TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሩስያ ያቀደችውን ታሳካለች " - ቭላድሚር ፑቲን የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ከፈረንሳዩ አቻቸው ኢማኑኤል ማክሮን ጋር 90 ደቂቃ ያህል የፈጀ የስልክ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅት ፑቲን ሞስኮ ዩክሬን ውስጥ በምታካሂደው ዘመቻ ያቀደችውን ታሳካለች ብለዋል። ፑቲን አስተዳደራቸው የኪዬቭን ወታደራዊ እንቅስቃሴ በማስቆም ለሩሲያ ደኅንት ወታደራዊ ስጋት እንዳትሆን እናደርጋለን ስለማለታቸው…
" ከእኔ ጋር ቁጭ ብለህ ተነጋገር " - ቮልድሚር ዜኔንስኪ

የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ከሩሲያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ጋር በቀጥታ ለመነጋገር ጠያቄ አቀረቡ።

ዜሌንስኪ ይህን ጥያቄ ያቀረቡት ዛሬ አመሻሽ ላይ በሰጡት መግለጫ ነው።

ፕሬዜዳንቱ ፤ " ጦርነቱን ለማቆም #ብቸኛው አማራጭ ከፑቲን ጋር በቀጥታ መነጋገር ነው " ብለዋል።

ዜሌንስኪ ለፑቲን ባስተላለፉት መልዕክት ፥ " ሩሲያን እያጠቃን አይደለም፤ ለማጥቃትም እቅዱ የለንም። ከእኛ ምንድነው የምትፈልገው ? መሬታችንን ትልቀቅ " ብለዋል።

ፕሬዜዳንቱ አክለው ፤ " ከእኔ ጋር ቁጭ ብለህ ተነጋገር። 30 ሜትር ሳይርቅ " በማለት ፑቲን ከፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ጋር በረዥሙ ጠረጴዛቸው ፊት ለፊት ያደረጉትን ንግግር አስታውስዋል።

ዜሌኒስኪ በመግለጫቸው ላይ #ምዕራባውያን ተዋጊ አውሮፕላኖችን እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል።

" የአየር ክልሉን መዝጋት የማትችሉ ከሆነ ፤ አውሮፕላኖችን ስጡኝ " ሲሉ ነው ዜሌንስኪ የጠየቁት።

ምዕራባውያን የሩሲያ ተዋጊ አውሮፕላኖችን በዩክሬን ላይ ጥቃት እንዳያደርሱ የዩክሬንን አየር ክልል እንዲዘጉ ሲጠየቁ ቆይተዋል።

ዜሌንስኪ ፤ " በቀጣይ ሩሲያ ላትቪያ ፣ ሊትዌኒያ እና ኢስቶኒያን ልትወር ትችላለች " ሲሉ መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

በሌላ መረጃ ፥ የሩስያ እና ዩክሬን ሁለተኛው ዙር የሰላም ድርድር ዛሬ በቤላሩስ ተጀምሯል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከእኔ ጋር ቁጭ ብለህ ተነጋገር " - ቮልድሚር ዜኔንስኪ የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ከሩሲያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ጋር በቀጥታ ለመነጋገር ጠያቄ አቀረቡ። ዜሌንስኪ ይህን ጥያቄ ያቀረቡት ዛሬ አመሻሽ ላይ በሰጡት መግለጫ ነው። ፕሬዜዳንቱ ፤ " ጦርነቱን ለማቆም #ብቸኛው አማራጭ ከፑቲን ጋር በቀጥታ መነጋገር ነው " ብለዋል። ዜሌንስኪ ለፑቲን ባስተላለፉት መልዕክት ፥ " ሩሲያን…
#ተስማምተዋል

ዛሬ ሀሙስ በቤላሩስ በተካሄደው 2ኛ ዙር ውይይት ሩስያ እና ዩክሬን ሰላማዊ ዜጎች ከዩክሬን የውጊያ ቀጠና የሚወጡበትን መንገዶች ለማመቻቸት ተስማምተዋል።

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ረዳት የሆኑት ሚካሂል ፖዶሊያክ " 2ቱም ወገኖች በጊዜያዊ የተኩስ አቁም የሰብአዊነት ኮሪደሮችን በጋራ ማቋቋም ላይ መግባባት ላይ ደርሰዋል። እነዚህንም ኮሪደሮችን ለማደራጀት ሩሲያ እና ዩክሬን በቅርቡ የግንኙነት እና የትብብር መንገዶችን ይፈጥራሉ " ሲሉ ተናግረዋል።

የሩሲያው ልዑካን ቡድን መሪ ቭላድሚር ሜዲንስኪ ያለውን ሂደት አረጋግጠዋል። ሁለቱ ወገኖች የሲቪሎችን ህይወት ለማዳን " ዋናውን ጉዳይ " እንደፈቱ ተናግረዋል።

ተደራዳሪዎቹ በወታደራዊ እና በሰብአዊ ጉዳዮች እንዲሁም ወደፊት በሚደረጉ የፖለቲካ ዕርቅ ጉዳዮች ላይ የጋራ አቋም መያዛቸውንም ቭላድሚር ሜዲንስኪ ገልፀዋል።

የዩክሬን ወገን ድርድሩ የሚጠብቁትን ውጤት እንዳላመጣ ገለፀው የሚቀጥለው ዙር ድርድር በቅርብ ጊዜ ይካሄዳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ማሳወቃቸውን አር ቲ ኒውስ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
ሩብል📉

የምዕራባውያን ማዕቀብ እጅጉን የበረታባት ሩስያ የመገበያያ ገንዘቧ የሆነው #ሩብል ከአሜሪካ #ዶላር አንፃር በእጅጉ ቀንሷል።

አሁን ላይ 1 የሩስያ ሩብል $0.0085 ከ1 የአሜሪካ ሳንቲም በታች ወይም አንድ የአሜሪካ ዶላር በ117.18 የሩስያ ሩብል እየተመነዘረ ነው።

አንድ የአሜሪካ ዶላር በሩስያ ሩብል ሲመነዘር ፦

• ከአንድ ወር በፊት : 76.2 ሩብል
• ከአንድ ሳምንት በፊት : 81.4 ሩብል
• ከአንድ ቀን በፊት : 108.5 ሩብል
• አሁን : 117.18 ሩብል

ምዕራባውያን አንዳንድ የሩሲያ ባንኮች #ስዊፍት የተሰኘውን ዓለም አቀፍ የገንዘብ ማዘዋወሪያ ስርዓትን እንዳይጠቀሙ አግደዋቸዋል።

እገዳውን ተከትሎ ነው የሩሲያው ሩብል በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ደረጃ ዋጋው የወረደው።

ምዕራባውያን በሩስያ ባንኮች ላይ ጠንካራ የሆኑ ማዕቀቦችን ጥለዋል ፤ የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክም 630 ቢሊዮን ዶላር ከማንቀሳቀስ ታግዷል።

አሁንም የምዕራባውያኑ ሀገራት በሩስያ ላይ እየጣሉት ያለው ጠንካራ ማዕቀብ የሩስያን ኢኮኖሚ እንደሚያሽመደምደው እና ከዓለም አቀፉ ስርዓት እንደሚገፋው ተንታኞች እየተናገሩ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዐቢይ_ፆም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዐቢይ ፆምን በማስመልከት ፥ " መላው ኦርቶዶክሳዊያን ወርሃ ጾሙን ፈጣሬ ዓለማት መድሃኔዓለም ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ፍጹም ምህረቱን እንዲያወርድልን በመጸለይ ልናሳልፈው ይገባል " ስትል መንፈሳዊ መልዕክቷን አስተላልፋለች። አራተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ…
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ አርፈዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

የቅዱስነታቸውን ሽኝት በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ተሰብስቦ በሚያስተላልፈው ውሳኔና በሚያወጣው መርሐ ግብር መሰረት የሚፈጸም መሆኑን የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት አሳውቋል።

አራተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ህመም አጋጥሟቸው በሀሌሉያ ሆስፒታል በህክምና ላይ እንደነበሩ መገለፁ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#DrAbiyAhmed

የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ በአራተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ እረፍት የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ " አራተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ማረፋቸውን በመስማቴ ጥልቅ ኀዘን ተሰምቶኛል። " ብለዋል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ፥ ተለያይተው የነበሩት ሁለቱ ሲኖዶሶች አንድ እንዲሆኑ ቅዱስነታቸው ወሳኙን ሚና መጫወታቸውን አስታውሰዋል።

" ነገሮችን በአርምሞ እየተመለከቱ ሀገራችንን በጸሎት ያግዙ ነበር። " ያሉት ጠቅለይ ሚኒስትሩ " በዚህ ወቅት እርሳቸውን ማጣት ከባድ ጉዳት ነው። ለሁላችንም መጽናናትን እመኛለሁ " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ አርፈዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። የቅዱስነታቸውን ሽኝት በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ተሰብስቦ በሚያስተላልፈው ውሳኔና በሚያወጣው መርሐ ግብር መሰረት የሚፈጸም መሆኑን የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት አሳውቋል። አራተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ…
#Update

ቅዱስ ሲኖዶስ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር እሑድ እንዲፈጸም ወስኗል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ 4ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር እሑድ ዕለት እንዲፈጸም ውሳኔ አሳልፏል፡፡

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚከናወን ተገልጿል።

@tikvahethiopia
Situation_Report_Northern_Ethiopia_Humanitarian_Update_3_Mar_2022.pdf
3.1 MB
#UNOCHA

PDF የሰሜን ኢትዮጵያ ወቅታዊ የሰብዓዊ ድጋፍ ሁኔታ ሪፖርት።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Situation_Report_Northern_Ethiopia_Humanitarian_Update_3_Mar_2022.pdf
#SituationReport

#Tigray #Amhara #Afar📍

የሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ የተመድ ሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ የዚህን ሳምንት ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።

ዋና ዋና ነጥቦች ፦

#Afar📍

- በአፋር ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች ያለው ሁኔታ ተባብሶ ቀጥሏል። በተለይም በራህሌ፣ ኢሬብቲ፣ ኬልቤቲ ዞን (ዞን 2) ውስጥ የትጥቅ ግጭቶች መኖራቸው ሪፖርት ተደርጓል።

- በአፋር እየተካሄደ ያለው ግጭት የሰብአዊ ድጋፍ መርሃ ግብሮችን እያደናቀፈ ፤ የሲቪሎችን ህይወት፣ ደህንነታቸውን አደጋ ላይ እየጣለ እና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የሚሄደው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥርም የሰብአዊ ፍላጎቶችን እየጨመረው ይገኛል።

- በአፋር ክልል ዞን 4 መረጋጋት በመፈጠሩ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የውስጥ ተፈናቃዮች ወደ ቀደመው ቀያቸው ተመልሰዋል።

- በዞን 2 በቀጠለው ግጭት ምክንያት ተጨማሪ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው መፈናቀላቸውን የክልሉ ባለስልጣናት አሳውቀዋል። ተፈናቃዮቹ በተለይም ከአባላ፣ ኢረብቲ፣ በረሃሌ፣ መጋሌ እና ዳሎል ወረዳዎች መሆናቸው ተገልጿል። አብዛኞቹ ተፈናቃዮች በአሁኑ ወቅት በዳሎል፣ አፍዴራ፣ ሲልሳ/ጉያህ እና ሰመራ እየተጠለሉ ሲሆን አንዳንድ ተፈናቃዮች ደግሞ ራቅ ባሉ እና ለመድረስ አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ነው ያሉት።

- የተመድ አጋሮች በተደራሽነት ውስንነት ምክንያት በዞን 2 የሚገኙትን የተፈናቃዮች ቁጥር ማረጋገጥ አልቻሉም።

- ቁጥራቸው ያልተረጋገጠ ከአፋር የተፈናቀሉ ተፈናቃዮች በትግራይ ክልል በሚገኙ ጥቂት ትምህርት ቤቶች ይገኛሉ።

#Tigray 📍

- አሁን ላይ የ ሰመራ - አብአላ - መቐለ መስመር መዘጋት ወደ ትግራይ የሚደርሰውን የሰብአዊ አቅርቦት የበለጠ አባብሶታል። ሰብዓዊ አቅርቦቱ ከታህሳስ አጋማሽ በፊት ከተፈቀደው ውስን አቅርቦት ጋር ተዳምሮ በዋነኛነት ቀደም ባሉት አስተዳደራዊ ርምጃዎች ምክንያት ሰብዓዊ አቅርቦቱ ከሚያስፈልገው በታች ነበር።

- እኤአ ከሃምሌ 12 ጀምሮ አስፈላጊውን የሰብአዊ አቅርቦት ከያዙ 16,500 የጭነት መኪናዎች ውስጥ 8 በመቶው ብቻ ትግራይ ገብተዋል። በዚህም የተመድ ሰብአዊ አጋሮች ተግባራቸውን መቀነሳቸውን ቀጥለዋል።

- ይህ ሪፖርት በተዘጋጀበት በዚህ ሳምንት የሰብአዊ ድጋፍ አድራጊ ድርጅቶች 47 ሜትሪክ ቶን የህክምናና የስነ ምግብ አቅርቦቶችን ወደ ትግራይ ክልል መዲና መቐለ በበረራ አድርሰዋል። ይህ እኤአ ከጥር 24 አንስቶ በበረራ ወደ ትግራይ የገባውን አጠቃላይ አቅርቦት 144 ሜትሪክ ቶን አድርሶታል።

- በዚህ ሳምንት ወደ ትግራይ ከቀረበው አቅርቦት መካከል 10 ሜትሪክ ቶን የተመጣጠነ ምግብ (Ready to Use Therapeutic Food - RUTF) ይገኝበታል። ይህም ከታህሳስ አጋማሽ ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የገባ ሲሆን በመቐለ፣ በምስራቅ እና ደቡብ-ምስራቃዊ ዞን ይከፋፈላል። ከፍተኛ የሆነ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ያለባቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናትን ለመንከባከብ ይውላል።

- ባለፉት ሳምንታት ወደ መቐለ የደረሱ የህክምና ቁሳቁሶች ይህ ሪፖርት በተዘጋጀበት ሳምንት ወደ ምስራቅ ዞን ውቅሮ እና ዓዲግራት አጠቃላይ ሆስፒታሎች፣ ወደ ማዕከላይ ዞን ዓድዋ፣ አክሱም፣ አቢአዲ ጠቅላላ ሆስፒታሎች እና አክሱም ሪፈራል ሆስፒታል፣ በሰሜን ምዕራብ ዞን ወደ ስሁል ሽሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ተከፋፍለዋል።

- አሁንም የነዳጅ እጥረት ቀሪዎቹን ቁሳቁሶች ለማከፋፈል እንቅፋት እንደሆነ ነው።

- በትግራይ አሁንም የህክምና ቁሳቁሶች ችግርና የተወሰኑ አይነት መድሃኒት እጥረቶች ያሉ ሲሆን ከነዚህም መካከል HIV ላለባቸው ሰዎች ሚሰጥ መድሃኒት ይጠቀሳል፣ የHIV መመርመሪያ ኪት፣ የፀረ ራቢስ መድሃኒት፣ የኮሌራ ክትባት እጥረትም አለ።

#Amhara 📍

- በአማራ ክልል አንዳንድ ' ከትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች ' አሁንም ተደራሽ አይደሉም። በተለይም በሰሜን ጎንደር ፣ ዋግ ኽምራ እና ሰሜን ወሎ ዞኖች ያሉ አካባቢዎች እጅግ አሳሳቢ ሲሆኑ አልፎ አልፎ በሚከሰቱት ግጭቶች ምክንያት ሰዎች ወደ ዝቋላ ፣ ሰቆጣ ፣ ቆቦ እና ዛሪማ መፈናቀላቸውን የሚገልፁ ሪፖርቶች አሉ።

- በሰቆጣ እና ዝቋላ ከ40 ሺ በላይ ተፈናቃዮች እንደሚኖሩ ይገመታል።

- በአማራ ክልል በዘጠኝ ዞኖች እኤአ ከታህሳስ እስከ ጥር ባለው ጊዜ ውስጥ በ " Find -and - Treat " ዘመቻ ከ1 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ህጻናትን የመለየት ዘመቻ የተካሄደ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 21,804 ህጻናት ወይም 1.1 በመቶው ህጻናት በከፋ የምግብ እጥረት (SAM) ተጠቅተዋል።

- በምስራቅ አማራ እ.ኤ.አ. ከየካቲት 14 ጀምሮ በመካሄድ ላይ ባለው 'find and treat' ዘመቻ እስካሁን ምርመራ ከተደረገላቸው 293,208 ከ5 አመት በታች ህጻናት 8,160 SAM ኬዝ ወይም 2.7 በመቶና 48,118 GAM ኬዞች ወይም 16.4 በመቶ ተገኝቷል። ምርመራ ከተደረገላቸው 52,828 ነፍሰጡር እና የሚያጠቡ እናቶች ውስጥ 21,687 ሴቶች ወይም 41 በመቶው የተመጣጠነ ምግብ እጥረት አለባቸው ተብሏል።

#UNOCHA

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #UKRAINE #RUSSIA

ሩስያ ዩክሬን ላይ የጀመረችው ወታደራዊ ዘመቻ ተከትሎ በኢትዮጵያ ላይ የሚፈጠር ጫና እንደሚኖር የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እዮብ ተካልኝ ተናግረዋል።

ዶ/ር እዮብ ለፋና ብሮድካስት በሰጡት ቃል ፤ " ሩስያ እና ዩክሬን የንግድ አጋሮቻችን እንደመሆናቸው የሚፈጠር ጫና ይኖራል " ብለዋል።

" ያም ሆኖ ግን ከሀገራቱ በብዛት ኢትዮጵያ ምታስገባው ስንዴ ለዚህ ዓመት የሚበቃው ቀድሞ በመገዛቱ ተፅእኖው ፈጥኖ ላይደርስብን ይችላል " ሲሉ ሚኒስትር ዴኤታው አስረድተዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ አርፈዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። የቅዱስነታቸውን ሽኝት በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ተሰብስቦ በሚያስተላልፈው ውሳኔና በሚያወጣው መርሐ ግብር መሰረት የሚፈጸም መሆኑን የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት አሳውቋል። አራተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ…
#USA

አሜሪካ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ እረፍት የተሰማትን ሀዘን ገለፀች።

አሜሪካ 🇺🇸 በአዲስ አበባ ባለው ኤምባሲዋ አማካኝነት በ4ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ እረፍት የተሰማትን ሀዘን ገልፃለች።

ሀገሪቱ በሀዘን ላይ ላሉ ሁሉ መፅናናትን ተመኝታለች።

@tikvahethiopia
#Russia

የሩስያ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ተቆጣጣሪ ቡድን የዩክሬን ግጭትን አስመልክቶ ሀሰተኛ መረጃዎችን እያሰራጩ ነው ባላቸው የብሪቲሽ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (#ቢቢሲ) እና የራዲዮ ሊብሪቲ ድረ-ገጾች ላይ ገደብ ጥሏል።

ሩስያ የምዕራባውያን ሚዲያዎች ፤ በውጭ ሀገራት ጦርነት ለምሳሌ እንደ #ኢራቅ ባሉ እና በሙስና እጃቸው ያለባቸው የገዛ የራሳቸው ሀገራት መሪዎች ተጠያቂ ማድረግ ሳይችሉ በከፊል እና ብዙ ጊዜ ፀረ-ሩሲያ የሆነ አመለካከትን ለዓለም ያስተላልፋሉ ስትል በተደጋጋሚ ስትወቅስ ቆይታለች።

ከዩክሬን ጋር በተያያዘ የሩስያ ባለስልጣናት "ወረራ" ሚለውን ቃል የማይጠቀሙ ሲሆን የምዕራባውያን ሚዲያዎች ዩክሬን ውስጥ በሩሲያኛ ተናጋሪ ህዝቦች ላይ የሚፈፀመውን " የዘር ማጥፋት ወንጀል " ሪፖርት እንደማያደርጉ ይናገራሉ።

ሩስያ ምዕራባውያን ሚዲያዎች ላይ ገደብ ከመጣሏ በፊት ምዕራባውያኑም በሩስያ ሚዲያዎች ላይ የተለያዩ ገደቦችን ጥለዋል።

ለአብነት ዩናይትድ ኪንግደም በሩስያ የሚደገፈው " ራሺያ ቱዴይ " ቴሌቪዥን ዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ እንዳይታይ አግዳዋለች።

@tikvahethiopia
" እንቅጠራችሁ እና ዩክሬን ሄዳችሁ ከሩስያ ጋር ተዋጉልን " - የዩክሬን ኤምባሲ

ሴኔጋል ዳካር ከተማ ሚገኘው የዩክሬን ኢምባሲ በጎ ፈቃደኛ ሴኔጋላዊያን እና ሌሎችም የውጭ ሀገራት ዜጎች ወደ ዩክሬን አምርተው ከሩሲያ ጋር እየተደረገ ባለው ጦርነት እንዲዋጉ የቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል።

ይህ ማስታወቂያ ሴኔጋልን አበሳጭቷል።

የሴኔጋል ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዳካር የዩክሬን አምባሳደር ዩሪ ፒቮቫሮቭ በጉዳዩ ዙሪያ ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠርቷል።

ሚኒስቴሩ የኢምባሲው ድርጊት የሀገራት የዲፕሎማሲ ግንኙነት ዙሪያ የወጣው የቬና ድንጋጌዎችን የሚጥስ ነው ብሏል።

ኤምባሲው ወደ ዩክሬን ሄደው እንዲዋጉ ያወጣወን የቅጥር ማስታወቂያ ቆይቶ ያጠፋ ቢሆንም በቀጣይ ምን አይነት እርምጃዎችን ሊወስድ እንደሚችል ግልጽ አይደለም በሚል የሴኔጋል ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለፁን አል ዓይን ኒውስ ዘግቧል።

ሴኔጋል በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ (UNGA) ላይ የቀረበውን " ሩስያ ዩክሬንን ወራለች ፤ ወታደሮቿንም ከዩክሬን ታስወጣ " የሚለውን የውሳኔ ሃሳብ ላይ የድምጸ ተዓቅቦ ካደረጉ ሀገራት አንዷ ናት።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ አርፈዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። የቅዱስነታቸውን ሽኝት በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ተሰብስቦ በሚያስተላልፈው ውሳኔና በሚያወጣው መርሐ ግብር መሰረት የሚፈጸም መሆኑን የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት አሳውቋል። አራተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ…
#Russia

ሩስያ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ እረፍት የተሰማትን ሀዘን ገለፀች።

ሩስያ በአዲስ አበባ ባለው ኤምባሲዋ አማካኝነት በ4ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ እረፍት የተሰማትን ሀዘን ገልፃለች።

የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ እረፍት በዓለም ለሚገኙ የኦርቶዶክስ አማኞች ከባድ ሐዘን ነው ብላለች።

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ታላቅነት ማስቀጠልና መጠበቅ ውስጥ የማይተካ ሚና መጫወታቸውንም ሩስያ ገልፃለች።

ሩስያ በብፁዕነታቸው እረፍት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ሆነን እናዝናለን ብላለች።

@tikvahethiopia