TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
CSA ግቢ ውስጥ ተኩስ ነበር!

የማእከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ዛሬ ተኩስ ነበር ተብሏል። ጋዜጠኛ አሮን ማሾ ትዊተሩ ላይ እንዳሰፈረው ተኩሱ የነበረው ለህዝብና ቤት ቆጠራ የሚያገለግሉ ታብሌት ኮምፒውተሮችን ይጠብቁ በነበሩ ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት መሀከል ነበር ብሏል። ስለ ጉዳዩ ያውቁ እንደሆን የተጠየቁ ሁለት የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች "ልክ ነው፣ ግን መናገር አንችልም። ፖሊሶች መጥተው ምርመራ አርገው ሄደዋል" ብለው።

ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት/#AP/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኮሮና ቫይረስ ለተራራ ጎሪላዎች ሕይወት አስጊ ሆኗል!

የኮሮና ቫይረስ አስጊነት ተከትሎ የኮንጎ ዲሞክራሲያዊት ሪፐብሊክ ቨሩንጋ ብሔራዊ ፓርኳን እስከ ወርኃ ጁን ለቱሪስት ዘግታለች።

ሩዋንዳም በተመሳሳይ ሶስት ብሄራዊ ፓርኮችን ለቱሪስቶች እንዲሁም ለጥናት ስራዎች ዘግታለች። ኡጋንዳ ግን እንደ ሩዋንዳ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ተመሳሳይ እርምጃ አልወሰደችም።

በኡጋንዳ ፣ ሩዋንዳና ኮንጎ ጥበቃ በሚደረግላቸው ሥፍራዎች የሚገኙት የተራራ ጎሪላዎቹ ቁጥር ከ1,000 ያልበለጠ ነው።

#AP #SBS
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia