TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሐምሌ19

የፀጥታ ኃይሎች ዝግጅት ምን ይመስላል ?

(ቁልቢ ገብርኤል)

የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ ፤ በዓመታዊው የቁልቢ ገብርኤል ንግስ በዓል ላይ የሚታደሙ ምዕመናንን እና እንግዶችን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ አስተማማኝ ዝግጅት መደረጉን አሳውቋል።

ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ የምስራቅ እና የምዕራብ ሐረርጌ ዞኖች፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ፣ የሐረሪ ክልል ፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ተቀናጅተው በቂ ዝግጅት አድርገዋል።

የንግስ በዓሉ ታዳሚዎች መጨናነቅ በሚበዛባቸው ቦታዎች ላይ በተለይ የደብሩ መግቢያና መውጫ በሮች አካባቢ የኪስ ቦርሳቸውን ፣ ሞባይላቸውን እና ሌሎች ንብረቶቻቸውን በጥንቃቄ እንዲይዙ ፖሊስ አሳስቧል።

አሽከርካሪዎች ወደ ንግስ በዓሉ ሲመጡ #ከኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_መለያ ወይንም ከህጋዊው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በስተቀር ሌላ ለፖለቲካ ማራመጃ የሚሆን ዓርማና ምልክት ይዞ መገኘት እንደማይቻል አሳስቧል።

በንግስ በዓል ላይ ሶስት ጊዜያዊ ፖሊስ ጣቢያ እና የወንጀል ድርጊት ተጠርጣሪዎች ሲያዙ ውሳኔ ለመስጠት ዐቃቤ ህግና ጊዜያዊ ፍርድ ቤት ተቋቁሟል።

የበዓሉ ታዳሚዎች አጠራጣሪ ነገር ሲያጋጥማቸው በስልክ ቁጥር 0256665056 መጠቆም እንደሚችሉ ፖሊስ ገልጿል።

የአካባቢው የመሬቱ አቀማመጥ ዳገታማ፣ ቁልቁለታማና ጠመዝማዛ በመሆኑ አሽከርካሪዎች የትራፊክ ህግና ደንብ አክብረው በማሽከርከር ከአደጋ እንዲጠበቁ ተብሏል።

ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 19 ቀን 2014 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ከጨለንቆ ከተማ እስከ ቀርሳ ከተማ ባለው ዋናው የተሸከርካሪ መንገድ ላይ ከባድ መኪና ማለፍ የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ አሳስቧል።

#ENA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ሶማሌክልል : በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል በኩል ሀገርን ሊዳፈር የሞከረው የአልሸባብ የሽብር ቡድን በክልሉ ልዩ ኃይል የማያዳግም ፣ ሁሌም የማይረሳው አስተማሪ ቅጣት መቀጣቱ ይታወቃል።

ባለፉት ቀናት በአፍዴር ዞን ቆህሌ ወረዳ በሁልሁል ንዑስ ቀበሌ ላይ ሰርጎ በገባው አልሸባብ ላይ በተካሄደው ጠንካራ ኦፕሬሽን ድል ያደረገው የሶማሌ ልዩ ኃይል ለሌላ ግዳጅ ደግሞ ወደ ሀገሪቱ ድንበር ተሸኝቷል።

በሌላ መረጃ ፦ የሶማሊያ ፌዴራሉ መንግስት ባልፈው ሳምንት የአልሸባብ የሽብር ቡድን ከባኮል ግዛት ከፍቶት በነበረው ጥቃት ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች የምግብ እና የመድሃኒት ድጋፎችን ልኳል። አካባቢው በድርቅም የተጎዳ ነው። ባኮል በ420 ኪ/ሜ ከሞቃዲሹ የሚርቅ ሲሆን ከኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ጋር የሚዋሰን የሀገሪቱ ክፍል ነው።

Photo Credit : Somali Region Communication

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ🇪🇹

የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ሌሊት በሚደረጉ ተጠባቂ ውድድሮች ፍፃሜውን የሚያገኝ ይሆናል።

በዛሬው የመጨረሻ የውድድር ቀን የሀገራችን ልጆች የሚሳተፉባቸው ውድድሮች ይካሄዳሉ።

🏟️ የወንዶች 5,000 ሜትር #ፍፃሜ

🇪🇹 ሰለሞን ባረጋ
🇪🇹 ሙክታር እድሪስ
🇪🇹 ዮሚፍ ቀጀልቻ

(ሰዓት - ሌሊት 10:05)

🏟️ የሴቶች 800 ሜትር #ፍፃሜ

🇪🇹 ድርቤ ወልተጂ

(ሰዓት - ሌሊት 10:35)

ድል ለሀገራችን ኢትዮጵያ 🇪🇹 !!

@tikvahethsport @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ🇪🇹 የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ሌሊት በሚደረጉ ተጠባቂ ውድድሮች ፍፃሜውን የሚያገኝ ይሆናል። በዛሬው የመጨረሻ የውድድር ቀን የሀገራችን ልጆች የሚሳተፉባቸው ውድድሮች ይካሄዳሉ። 🏟️ የወንዶች 5,000 ሜትር #ፍፃሜ ፦ 🇪🇹 ሰለሞን ባረጋ 🇪🇹 ሙክታር እድሪስ 🇪🇹 ዮሚፍ ቀጀልቻ (ሰዓት - ሌሊት 10:05) 🏟️ የሴቶች 800 ሜትር #ፍፃሜ ፦ 🇪🇹 ድርቤ ወልተጂ (ሰዓት …
#ተጀመረ

እጅግ በጉጉት የሚጠበቀው የወንዶች 5000 ሜትር ፍፃሜ ውድድር ተጀምሯል።

ውድድሩ ፍጥነትን ከጥንካሬ ጋር አዳምሮ የሚጠይቅ ነው።

ሀገራችን በውድድሩ ፦

🇪🇹 ሙክታር እድሪስ
🇪🇹 ዩሚፍ ቀጀልቻ
🇪🇹 ሰለሞን ባረጋ ተወክላለች።

ትላንት ለሊት በሴቶች 5 ሺህ ሜትር ከከፍተኛ የቡድን ስራ ጋር የተመዘገበው ድል ትልቅ የሞራል ስንቅ እንደሚሆናቸው አንጠራጠርም።

ድል ለሀገራችን 🇪🇹❤️ !

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
3 ዙር ይቀራል ! የወንዶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር እጅግ ፈጣን ከፍተኛ ፉክክር እየተካሄደባት ነው። የሀገራችን ልጆች ከመሪዎቹ በቅርብ ርቀት በመሆን ባለድል ለመሆን እየተፋለሙ ነው። @tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

በወንዶች 5 ሺህ ሜትር ድል አልቀናንም፦

🇪🇹 ዩሚፍ ቀጀልቻ 8ኛ
🇪🇹 ሰለሞን ባረጋ 12ኛ
🇪🇹 ሙክታር እድሪስ 13ኛ ሆነው አጠናቀዋል።

በ10 ሺህ ሜትር ፍፃሜ ውድድር ያልተገኘው ድል በዚህኛው ውድድር ይገኛል ተብሎ ተጠብቆ ነበር፤ ነገር ግን የወንዶች 5 ሺህ ሜትር እንደተጠበቀው አልሆነም።

የውድድሩ የወርቅ፣ ብር እና ነሀስ ባለድሎች ፦

1ኛ ኖርዌይ 🥇
2ኛ ኬንያ 🥈
3ኛ ዩጋንዳ 🥉

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተጀመረ ሀገራችን በድርቤ ወልተጂ የተወከለችበት የ800 ሜትር የሴቶች #ፍፃሜ ውድድር ተጀምሯል። ድል ለሀገራችን 🇪🇹❤️ ! @tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ🇪🇹

በ800 ሜትር የሴቶች ፍፃሜ ብቸኛዋ የሀገራችን ተወካይ ድርቤ ወልተጂ አራተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች። ነሀስ ለማግኘት ከፍተኛ ትግል ነው ያደረገችው 👏

ውድድሩን ፦

1ኛ አሜሪካ 🥇(ወርቅ)
2ኛ እንግሊዝ 🥈(ብር)
3ኛ ኬንያ 🥉(ነሀስ) በመሆን አጠናቀዋል።

ሀገራችን #ኢትዮጵያ በተለይም #በሴቶች ከፍተኛ ድል ያስመዘገበችበት የኦሪገን ዓለም ሻምፒዮና በዚህ አብቅቷል።

@tikvahethsport