልፀውልናል።

Photo Credit : Tikvah Family (Addis Ababa)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#HappeningNow በአሁን ሰዓት በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ ህወሓትን እና ሸኔን የሚያወግዝ የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊትን የሚደግፍ ሰልፍ በመካሄድ ላይ ነው። በሰልፉ ላይ የውጭ ሀገር ጣልቃ ገብነትንና የውጭ ሀገር መገነኛ ብዙሃንን አጥብቀው የሚተቹ በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ የተፃፉ የተለያዩ መፈክሮች በሰልፈኞች ተይዘዋል። ሰልፈኞች ካያዟቸው መፈክሮች መካከል ፦ - የአሜሪካ…
#Update

" ሰልፉ በሰላም ተጠናቋል " - የአዲስ አበባ ፖሊስ

በመስቀል አደባባይና በዙሪያው የተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ #በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ፕሮግራሙ በሰላም እንዲጠናቀቅ የከተማው ነዋሪ በተለይ ደግሞ የሰላማዊ ሰልፉ ታዳሚዎች ከፀጥታ አካላት ጎን በመቆም ተገቢውን ትብብር በማድረጋቸው ፖሊስ ምስጋና አቅርቧል።

በተጨማሪ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እየተወጡ ላሉ የፀጥታ አካላት እንዲሁም ሰልፉን ላስተባበሩ እና ለመሩ አካላት በሙሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ምስጋናውን አቅርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት #በሰላማዊ_መንገድ ለመፍታት ሰላማዊ ድርድሮች እንዲጀመሩ ገዢው ብልፅግና ፓርቲ አቅጣጫ አስቀመጠ። በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ላይ የተፈጠሩ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ዉይይት በብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እና በማእከላዊ ኮሚቴዉ መካሄዱን የፍትሕ ሚኒስትርና የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ አስታወቁ። ዶ/ር…
#Peace

የተደራዳሪ ቡድኑ !

የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት #በሰላም_ድርድር እንዲፈታ ገዢው የብልፅግና ፓርቲ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል።

በዚህም መሰረት በፌዴራል መንግሥት በኩል የሰላም ተደራዳሪ ቡድን መሰየሙ ተረጋግጧል።

የቡድኑ አባላት ፦

1ኛ. አቶ ደመቀ መኮንን ➡️ ሰብሳቢ
2ኛ. ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቲዎስ ➡️ አባል
3ኛ. አቶ ተመስገን ጥሩነህ ➡️ አባል
4ኛ. አምባሳደር ሀሰን አብዱልቃድር ➡️ አባል
5ኛ. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ➡️ አባል
6ኛ. ሌ/ል ጀኔራል ብርሀኑ በቀለ ➡️ አባል
7ኛ. ዶ/ር ጌታቸው ጀምበር ➡️ አባል መሆናቸውን የኢፕድ ዘግቧል።

@tikvahethiopia