TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ምክክር ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ /ምክክር/ በ6ኛው ብሔራዊ ምርጫ የሚታገልባቸው የምርጫ ማኒፌስቶ 132 ገፅ የያዘ እና 70 አንቀፆች ያሉትን በማዘጋጀት ከነሀሴ 02 እስከ ነሀሴ 04 ቀን 2012 ዓ.ም (ለ3 ተከታታይ ቀናት) ከፍተኛ አመራሩ ውይይት አድርጎ ማሻሻያዎችን በማድረግ አፅድቋል በዚህ ጉዳይ ፓርቲው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጫ ልኳል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"በወላይታ ዞን የጸጥታ ኃይሎች በተቃውሞ ሰልፈኞች ላይ ተመጣጣኝ ያልሆነ ኃይል ከመጠቀም ሊቆጠቡ ይገባል!" - ኢሰመኮ

በወላይታ በዞን አንዳንድ አከባቢዎች ነሐሴ 4 ቀን 2012 ዓ.ም. በተደረጉት ተቃውሞዎች የፀጥታ ኃይሎች በተቃውሞ ሰልፈኞች ላይ የወሰዱት እርምጃ ተመጣጣኝነት አጠያያቂ መሆኑን የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ገለጸ፡፡

ኮሚሽኑ ለሰልፍ ወጥተው ሞቱ ባላቸው 6 ሰዎችን አስመልክቶ ፈጣን ምርመራ የሚያስፈልግ መሆኑን በመግለጫው ጠቅሷል፡፡

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ቃል አቀባይ፣ አቶ አሮን ማሾ እንደገለጹት “የፀጥታ ኃይሎች ሰላማዊ ሰልፎችን በሚቆጣጠሩበት ወቅት የሞት አደጋን የሚያስከትል የኃይል እርምጃ ከመውሰድ ሊቆጠቡ ይገባል፤ እንደነዚህ ያሉ እርምጃዎች ቀድሞውኑን የነበረ ውጥረትን ያባብሱ እንደሆን እንጂ መፍትሔ አይሆኑም” ብለዋል፡፡

በሰኞው እስር ወቅት በጠቅላላው 178 ሰዎች የተያዙ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 28ቱ የዞኑ ከፍተኛ ባለስልጣናት መሆናቸው እና በወላይታ ሶዶ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሌጅ ውስጥ በቁጥጥር ስር የሚገኙ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ኢሰመኮ የታሳሪዎችን መብቶች ማክበርና በአፋጣኝ ወደ ፍርድ ቤት መቅረብ ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብሏል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኢትዮጵያ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች ከ24 ሺህ አለፉ!

ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 11,881 የላብራቶሪ ምርመራ 584 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ የ20 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በትላንትናው ዕለት 285 ሰዎች አገግመዋል።

በአጠቃላይ በሀገራችን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 24,175 የደረሱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 440 ደርሷል ፤ እንዲሁም አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች 10,696 ደርሰዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የአቶ ጃዋር የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደረገ!

የኦሮሞ ፌደራሊስ ኮንግረስ (ኦፌኮ) አባል የሆኑት አቶ ጃዋር መሐመድ ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ ፍርድ ቤቱ ውድቅ አደረገ።

በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት የአራዳ ተረኛ ወንጀል ችሎት ላይ ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል።

መርማሪ ፖሊስ ሲያካሂድ የነበረውን ምርመራ ማጠናቀቁን በመግለጽ፤ ዐቃቤ ሕግ በተጠርጣሪው ላይ የቀዳሚ ምርመራ መዝገብ እንደከፈተባቸው አስታውቋል። በመሆኑም የምርመራ መዝገቡ እንዲዘጋ ጠይቋል።

የአቶ ጃዋር ጠበቃ በበኩላቸው በደንበኛቸው ላይ ፖሊስ ባካሄደው የምርመራ ስራ ያገኘው ውጤት ዋስትና የማያስከለክል በመሆኑ የዋስ መብታቸው እንዲጠበቅ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል።

ጉዳዩን የመረመረው ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪው ወደ ፊት ክስ የሚመሰረትባቸው ከሆነ የተጠረጠሩበት መዝገብ የሰው ህይወት የጠፋበትና ከ15 ዓመታት በላይ ሊያስቀጣ የሚችል በመሆኑ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጎታል።

ተጠርጣሪው (አቶ ጃዋር መሃመድ) ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት መብታቸውን መጠየቅ እንደሚችሉ ትዕዛዝ በመስጠት መዝገቡን ተዘግቷል - ENA

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ችሎት!

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በእነ እስክንድር ነጋ ላይ የቀዳሚ ምርመራ ምስክሮችን ለመስማት ለነገ ቀጠረ።

#MORE : telegra.ph/EskinderNega-08-11

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የአማራ ብልፅግና ፓርቲ!

የአማራ ብልጽግና ሥራ አስፈጻሚ አባላት በክልሉና በሀገሪቱ ጉዳዮች በባህር ዳር ስብሰባ ላይ መሆናቸው ይታወቃል።

በማህበራዊ ሚዲያ ላይ 'ከውስጥ ያገኘነው መረጃ' በማለት እየወጡ ያሉ መረጃዎች #ሀሰተኛ መሆናቸውን የአማራ ክልል ኮሚውኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የትግራይ ምርጫ ቅስቀሳ ነገ ይጀምራል!

የትግራይ ክልል ምርጫ ቅስቀሳ ዛሬ ነሐሴ 5/2012 ዓ/ም መጀመር የነበረበት ቢሆንም የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ለፕሮዳክሽን ዝግጅት በአንድ ቀን እንዲገፋላቸው በጠየቁት መሰረት ከነገ ነሃሴ 6/2012 ዓ/ም ጀምሮ ቅስቀሳ ይጀምራሉ።

የድምፂ ወያነ ቲቪ፣ ትግራይ ቲቪ ፣ የትግራይ ሚዲያ ሃውስ ፣ ኤፍ ኤም መቐለ 104.4 ፣ ሞሞና ሬድዮ ጣቢያ፣ ድምፂ ወያነ ሬድዮ ፣ ብሄራዊ ኤፍ ኤም ሬድዮ እና መቓልሕ ጋዜጣ ቅስቀሳ የሚደረግባቸው ሚዲያዎች ናቸው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጫልቱ ታከለ ከእስር ተፈታች!

በዋስ እንድትፈታ ፍርድ ቤት ወስኖላት ከእስር ሳትፈታ የቆየችው ጫልቱ ታከለ በዛሬው ዕለት ከእስር ተፈታ ከቤተሰቦቿ ጋር መቀላቀሏ ተሰምቷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኮሮና የተያዙ የጤና ባለሞያዎችና ድጋፍ ሰጪዎች!

- በትግራይ ክልል እስካሁን ከ30 በላይ የጤና ባለሞያዎችና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች በቫይረሱ ተይዘዋል ፤ አላማጣ ብቻ በላብራቶሪ ቴክኒሻንነት የሚሰሩ 7 ባለሞያዎች በቫይረሱ ተይዘዋል፤ በአይደር ሆስፒታል 3 ከፍተኛ የጤና ባለሞያዎችን ጨምሮ ብዙ ሃኪሞች በቫይረሱ ተይዘዋል።

- በአማራ ክልል እስካሁን 23 የሚደርሱ የጤና ባለሞያዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

- በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እስካሁን 21 የሚደርሱ የጤና ባለሞያዎች እና የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

- በሲዳማ ክልል እስካሁን 13 የጤና ባለሞያዎች እንዲሁም ሁለት (2) የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

- በኦሮሚያ ክልል እስካሁን 34 የጤና ባለሞያዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ ከነዚህ መካከል አብዛኛዎቹ መደበኛ አገልግሎት የሚሰጡ ሆስፒታሎችና ጤና ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ ናቸው። #BBC

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ችሎት!

እነ አቶ ጃዋር መሀመድ ዳኛ ይቀየርልን ሲሉ ያቀረቡት ጥያቄ ውድቅ ተደረገ፡፡ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እነ አቶ ጃዋር ባቀረቡት አቤቱታ ላይ መርምሮ ብይን ሰጥቷል፡፡

በዚህም አቤቱታው በማስረጃ የተደገፈ አይደለም በሚል ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርጎታል፡፡ ይህን ተከትሎም ችሎቱ ከዚህ በፊት በነበረው ዳኛ የሚታይ ይሆናል ተብሏል፡፡

በእነ አቶ ጃዋር መሃመድ መዝገብ አስራ አራት (14) ሰዎች በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት የቀረቡ ቢሆንም ዳዊት አብደታ የተባለው ተጠርጣሪ በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ተጠርጥሮ ችሎት አልቀረበም፡፡

Via Tarik Adugna (FBC)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

ደሴ ማረሚያ ቤት በተደረገ የኮቪድ-19 ምርመራ 10 ህግ ታራሚዎች ቫይረሱ መያዛቸው መረጋገጡን የከተማው ጤና መምሪያ ኃላፊ ለቪኦኤ አስታውቀዋል። በቫይረሱ የተያዙት ሰዎች ወደ ቦሩ ሜዳ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለህክምና ተልከዋል ተብሏል።

በሌላ በኩል ከቀናት በፊት በምሥራቅ ባሌ ዞን ጊንር ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የነበሩ ቁጥራቸው ወደ ሃምሣ (50) የሚጠጋ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

የምሥራቅ ባሌ ዞን አስተዳደር መረጃውን ለቪኦኤ ያረጋገጠ ሲሆን ከተጋላጮቹ ጋር ቅርበትና ንክኪ የነበራቸውን ሰዎች እየተከታተለ መሆኑን እና ሌሎች እስረኞችም ለኮቪድ-19 እንዳይጋለጡ/በቫይረሱ እንዳይያዙ ለመከላከል የተለያየ ስራ እየሠራ መሆኑን ገልጿል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ምክንያትአልሆንም የኮሮና ስርጭትን እገታለሁ!

ኤ.ቲ.ኤም (ATM) ከመጠቀሜ በፊት እና በኃላ እጄን በውሃ እና በሳሙና ወይም በሳኒታይዘር አፀዳለሁ #EPHI #MoH

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

በወላይታ ሶዶ፣ ቦዲቲ፣ አረካ ለ4ኛ ቀን የንግድ እና ትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንደቆመ ነው። በወላይታ ዞን ካለፉት ቀናት የተሻለ መረጋጋት ይታያል። አሁንም የፀጥታ ኃይሎች በየአካባቢው በስፋት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ። የወላይታ የቲክቫህ አባላት እንዳሳወቁት ዛሬም የዳታ ኢንተርኔት አገልግሎት አልተከፈተም።

PHOTO : TEMESGEN
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኢሶዴፓ መግለጫ!

በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ክልል የመሆን ጥያቄ በማንሳት የሚንቀሳቀሰው የዞኑ አመራር እና ሕዝብ በሕገ መንግስቱ ድንጋጌ መሠረት ተገቢ መልስ በሰላማዊ አግባብ ሊሰጠው ይገባል ሲል የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ /ኢሶዴፓ/ ጠየቀ።

ኢሶዴፓ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ በዞኑ ለተነሳው ሕገ-መንግሥታዊ ጥያቄ ተገቢ ምላሽ በመስጠት፣ ጥያቄውን በማንገብ ምላሽ ለመሻት የተንቀሳቀሱትን የወላይታ ዞን አመራር አካላትን እና በጉዳዩ ሳቢያ የታሰሩትን ሁሉ በመፍታት፣ ለተከሰተው ችግር ሰላማዊ መፍትሄ በአስቸኳይ እንዲፈልግ አሳስቧል።

አስተዋዩና ሰፊው የወላይታ ሕዝብ ጉዳዩን በወትሮ ጥበቡ በትዕግስት በመያዝ ፣ የሰላማዊ መፍትሄ አካል እንዲሆን ኢሶዴፓ ጥሪ አድርጓል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia