TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
* Update አቶ ከድር ጁሀር የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ሆነው ተሾሙ። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት በሙሉ ድምፅ ነው ሹመታቸውን ያፀደቀው። በድሬዳዋ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዪት አቶ ከድር ጁሀር የአስተዳደሩ ከንቲባ በመሆን ቃለ መሀላ ፈፀመዋል። በሌላ በኩል ፥ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፈትህያ አደም ሆነው በሙሉ ድምፅ ተሹመዋል። የአስተዳደሩ…
#Diredawa : ድሬዳዋ ከተማ ዛሬ አዲስ መንግስት መስርታለች።

ዛሬ ከሰዓት በተካሃደው የድሬዳዋ ከተማ አዲስ መንግስት መስረታ የከተማው ምክር ቤት አቶ ከድር ጁሃርን በሙሉ ድምፅ ከንቲባ አድርጎ ሲሾም በከንቲባው የቀረቡትን የካቤኔ አባላትንም ሹመት አፅድቋል።

ሹመታቸው በምክር ቤት የፀደቀላቸው የካቢኔ አባላት የሚከተሉት ናቸው ፦

1. ም/ከንቲባና ንግድ ቢሮ - ሀርቢ ቡህ ወርሰሜ
2. የፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ/ የመንግስት ተጠሪ - ኢብራሂም ዩሱፍ
3. ፋይናንስ ቢሮ - ሱልጣን አሊይ
4. ቴክኒክና ሙያ ቢሮ - ሮቤል ጌታቸው
5. ግብርና ቢሮ - ኑረዲን አብደላ
6. ኮንስትራክሽን - ኢ/ር ጀማል ኢብራሂም
7. ጤና ጥበቃ ቢሮ - ለምለም በዛብህ
8. ፍትህ ቢሮ - አብዱሰላም አህመድ
9. መሬት ልማት ቢሮ - ሳጂድ አሊይ ሁሴን
10. ትምህርት ቢሮ - ሙሉካ መሀመድ ሁሴን
11. መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ - ኢስቂያስ ታፈሰ
12. ሴቶችና ህጻናት - ፈጡም ሙስጠፋ ሀቢብ
13. ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ - አቡበከር አዶሽ ኦልሀዬ
14. ዋናው ኦዲተር - ጫልቱ ሁሴን
15. ብዙሃን መገናኛ - አብዱሰላም መይደኔ

Credit : ድሬዳዋ ኮሚኒኬሽን

@tikvahethiopia
#DireDawa : " ሙሉ እና ጎዶሎ በሚል የተጀመረ የትራንስፖርት አገልግሎት የለም " - የት/ባለስልጣን

በት/ባለስልጣን የድ/ዳ/ቅ/ጽ/ቤት ፥ በድሬደዋ የታክሲ አገልግሎት ሙሉ ጎዶሎ በሚል
መሰጠት ስለመጀመሩ እየተሰራጨ ያለው መረጃ
#ሀሰት ነው ሲል አሳውቋል።

ቅ/መስሪያ ቤቱ የታክሲ አሽከርካሪዎች ከመሰል የሀሰት ማደናገሪያዎችበመጠበቅ አገልግሎት መስጠታቸውን እንዲቀጥሉም አሳስቧል፡፡

የሚቀየሩ የአገልግሎት አሰጣጦች ሲኖሩ ከትራፊክ ፖሊስ ዳይሬክቶሬት ጋር በመቀናጀት እንደሚወጡና ይህንንም በተቋሙ ይፋዊ የፌስ ቡክ ገፅና በሌሎች ሚዲያዎች ይፋ እንደሚደረግ አሁን ላይ ግን ምንም አይነት የሙሉ ጎዶሎ አገልግሎት እንዳልተጀመረ እና እንደማይጀመር ገልጿል።

ከሰሞኑ በከተማው የታክሲ አገልግሎት ጎዶሎና ሙሉ በሚል እየተሰጠ አንደሚገኝ ተደርጎ ምንጩ ያልታወቀ መረጃ እየተሰራጨ ይገኛል፡፡

@tikvahethiopia
#DireDawa

የድሬዳዋ ፖሊስ ማንኛውም ድሬዳዋ ከተማና ገጠር ውስጥ የሚገኝ ግለሰብ በእጁ የሚገኘውን የጦር መሳሪያ ፍቃድ ቢኖረውም ባይኖረውም በአቅራቢያው በሚገኝ የቀጠናው ፖሊስ ጣቢያ ድረስ በግንባር በመሄድ ማስመዝገብ እንዳለበት በጥብቅ አሳስቧል።

ድሬዳዋ ፖሊስ ፥ ከህዳር 2 ቀንእስከ ህዳር 3 ቀን 2014 ዓ.ም ባሉት 2 ቀናት ውስጥ ማንኛውም ግለሰብ በእጁ የሚገኘውን የጦር መሳሪያ ሳያስመዘግብ የቀረ ከሆነ በህግ አግባብ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወሰድ ገልጿል፡፡

@tikvahethiopia
#DireDawa

በድሬዳዋ አስተዳደር ከተማ እና ገጠር የሚኖር ማንኛውም ግለሰብ በእጁ የሚገኝ የጦር መሳሪያ በድሬዳዋ አስተዳደር ከተማ እና ገጠር በሚገኙ በሁሉም ፖሊስ ጣቢያዎች በግንባር ቀርቦ ማስመዝገብ እንዳለበት የድሬዳዋ ፖሊስ ማሳሰቢያ መስጠቱ ይታወሳል፡፡

ዜጎች እጃቸው ላይ የሚገኝ ጦር መሳሪያ እንዲያስመዘግቡ የተቀመጠው ቀነ ገደብ ዛሬ ህዳር 6 ቀን 2014 ዓ/ም ይጠናቀቃል።

@tikvahethiopi
#DireDawa

የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ወደ ትግል ሜዳ ለመዝመት ተዘጋጅቻለሁ ብለዋል።

ከንቲባው ዛሬ አመሻሹን በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ፥ " ሀገርን በመሥዋዕትነት መምራት ከእኛ ይጠበቃልና፤ እኔም ከሌሎች ወንድሞቼ ጋር ወደ ትግሉ ሜዳ ለመዝመት ተዘጋጅቻለሁ። በግንባር ተገኝተን ያዘጋጀነውን ስንቅ እናቀብላለን፤ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ጀግናው ሠራዊታችንን በወኔ እናበረታታለን " ብለዋል።

የአስተዳደሩ የፀጥታ ኃይሎችና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች፤ ከመቼውም ጊዜ በላይ የድሬዳዋን ሠላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ፤ የልማትና አስተዳደራዊ ሥራዎችን በሙሉ አቅማቸው ለማከናወን ተዘጋጅተዋል ሲሉም አሳውቀዋል።

አቶ ከድር ጁሀር ፥ " መላው ነዋሪዎች አካባቢያችሁን በመጠበቅ፤ ሠራዊቱን በመደገፍና፤ ወደ ግንባር በመዝመት፤ እንዲሁም በፀሎት ከጎናችን እንድትሆኑ ጥሪ አቀርባለሁ። ያለጥርጥር ኢትዮጵያ ታሸንፋለች " ሲሉ ነው በተረጋገጠ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ያሰፈሩት።

የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ወደግንባር ዘምተው ሰራዊቱን እንደሚመሩ ካሳወቁ በኃላ የተለያዩ ባለስልጣናት ፣ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ ታዋቂ የስፖርት ሰዎች ጨምሮ ሌሎችም ወደ ግንባር እንደሚዘምቱ እገለፁ መሆናቸው ይታወቃል።

#Teddy

@tikvahethiopia