TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከዓለም ዙሪያ 🌍

➡️ #ሶማሊያ ፦ በሶማሊያ እየተባባሰ ያለው የድርቅ ሁኔታ ለምግብ እጦት እና ለውሃ እጥረት የተጋለጠው ህዝብ ቁጥር 8 ሚሊየን ሊደርስ ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋትን ፈጥሯል። አሁን ላይ በሀገሪቱ ያለው ድርቅ በገጠር 66 ወረዳዎችና ሰፊ አካባቢዎች ክፉኛ መቷል።

➡️ #ዩክሬን ፦ ዩክሬን በጦርነቱ ምክንያት 243 ህጻናት መሞታቸውን እና 444 ህፃናት መቁሰላቸውን አረጋግጫለሁ ስትል አስታውቃለች።

➡️ #ግብፅ ፦ የግብፅ ፍርድ ቤት በቀድሞው የፕሬዚዳንት እጩ አብደል ሞኒም አቡል ፎቱህ እና በሙስሊም ወንድማማች ቡድን ውስጥ ያሉ ታዋቂ ግለሰቦችን " የሀሰት ዜና በማሰራጨት " እና መንግስትን ለመገልበጥ አሲረዋል በሚል በእስራት እንዲቀጡ ወስኗል። አቡል ፎቱህ 70 ዓመታቸው ሲሆን የ15 አመት እስራት ተፈርዶባቸዋል፣ መሐመድ አል-ካሳስ የአቡል ፎቱህ " Strong Egypt Party " ምክትል ኃላፊ የ10 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል፣ እንዲሁም የ15 አመት እስራት የተፈረደባቸው የወንድማማችነት የቀድሞ የበላይ መሪ ማህሙድ ኢዛት ሲሆኑ እሳቸው ቀደም ሲልም በሌሎች ክሶች የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው ነበር።

➡️ #ሱዳን ፦ የሱዳኑ ወታደራዊ መሪ ጄኔራል አብደል ፈታህ አል ቡርሃን ጥቅምት 25 የተደረገውን መፈንቅለ መንግስት ተከትሎ ተጥሎ የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መነሳቱን አሳውቀዋል። ቡርሃን " የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በአገር አቀፍ ደረጃ ተነስቷል " ብለዋል።

➡️ #ሩስያ ፦ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ የዩክሬን #ዶንባስ ግዛትን ነፃ ማውጣት ለሞስኮ ምንም ቅድመ ሁኔታ የሌለው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን ገልፀው ሌሎች ግዛቶች የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን ለራሳቸው መወሰን አለባቸው ብለዋል።

#ቲአርቲ #AJ #ኤፒ #SNTV

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በዳግማዊ ምኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታል የተገነባው የኩላሊት እጥበት ማዕከል ተመረቀ።

ማዕከሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ነው የተመረቀው።

ለኩላሊት ህመምተኞች እፎይታን ይሰጣል ተብሎ የሚጠበቀው ዛራ ለምርቃት የበቃው በዳግማዊ ምኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ የተሰራው የኩላሊት እጥበት ማዕከል ቀድሞ #በሁሉም የመንግስት ሆስፒታሎች ይሰጥ የነበረውን አገልግሎት #በአምስት_እጥፍ ያሳድገዋል ተብሏል።

የኩላሊት እጥበት ማዝእከሉ የከተማ አስተዳደሩና የአብ ሜዲካል ሴንተር በትብብር የተሰራው መሆኑ ተገልጿል።

Via AA Mayor Office

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update #ችሎት

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ፤ " ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት " ወንጀል ተጠርጥሮ በእስር ላይ በሚገኘው በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ የ10 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል።

የጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ የምርምራ ጊዜውን የፈቀደው የተከሳሽ ጠበቃ ያቀረቡትን መከራከሪያ እና የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ነው።

የምርመራ ጊዜው ከግንቦት 19 ቀን 2014 ጀምሮ የሚታሰብ መሆኑን ችሎቱ ገልጿል። 

በአዳራሽ በኩል በተሰየመው በዛሬው ችሎት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከጠበቃው ጋር በአካል ቀርቦ ሂደቱን መከታተሉን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገፅ (www.ethiopiainsider.com) አስነብቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba በዳግማዊ ምኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታል የተገነባው የኩላሊት እጥበት ማዕከል ተመረቀ። ማዕከሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ነው የተመረቀው። ለኩላሊት ህመምተኞች እፎይታን ይሰጣል ተብሎ የሚጠበቀው ዛራ ለምርቃት የበቃው በዳግማዊ ምኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ የተሰራው የኩላሊት እጥበት ማዕከል…
#የኩላሊት_እጥበት_ማዕከል

በዳግማዊ ምኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታል የተገነባው የኩላሊት እጥበት ማዕከል በተመረቀበት ወቅት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የተናገሩት ፦

" ሰው በሚያውቀው በተማረበት በርካታ ድንቅ ስራ ሊሰራ እንደሚችል ዛሬ አይቻለሁ፤ ባየሁትም ነገር ተደስቻለሁ።

ኢትዮጵያ ውስጥ ፕሮፌሽናሊዝም ጠፍቶ በመቆየቱ ምክንያት ማየት የሚገባንን ነገር ለብዙ ጊዜ ማየት ሳንችል ቆይተናል።

በምንችለው በተማርነው ሁላችንም አስተዋፅኦ ማድረግ አለብን።

ለከተማ አስተዳደሩም እንደ አዲስ ሲዋቀር ከተሰጡት ተልእኮ ውስጥ አንዱ የጤና ስራ ማስፋፋት ነው አሁን ተስፋ ሰጪ ነገሮችን ማየት ችለናል።

ሆስፒታሎች ንፁህና ለሁሉም ሰው የሚስማማ መሆን አለባቸው፤ መኖርያዎች ከተማዋ ባጠቃላይ ንፁህና ያማሩ እንዲሁም አረንጓዴ መሆን አለባቸው።

ለውበት ለአረንጓዴነት ለንፅህና ቢያንስ የገባን ሰዎች እንተባበር። ሌሎች ጊዜ ወስዶ ይገባቸዋል፤ ዋናው ፍርድ ቤትና ዳኛ ትውልድ ነው ፤ትውልድ ይፈርዳል። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#የኩላሊት_እጥበት_ማዕከል በዳግማዊ ምኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታል የተገነባው የኩላሊት እጥበት ማዕከል በተመረቀበት ወቅት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የተናገሩት ፦ " ሰው በሚያውቀው በተማረበት በርካታ ድንቅ ስራ ሊሰራ እንደሚችል ዛሬ አይቻለሁ፤ ባየሁትም ነገር ተደስቻለሁ። ኢትዮጵያ ውስጥ ፕሮፌሽናሊዝም ጠፍቶ በመቆየቱ ምክንያት ማየት የሚገባንን ነገር ለብዙ ጊዜ ማየት ሳንችል ቆይተናል። በምንችለው በተማርነው…
#የኩላሊት_እጥበት_ማዕከል

በዳግማዊ ምኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታል የተገነባው የኩላሊት እጥበት ማዕከል በተመረቀበት ወቅት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የተናገሩት ፦

" የኩላሊት ህመም የጤና ስርዓቱን እየፈተነ ያለ ህመም በመሆኑ ምክንያት የከተማ አስተዳደሩ ባለፉት ሁለት አመታት ምንም ገቢ የሌላቸውንና አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች በሁሉም የመንግስት ሆስፒታሎች ነፃ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል። በዚህም በሁለቱ አመታት 24 ሚሊየን ብር ያህል ድጎማ አድርጓል።

አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የመንግስትና የግሉ ዘርፍ በአጋርነት መስራት አስፈላጊነት ታምኖበት ህግ ማእቀፍ ወጥቶለት እየተተገበረ ነው። መቀመጫውን በአሜሪካ ያደረገውን የአብ ሜዲካል ሴንተር ላበረከተው አስተዋፅኤ አድናቆቴን እገልፃለሁ።

ይህ የኩላሊት መድከም ላለባቸው ዜጎች ትልቅ የምስራች ነው ፤ ሌሎችም ተጨማሪ አገልግሎቶችን እናሰፋለን።

በተጨማሪም ዳግማዊ ምኒሊክ ሆስፒታል ትልቁና ዘመናዊ የአይን ህክምና ማእከል ሆኖ እንዲወጣ በአዲሱ አመት ለህዝባችን አዲስ ምስራች እናበስራለን።

በአጠቃላይ የከተማ አስተዳደሩ አዲስ አበባን የጤና ማእከል ለማድረግ 24 ቦታዎችን ለግል ዘርፉ የሰጠ ሲሆን አስተዳደሩ በራሱ አቅም ደግሞ ሶስት ሆስፒታሎችን በጀት መድቦ እየገነባ ነው።ነባር ሆስፒታሎችን የማደስም ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ' ስንፈልግሽ ትመጫለሽ ' በሚል እንደፈቷት ነግራኛለች " - አቶ ለሚ ታዬ

የ " ፊንፊኔ ኢንተግሬትድ ብሮድካስቲንግ " የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኛ ሰቦንቱ አህመድ ዛሬ ረፋዱን ከእስር መለቀቋን የጣቢያው ዋና ዳይሬክተር ለሚ ታዬ ተናግረዋል።

ጋዜጠኛ ሶቦንቱ የተለቀቀችው በቢሾፍቱ ከተማ ከሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ መሆኑን ገልጸዋል።

ጋዜጠኛ ሶቦንቱ በፖሊስ ቁጥጥር የዋለችው ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ግንቦት 18/2014 አመሻሽ ላይ ከስራ ቦታዋ ስትወጣ መሆኑን በወቅቱ ተገልጾ ነበር።

በ " ፊንፊኔ ኢንተግሬትድ ብሮድካስቲንግ " ቴሌቪዥን ጣቢያ ዜና አንባቢ እና የመዝናኝ ፕሮግራም አዘጋጅ የሆነችው ሰቦንቱ በማግስቱ ወደ ቢሾፍቱ ከተማ መወሰዷን የጣቢያው ዋና ዳይሬክተር ተናግረው ነበር።

ያለፉትን ሶስት ቀናት በእስር ያሳለፈችው ሰቦንቱ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 22 ከጠዋቱ አራት ሰዓት ተኩል ገደማ በዋስ መለቀቋን አቶ ለሚ ገልጸዋል።

ጋዜጠኛዋ ከእስር ከተለቀቀች በኋላ በስልክ እንዳነጋገሯት የገለጹት የቴሌቪዥን ጣቢያው ዋና ዳይሬክተር ፖሊስ " ስንፈልግሽ ትመጫለሽ " በሚል መፈታቷን እንደነገረቻቸው አስታውቀዋል።

ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር (www.ethiopiainsider.com)

@tikvahethiopia
#Ashewa

አሸዋ ቴክኖሎጂ የድጅታል ኢኮኖሚው ላይ የሚሰራ የዘልማዱን ግብይት በአፍሪካ ላይ የሚቀይር፣ ህይወት የሚያቀል፣ የሚያዘምን፣ የሚያሻግር ነው። ባሁኑ ሰአት በአገራችን ያለውን የንግድ ሰንሰለት ችግር ሊቀርፍ፣ አምራቹን በቀጥታ ከሸማቹ ጋር ከኑሮ ውድነት ሊገላግል ብዙ የክፍያ እና ደሊቨሪ አማራጮችን ይዞ በኢኮሜርሱ ዘርፍ በኩል ስራውን መጀመሩን ስናበስራችሁ ትልቅ ኩራት ይሰማናል።

ግዙ ሽጡ በአዲስ አበባ ላይ https://bit.ly/3smsyrx

ድርጅቱ ላይ ኢንቨስት ለማድረግ እና ትርፍ ተካፋይ ለመሆን Ashewatechnology.com
ስልክ ፦ 0976005500 or 0976005100

Join our telegram channel
t.me/ashewatechnology
#አቢሲንያ_ባንክ

Be A Legend!

Pay with your BoA Visa card like Drogba!

የአቢሲንያ ባንክን ትክክለኛ የቴሌግራም ቻነል ይቀላቀሉ! https://publielectoral.lat/BoAEth
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #ችሎት ፍርድ ቤት በብርጋዴል ጀኔራል ተፈራ ማሞ ጉዳይ ለግንቦት 22 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ። የአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት አመልካች የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ዘርፍና በተጠሪ ብርጋዴል ጄኔራል ተፈራ ማሞ መካከል በነበረው የጊዜ ቀጠሮ ጉዳይ ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ሀሳብ አዳምጧል። ፍርድ ቤቱም ፤ ፖሊስ ከጠየቀው የ14 ቀን ውስጥ 10 ቀን በመፍቀድ ለግንቦት 22 ቀን…
#Update #ችሎት

የአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ ግንቦት 22/2014 ዓ/ም በዋለው ችሎት የብርጋዴል ጀኔራል ተፈራ ማሞን ጉዳይ ተመልክቷል።

የመርማሪ ቡድኑ ምርመራዬን ስላልጨረስኩ የተለያዩ ማስረጃዎችን ከባንክ፣ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት፣ ከኢሳት እና ከሌሎች ተቋማት የምንሰበስባቸው መረጃዎች ስላሉ የ14 ቀናት ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል።

የተከሳሽ ጠበቃ በበኩላቸው አስፈላጊ ናቸው የተባሉ መረጃዎችን ለመሰብሰብ መረጃው የሚሰበሰብባቸው ተቋማት የመንግስት ስለሆኑ ያን ያህል ጊዜ ስለማይዎስዱ ተከሳሽ በውጭ ሆነው እንዲከራከሩ በዋስትና እንዲለቀቁ ጠይቀዋል።

የምርመራ ቡድኑ የጠበቃውን በዋስትና ይለቀቁልኝ ክርክር በመቃዎም ተከሳሹ ከእስር ቢለቀቁ የተለያዩ ማስረጃዎችን ያጠፉብናል በዚህ ምክንያት በእስር ሊቆዩ እና የጠየቅነው የጊዜ ቀጠሮ እንዲፈቀድላቸው ጠይቋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶ የጊዜ ቀጠሮ መስጠቱን ስላመነበት የምርመራ ቡድኑ ከጠየቀው የ14 ቀን ውስጥ 4 ቀን ቀንሶ 10 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ በመፍቀድ ለሰኔ 2/2014 ዓ/ም ቀጠሮ ሰጥቷል።

ምንጭ፦ የአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ በፌደራል ፖሊስ አባላት ተያዘች። " ሮሃ ሚዲያ " የተሰኘው የዩቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት የሆነችው መዓዛ መሐመድ ዛሬ ጠዋት በፖሊስ ተይዛ መወሰዷን የስራ ባልደረባዋ እና ጓደኛዋን ዋቢ አድርጎ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገፅ " ዘግቧል። የጋዜጠኛዋ እስር በኢትዮጵያ ከሰሞኑ በጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር የዋሉ ጋዜጠኞች እና የመገናኛ ብዙኃን ሰራተኞችን ቁጥር 19 አድርሶታል።…
#Update #ችሎት

ጋዜጠኛ መዓዛ መሃመድ ፍርድ ቤት ቀርባለች።

ባሳለፍነው ቅዳሜ በፀጥታ ሃይሎች የተያዘችው መዓዛ መሃመድ ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ነው የቀረበችው።

ፖሊስ በመዓዛ መሃመድ ላይ " ሁከትና ብጥብጥ ማስነሳት " የሚል ክስ ያቀረበባት ሲሆን በጉዳዩ ላይም መረጃ ለማሰባሰብ የ14 ቀን ቀጠሮ ይሰጠኝ ሲል ጠይቋል።

የጋዜጠኛዋ ጠበቆች ጋዜጠኛዋ ሰራች የተባለው ወንጀል ተፈፅሞ ቢሆን እንኳን ጉዳዩ ሊታይ የሚገባው በመገናኛ ብዙሀን አዋጅ ነው ፤ በእስር እንድትቆይ ህጉ አይፈቅድም ሲሉ ተከራክረዋል።

አክለውም ጋዜጠኛዋ ከወራት በፊት ታስራ ማስረጃ ሊቀርብባት ባለመቻሉ ነፃ መደረግዋን አስታውሰው አሁንም ሞጋች ጋዜጠኛ መሆኗ እንጂ የሰራችው ወንጀል የለም ይሄንን ፍ/ቤቱ ሊመለከተው ይገባል ሲሉ ሞግተዋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር አዳምጦ የ7 ቀናት የምርመራ ጊዜ መፍቀዱን የምትሰራበት " ሮሃ ሚዲያ " ዘግቧል።

በሌላ በኩል ፦ በጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬ ላይ የሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ ተፈቅዷል።

@tikvahethiopia