የኢሶዴፓ መግለጫ!

በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ክልል የመሆን ጥያቄ በማንሳት የሚንቀሳቀሰው የዞኑ አመራር እና ሕዝብ በሕገ መንግስቱ ድንጋጌ መሠረት ተገቢ መልስ በሰላማዊ አግባብ ሊሰጠው ይገባል ሲል የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ /ኢሶዴፓ/ ጠየቀ።

ኢሶዴፓ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ በዞኑ ለተነሳው ሕገ-መንግሥታዊ ጥያቄ ተገቢ ምላሽ በመስጠት፣ ጥያቄውን በማንገብ ምላሽ ለመሻት የተንቀሳቀሱትን የወላይታ ዞን አመራር አካላትን እና በጉዳዩ ሳቢያ የታሰሩትን ሁሉ በመፍታት፣ ለተከሰተው ችግር ሰላማዊ መፍትሄ በአስቸኳይ እንዲፈልግ አሳስቧል።

አስተዋዩና ሰፊው የወላይታ ሕዝብ ጉዳዩን በወትሮ ጥበቡ በትዕግስት በመያዝ ፣ የሰላማዊ መፍትሄ አካል እንዲሆን ኢሶዴፓ ጥሪ አድርጓል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia