TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Gambella

በጎርፍ አደጋ ወገኖቻችን ተፈናቀሉ።

በጋምቤላ ክልል በ4 ወረዳዎች በደረሰ የጎርፍ አደጋ ከአራት ሺህ በላይ አባዎራና እማዎራ ወገኖቻችን ከመኖሪያ ቀያቸዉ ተፈናቅለዋል።

ከክልሉ አደጋ ስጋት አመራር በተገኘው መረጃ በሃገራችን ደጋማዉ አካባቢ በጣለዉ ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በላሬ፣ በመኮይ በዋንቱዋና በኢታንግ ልዩ ወረዳ በሚገኙ ቀበሌዎች ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ ተከስቷታ።

የጎርፍ መጥለቅለቅ ከደረሰባቸዉ 4 ወረዳዎች ዉስጥ አራት ሺህ አንድ መቶ ሰላሳ ዘጠኝ አባዎራና እማዎራ ከመኖሪያ ቀያቸዉ የተፈናቀሉ ሲሆን ለጊዜዉ ደረቃማ በሆኑ አካባቢዎች እንዲሰፍሩ ተደርጓል።

የደረሰው ጉዳት ዝርዝር ፦
- በኢታንግ ልዩ ወረዳ 2040 አባወራና እማወራ፣
- በላሬ ወረዳ 1000፣
- በዋንቱዋ ወረዳ 619፣
- በመኮይ 480 አባወራና እማወራ የተፈቀሉ ሲሆን በጂካዎ ወረዳም ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።

የጎርፍ አደጋዉ በቤት ዉስጥ ያሉ ቁሳቁሶች እንዲሁም በቁም እንስሳት ላይ ጉዳት አድርሷሳ።

በጎርፍ አደጋ ከቤት ንብረታቸዉ ለተፈናቀሉ ነዋሪዎች የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው የተገለፀ ሲሆን ከክልሉ መንግስትና ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት በመነጋገር አፋጣኝ ድጋፍ የሚደርስበት ሁኔታ ይመቻቻል ሲል የክልሉ አደጋ ስጋት አመራር አስታውቋል።

መረጃው ከክልሉ ኮሚኒኬሽን የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
በወይንሸት ካምፕ ምን ተፈጠሮ ነበር ?

በደብረ ብርሃን ከተማ ወይንሸት ካምፕ ለሚገኙ ተፈናቃይ በተደረገ የምገባ ፕሮግራም ችግር ተከስቶ እንደነበር እና ችግሩን መቆጣጠች መቻሉ ተገልጿል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በቀለ ገብሬ ነሀሴ 15 ቀን 2014ዓ.ም በወይንሸት መጠለያ ካምፕ ውስጥ ከሚገኙ ተፈናቃዮች ውስጥ ለ3 መቶ ተፈናቃዮች የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም መካሄዱን ገልጸው ከተመገቡት ውስጥ 1 መቶ 17ቱ መታመማቸውን አስረድተዋል፡፡

ችግሩ እንደተከሰተ የከተማው አመራሮች፣ የጸጥታ መዋቅር አካላትና የጤና ባለሙያዎች ባደረጉት ርብርብ የታመሙትን ወገኖች በፍጥነት ደብረ ብርሃን ሪፈራል ሆስፒታል ፣ 04 ጤና ጣቢያ ፣ አየር ጤና፣ እና ጠባሴ ጤና ጣቢያዎች በመውሰድ እንዲታከሙ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል፡፡

በዚህም ታመው ከነበሩት ውስጥ 116ቱ ወደ መጠለያ ጣቢያቸው መመለሳቸውን አረጋግጠው ፤ አንድ ሰው ግን አሁንም ህክምናውን እየተከታተለ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

ከምግቡ ጋር ተያይዞ ለተፈጠረው ችግር  መንስዔው ምን እንደሆነ ለማወቅ ለደብረ ብርሃን ሪፈራል ሆስታል ናሙናው ተሰጥቶ በምርመራ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

የናመናው ምርመራ  ውጤቱ እንደደረሰም ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ አሳውቀዋል፡፡

የችግሩን መንስዔ ውጤት እንደደረሰ ትክክለኛው መረጃ ይፋ እስከሚደረግ ድረስ ህብረተሰቡ  በትዕግስት እንዲጠባበቅ የጤና መምሪያ ኃላፊው ማሳሰባቸውን የከተማው አስተዳደር በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አስፍሯል።

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA

የአሸንዳ፣ ሻደይ፤ አሸንድዬ እና ሶለል በዓላት !

በሰሜን የሀገራችን ክፍል ላይ ከሚከበሩ በዓላት መካከል የአሸንዳ፣ ሻደይ እና አሸንድየ እና ሶለል በዓላት ይጠቀሳሉ።

በዓላቱ በተለይ በሴቶች ዘንድ በእጅጉ በድምቀት ነው የሚከበሩት።

እነዚህ በዓላት ከባለፈው ዓመት በፊት በዓለም አቀፉ ኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሳቢያ በነበረው ከፍተኛ የሆነ ስጋት በአደባባይ ሳይከበሩ ቀርተዋል ፤ ባለፈው ዓመት ደግሞ በጦርነት ሳቢያ ተቀዛቅዘው ተከብረዋል።

ዘንድሮ በአማራ ክልል የሻደይ ፣ አሸንድዬ እና ሶለል በዓላት ከአምናው በተሻለ ሁኔታ በድምቀት እየተከበረ ነው።

በትግራይ ክልል የሚከበረው የአሸንዳ በዓል ግን ዘንድሮም እንደቀደሙት ዓመታት በድምቀት ከሌላ የኢትዮጵያ ክፍሎች እና ከዓለም ሀገራት ጎብኝዎች ተሰባስበው ሊያከብሩት አልተቻለም።

የጦርነቱ ጉዳይ ሙሉ በሙሉ ባለመፈታቱ ወደ ክልሉ የሚደረግ ምንም እንቅስቃሴ የለም፣ የስልክ ሆነ ኢንተርኔት ግንኙነት ባለመኖሩ ነዋሪዎች ከዘመድ አዝማዶቻቸው ጋር እንኳን አደረሳችሁ መባባል እና ባህላቸውን ለሌሎች ለማስተዋወቅ አልተቻላቸውም።

የአሸንዳ ፣ አሸንድዬ ፣ ሻደይ በዓላት ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ ገጽታ ያላቸው ሲሆን ከማህበራዊ እሴታቸው በተጨማሪ በየዓመቱ የሚፈጥሩት የኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እያየለ መጥቶ ነበር።

በተለይ በዓላቱ ሚከበሩባቸው አካባቢዎች ያለው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እጅግ ከፍተኛ ነበር። የኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና ጦርነት ተዳምሮ ባለፉት 2 ዓመታት አጠቃላይ የቱሪስት እንቅስቃሴውን አዳክሞታል።

በሁሉም አካባቢዎች ዘላቂ ሰላም ወርዶ በዓላቱ ዳግም በድምቀት የሚከበሩበት ጊዜ ይመጣ ዘንድ ምኞታችን ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA የአሸንዳ፣ ሻደይ፤ አሸንድዬ እና ሶለል በዓላት ! በሰሜን የሀገራችን ክፍል ላይ ከሚከበሩ በዓላት መካከል የአሸንዳ፣ ሻደይ እና አሸንድየ እና ሶለል በዓላት ይጠቀሳሉ። በዓላቱ በተለይ በሴቶች ዘንድ በእጅጉ በድምቀት ነው የሚከበሩት። እነዚህ በዓላት ከባለፈው ዓመት በፊት በዓለም አቀፉ ኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሳቢያ በነበረው ከፍተኛ የሆነ ስጋት በአደባባይ ሳይከበሩ ቀርተዋል ፤ ባለፈው…
ስለ ሻደይ፣ አሸንድዬ፣ ሶለል ምን ያህል አውቃለሁ ?

የሻዳይ፣ አሸንድዬ እና ሶለል ባህል ዓመታዊ ክብረ በዓል በአማራ ክልል የሚከበር በዓል ነው።

በዋግ ሹሞች መዲና ሰቆጣና አካባቢዋ ሻደይ፣ በቆቦ አካባቢ ሶለል እና በላስታ እና በአብዛኛው የክልሉ አካባቢዎች አሸንድዬ በሚል የሚከበረ የልጅ አገረዶች ጨዋታ በዓል ነው።

በዓላቱ አማራ ክልል ባለብዙ ዘርፍ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ሀብት ባለቤት መሆኑን ፣ የተለያዩ ቋንቋዎች እና ባሕላዊ ትውፊቶች ያሉት፣ ሕዝቦች በመተሳሰብ በመፈቃቀር እና በአንድነት የሚኖሩበት መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው።

የሻደይ፣ አሸንድዬ፣ሶለል በዓል የአዲስ አመት መምጣቱን ተከትሎ የሚከበር ብስራት ነው።

ልጃገረዶች ከክረምት መግባት ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ ውጣ ውረዶችን አልፈው ብሩህ ዘመን እየመጣ መሆኑን የሚያበስሩበት፣ እጮኛ የሚያጩበት፣ ከአቻዎቻቸው ጋር የሚጨፍሩበት እና የሚጫወቱበት ባሕላዊ ጨዋታ ነው።

በተጨማሪ እናቶች እና ህጻናት ያለ ልዩነት ሚሳተፉበትም ነው።

በዓላቱ በህዝባዊ አንድነት የሚያከብሩ፣ የመተሳሰብ፣ የፍቅር እና አብሮ የመኖር እሴትን ለትውልድ ማስተላለፊያ ጠንካራ ገመድ ናቸው።

ለውጭ ሀገራት ብርቅ በመሆኑም የገቢ ምንጭም ነው።

(ከአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ያገኘነው)

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
#አሸንዳ

በአሸንዳ በዓል ዙሪያ የተደረገ ጥናት!

(መብራህተን ገ/ማሪያም)

በትግራይ የተለያዩ አካባቢዎች የሚከበረው የአሸንዳ በዓል ፍቅር፣ይቅር ባይነትና መልካም ተግባቦት በተግባር የሚንጸባረቅበት በዓል ነው።

በዓሉ በልጃገረዶች ይበልጥ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበረል፤ልጃገረዶች አደባባይ ወጥተው የሚያከብሩት ሃይማኖታዊና ባህላዊ በዓል ነው።

የበዓሉ ይዘት በዋናነት ህብረተሰቡ ውስጥ ያሉ መልካም ተግባቦቶች፣ፍቅርንና ይቅር ባይነት ላይ ያነጣጠረ ነው።

በዓሉ የሌሎች ሃሳቦች፣ጭፈራዎችና ትእይንቶችም እንዲታዩ የሚጋብዝ ከመሆኑ ባለፈ የሃይማኖትና የብሔር ልዩነት አይንፀባረቅበትም።

በአሸንዳ በዓል ላይ የሚነገሩ ስነ ቃሎች ይዘት በአብዛኛው ህብረትን የሚሰብኩ፣መድልዎን የሚጠየፉና ለሰው ክብርን የሚያጎናጽፉ ናቸው።

ልጃገረዶች በዓሉን በህብረሰቡ ውስጥ ያለውን እርስ በርስ የመተባበር፣የመረዳዳትና የጀግንነት መልካም እሴቶችን አጉልተው ለማሳየት ይጠቀሙበታል።

በዓሉ ሴቶች ያላቸውን የፈጠራ፣ የመደራደር፣ የውሳኔ ሰጭነት ብቃት በተግባር የሚያሳዩበትና መልካም ስሜታቸውን የሚገልጹበትም ነው።

በተጨማሪ በህዝቡ ውስጥ ያሉትን ጉድለቶች በስነ ቃልና በዘፈን መልክ እንዲስተካከሉ የሚነቅፉበት፣ማህበረሰቡ መድልዎን እንዲጠየፍ፣የሴቶችን መብት የሚጋፋ የአስተዳደር መዋቅር አሊያም ወንድ ካለ እንዲስተካከል መልዕክት የሚያስተላልፉበት ጭምር ነው።

አሸንዳ በዓል ለትግራይ ህዝብ ባህል የመሰረት ድንጋይ ተደርጎ ይወሰዳል፤ በዓሉ ማንነትን አጉልተው የሚያሳዩ እሴቶች አሉት።

አሸንዳ ለሴቶች መብት አጥብቆ የሚታገል፣ መከባበርንና መረዳዳትን አብዝቶ የሚሰብክ፣ ሰዎች ባላቸው የሃብት መጠን ሳይሆን በሰውነታቸው ብቻ ክብር እደሚገባቸው በስነ ቃልና በዘፈን መልክ መልዕክት ይተላለፍበታል።

#Repost2013

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#የዩኒቨርሲቲ_መምህራን ! በዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበራት በኩል የቀረቡ ጥያቄዎች ፦ • መንግሥትን የደመወዝ ጭማሪ እና የዕርከን ዕድገት እንዲያደርግ ጠይቀዋል። • ለዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ እና ቴክኒካል ረዳቶች የተሰራውን አዲሱን የስራ ደረጃ ማሻሻያ JEG በተመለከተ ቅሬታ አላቸው። • የመምህራን የቤት አበልን በተመለከተ በፍጥነት አሁን ያለው የቤት ኪራይ ዋጋ ከግምት አስገብቶ ተሻሽሎ ተግባራዊ እንዲደረገ…
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ መምህራን እና ዩኒቨርሲቲዎች ምን አሉ ?

ጠ/ሚር ዶክተር ዓብይ አህመድ ትላንት ከወጣቶች ጋር በተወያዩበት መድረክ ስለዩኒቨርስቲዎች እና ስለ መምህራን ተነስቶላቸው የሚከተለውን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦

" የዩኒቨርስቲ መምህራን እናንተም መገንዘብ ያለባችሁ ኢትዮጵያ ደሃ አገር ናት። አሜሪካ እንኳን ዩኒቨርስቲ ተማሪ አስገብታ አትቀልብም።

ዩኒቨርስቲ ሰው ከደረሰ ራሱን ነው ማስተማር ያለበት እንጂ ለአስተማሪም ደመወዝ ፣ ለተማሪ ቀለብ አይነት ጥያቄ እንደኢትዮጵያ ላሉ ድሃ አገራት ኢኖቬተርስ አይፈጥርም።

ዩኒቨርስቲዎች አውቶነመስ ሆነው ራሳቸውን ማስተዳደር አለባቸው። ሃይስኩል ላይ ኢንቨስት ካደረግን እኛ እሱ እንደ በቂ መወሰድ አለበት።

ዩኒቨርስቲ ሆኖ ገንዘብ አምጥቶ የራሱን ደመወዝ መክፈል የማይችል ከሆነ ኢትዮጵያን ማሳደግ አይችልም ማለት ነው።

ሃርቫርድ መንግሥትን አይጠይቅም በጀት፣ ኦክስፎርድ አይጠይቅም በጀት፣ ኬንያም ዩጋንዳንም ብትሄድ አይጠይቅም በጀት፣ እዚህ ግን ቀለቡም፣ ደመወዙም ሁሉም ነገር የሚጠየቅ ከሆነ ችግር አለ።

ሁለተኛ የዩኒቨርስቲ መምህር ስታንዳርድ አለው። በሴሚስተር አራት ክሬዲት ሃወር፣ አምስት ክሬዲት ሃወር አስተምረህ የዩኒቨርስቲ መምህር ነኝ አይባልም። ተጋባዥ መምህር ነኝ ነው የሚባለው። ማነው ሙሉ ጊዜ መምህር ለመባል የሚያበቃ ስራ እየሰራ ያለው የሚለውን ማየት አለባችሁ። ይሄ ብዙ ችግር አለ።

ሁሉም የዩኒቨርስቲ መምህር በርግጠኝነት የምነግራችሁ በቂ ደመወዝ አያገኝም። ደመወዙ ያንሳል ፣ ኑሮው ዝቅተኛ ነው ትክክል ነው። መቀየር አለበት። ነገር ግን ኢትዮጵያንም ማሰብ ጥሩ ነው። እዳ ተጭኖን፣ ዋጋ ግሽበት ሊገድለን፣ ጦርነት እያለብን፣ የዓለም ተጽዕኖ በዝቶብን ፕሮጀክቶች እዚህም፣ እዚያም፣ እዚያም ጥደን እያረሩብን፣ አያዋጣም !

የከፋው ደግሞ የዩኒቨርስቲ መምህር ሃላፊነቱን ዘንግቶ የፖለቲካ አጀንዳ መጫወቻ ሲሆን ደግሞ በጣም መጥፎ ነው። አሉ እንደዛ ምልክቶች! ይሄ መስተካከል አለበት።

የዩኒቨርስቲ መምህራን በሃሳብ እንዲያግዙን እንፈልጋለን። አሁን ካለንበት ችግር ከዋጋ ግሽበቱ ፣ ከፕሮጀክቱም ፣ ከድህነቱም እንድንወጣ ፣ የምንጠብቀው እነሱን ነው። ይቺ አገር ከሌላት አንጡራ ሃብት ላይ መንዝራ መቀነቷን ፈታ አስተምራቸዋለች፣ ያለችበትን ችግር መፍታት የእኔም የእነሱም እዳ ነው። "

@tikvahethiopia
እድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበታል !

“ አንተ ለምን ትንበቀበቃለህ ? ” ብሎኛል በሚል ምክንያት የስራ ባልደረቦቹን የገደለው እና ያቆሰለው የፌዴራል ፖሊስ በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተቀጣ።

የፌዴራል ፖሊስ አባል የሆነው ኮንስታብል ማማሩ ተመስገን ጥቅምት 1 ቀን 2012 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 10፡30 ሰዓት አካባቢ በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 07 ልዩ ቦታው ፍልዉሃ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ በፌዴራል ፖሊስ የፀረ ሽብር ፖሊስ ዲቪዥን የእግር አሰሳ ስራ ለማከናወን ተመድቦ ስራውን በማከናወን ላይ ነበር።

በዚህም ወቅት የመብራት ፊውዝ ፈንድቶ በመሮጡ የሥራ ባልደረባው የሆነው ሟች ትዕግስቱ እንድሪያስ “አንተ ለምን ትንበቀበቃለህʔ” በማለት ተናግሮኛል በሚል ምክንያት በያዘው ታጣፊ ክላሽ ተኩሶ የገደለው ሲሆን በተጨማሪም የእግር አሰሳ ስራን ሲያከናውኑ ከነበሩ እና የፌዴራል ፖሊስ አባላትን ወደካምፕ ለመውሰድ ተዘጋጅቶ በቆመ መኪና ውስጥ የነበረችዋን የስራ ባለደረባው ድመቅ ጌታቸውን ተኩሶ በመምታት ህይወቷ እንዲያልፍ አድርጓል።

በተጨማሪም ሌሎች 3 የስራ ባልደረቦቹ ላይ ጉዳት በማድረሱ በ2ቱ የሰው መግደል ወንጀል እና በ3ቱ የሰው መግደል ሙከራ ወንጀል በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ የልዩ ልዩ ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ አጠቃላይ 5 ክሶችን እንደመሰረተበት የክስ መዝገቡ ያሳያል፡፡

በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ከባድ ውንብድና እና ግድያ ወንጀል ችሎት የቀረበው የዐቃቤ ህግ ክስም ተነቦና ክርክር ተደርጎ ሲያበቃ ፍርድ ቤቱ በአምስቱም ክሶች ተከሳሹ ጥፋተኛ ነው በማለት በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ እና ለዘወትር ከህዝባዊ መብቶቹ እንዲታገድ ሲል ወስኖበታል፡፡

መረጃው የፍትህ ሚኒስቴር ነው።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ጥንቃቄ

በአዲስ አበባ ከባድ ዝናብ የጣለ ነው። በዚህም ሳቢያ በተለያዩ አካባቢዎች ላይ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ፈታኝ ሆነዋል።

አሽከርካሪዎች ፤ በእንደህ ያለው ወቅት ባለማሽከርከር የራሳችንን እና የሌሎችን ወገኖች ደህንነት ማስጠበቅ ይገባናል።

ቪድዮ : አብዱራህማን መኪ - ከደቂቃዎች በፊት ፒያሳ
አካባቢ (Tikvah Family)

@tikvahethiopia
ሱዳን ?

ሱዳን " ሰነድ የላቸውም " ያለቻቸውን የሀገራችንን ዜጎች እያፈሰች እያሰረችና እየቀጣች ነው።

ጎረቤት ሀገር ሱዳን በሀገሯ የሚገኙትን ዜጎቻችንን እያፈሰች እያሰረች ሲሆን በዛው ያሉ ዜጎቻችን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጉዳዩን የያዘበትን መንገድ እየወቀሱ ይገኛሉ።

ዜጎቻችን ከፍተኛ ቅጣት እየተጣለባቸው እስከ ድብደብዳ የደረሰ እንግልትም እየደረሰባቸው ኤምባሲው ዝምታን እየመረጠ ነው ሲሉ ተችተዋል።

ኤምባሲው በበኩሉ ዛሬ ባሰራጨው መልዕክት ፓስፖርት የሌላቸው በሱዳን የሚገኙ ዜጎቻችን ፓስፖርት እንዲያገኙ ኮሚቴ ተቋቁሞ ሰነድ አልባ ዜጎቻችን የሞሉትን ሰነድ አልባ ፎርም በማጣራት ውሳኔ በመስጠት ፓስፖርት እያዲያገኙ እየተሰራ ነው ብሏል።

ነገር ግን ብዙ ዜጎቻችን ፓስፖርት እያላቸው የመኖሪያ ፍቃድ (ኢቃማ) ባለማውጣታቸው ምክንያት እየታሰሩና ገንዘብ እየተቀጡ እንደሚገኙም አመልክቷል።

ኤምባሲው ፓስፖርት መያዝ ብቻ ከቅጣትና ከመታሠር አያድንም ብሏል።

ፓስፖርት አውጥተው 5 ዓመት ሙሉ መኖሪያ ፍቃድ(ኢቃማ) ሳያሰሩ ፓስፖርት የሚያሳድሱ ዜጎቻችን ብዙ ናቸው ያለድ ኤምባሲድ " የመኖሪያ ፍቃድ ካላወጡ ፓስፖርት ብቻ መያዝ ህጋዊ አያደርግም " ብሏል።

የመኖሪያ ፍቃድ ባላወጡ ዜጎች ላይ አሁንም #አፈሳው_ሊቀጥል ይችላል ያለው ኤምባሲው " ፓስፖርት ያላችሁ የመኖርያ ፍቃድ (ኢቃማ) እንድታወጡና ህጋዊ ሆናችሁ እንድትኖሩ እንመክራለን " ብሏል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#ቦረና

በኦሮሚያ ፣ ቦረና በድርቅ ሳቢያ በርካታ ወገኖቻችን ዛሬም ችግር ላይ ናቸው። እነዚህ ወገኖች በድርቁ ምክንያት ያላቸውን ከብቶች ስላጡ እጅግ በጣም ፈታኝ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ነው የሚኖሩት።

በድርቅ ተፈናቅለው መጠለያ ውስጥ ያሉ ወገኖች ሰሞኑን ቃላቸውን ለቪኦኤ ሬድዮ ሰጥተው የነበረ ሲሆን ያሉበት ሁኔታ እጅግ በጣም አሳዛኝ ነው።

(በድብሉቅ ወረዳ የሚገኙ ተፈናቃዮች)

የ7 ልጆች እናት ወ/ሮ ጂሎ ጉራቻ ፦

" የዘንድሮው ድርቅ የነበሩንን ከብቶች እና ሁሉንም ንብረቶችን ነው ያወደመብን። ባዶ እጃችንን ስንሆን ወደዚህ መጣን ፤ እዚህ ከመጣን በኃላ በምግብ እና ውሃ እጥረት እየተቸገርን ነው። በተለይም ህፃናት ነፍሰጡር ሴቶች፣ አዛውንቶች በምግብ እጥረት እየተጎዱ ናቸው። እኛ እዚህ ከሰፈርን ከ6 ወር በላይ ሆኖናል። በመጠለያው በጣም ብዙ ቤተሰቦች ነው ያሉት። በቆይታችን አንዴ ብቻ ነው ለተወሰኑ ቤተሰቦች የምግብ ድጋፍ የተሰጠው እንጂ ምንም አላገኘንም። ስለዚህ በጣም ችግር ላይ ውስጥ ነው ያለነው። "

የ6 ልጆች አባት ዳለቻ ዲዳ ፦

" ምንጠጣው ውሃ በጣም የቆሸሸ ነው። እንስሳት ሲሞቱ ከሚጣሉበት ነው ልጆቻችን የሚቀዱልን። በዛ ላይ የመፀዳጃ ቦታም የለንም። እንዲሁ በበሩ ደጃፍ ነው ይህ ሁሉ በዚህ የሰፈረው ህዝብ የሚፀዳዳው ስለዚህ የበሽታ ወረርሽኝ ፍራቻ አለብን። ሌላው የመጠለያ ቦታና ላስቲክ ሰጥተውናል። ይህ ላስቲክ #ብርድ የሚከላከል አይደለም። እናም በጣም ችግር ውስጥ ነን። "

የልጆች እናቷ ትዬ አደንጌ ፦

" #ብርዱ_በጣም_አስቸጋሪ_ነው። ለምግብ ፍለጋ ነው ከእሳት አጠገብ የምንነሳው። በዛ ላይ የምንለብሰው ልብስ የለንም። በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለነው። "

ያንብቡ : https://telegra.ph/Borana-08-23 #ገልሞ_ዳዊት

@tikvahethiopia