TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
OPA🔝

#የኦሮሚያ_ሀኪሞች_ማህበር በዛሬው ዕለት የኦሮሚያ ጤና ቢሮ፣ የአትዮጵያ ሐኪሞች ማህበር ተወካይ እና አክቲቪስት #ጀዋር_መሃመድ በተገኘበት በኢሊሊ ሆቴል የመጀመሪያ ጉባኤ እና የምስረታ ክብረበዓል ተከናውኗል።

Oromiyaa Physcians Association(OPA) inaugration ceremony held @ Elili International Hotel!

©ዶክተር ሲሳይ ከOPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
107 ፓርቲዎች

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ እባካችሁ ተዋሃዱ ብሎ ሲማፀናቸው የነበሩት ወደ ሰማንያ (80) አካባቢ የሚገመቱ ፓርቲዎች በጥቂት ወራት ውስጥ 107 ደርሰዋል።
--
ከ 107ቱ ውስጥ ሰላሳ ሶስቱ (33) "#ኢትዮጵያ "ን በፓርቲያቸው ስያሜ ውስጥ ተጠቅመዋል። #አማራ የሚል ስያሜአቸው ውስጥ ያላቸው
#አምስት ሲሆኑ #አስራ_ሶስቱ ደግሞ #የኦሮሚያ ፓርቲዎች ናቸው። እነ አንዳርጋቸው ፅጌ ብዙ ጊዜ ክፍፍል ያለው "በዘውግ" የተደራጁ ፓርቲዎች ላይ ነው ቢሉም በኢትዮጵያዊነት ስም የተደራጁት 33 ፓርቲዎች ራሱ ተቀራርበው መዋሃድ አልቻሉም። #ሰማያዊ_ፓርቲ ለምሳሌ #ከአግ7ጋር ተዋህዶ ፈርሷል ቢባልም ዝርዝሩ ውስጥ ተካቷል።
--
ኢህአዴግ እንደ ግንባርም በተናጠልም የፈረመበት ምክንያት ግራ ያጋባል። በዛ ላይ የተፈረመበት ሰነድ ላይ አዴፓ እና ኦዴፓ ሳይሆን #ብአዴን እና #ኦህዴድ ነው የሚለው። አንድ ወጥ ሀገር አቀፍ ፓርቲ ሆነው በድጋሚ ለመመዝገብ ነው ለስያሜው እንኳን ቸልተኛ የሆኑት?
--
ለማንኛውም ሰማንያ አካባቢ ፓርቲ የተሳተፈበት የ 1997 (2005) ምርጫ ላይ የክልል ምክር ቤት መቀመጫ ያሸነፉት ፓርቲዎች ከላይ ያሉት ነበሩ። በርካቶቹ አንድም መቀመጫ እንዳላገኙ የሚታወቅ ነው።

Via THE FINFINNE INTERCEPT
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጅግጅጋ ዝግጅቷን አጠናቃ እንግዶችን እየተቀበለች ነው። #የኦሮሚያ እና #የሶማሌ ክልል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት መድረክ #ነገ ይካሄዳል።

ፎቶ፦ Mame/TIKVAH-ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ለሊት በዚያው በተኙበት ነው የገደሏቸው..."

በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ቦርደዴ ወረዳ ጉምቢ በተባለ ቦታ በተፈጸመ ጥቃት በትንሹ ሰባት ሰዎች መገደላቸውን #የቦርደዴ ጤና ጣቢያ ባልደረባ ለጀርመን ራድዮ ተናግረዋል። የኦሮሚያ ኮምዩንኬሽን ቢሮ ጥቃቱ መፈጸሙን በፌስቡክ ገጹ ባወጣው አጭር መረጃ አረጋግጧል።

#የአፋር እና #የኦሮሚያ ክልሎች በሚዋሰኑበት አካባቢ በምትገኘው ጉምቢ በተፈጸመው ጥቃት ከሞቱ ሰዎች መካከል አንዲት እንስት እንደሚገኙበት እና ሌሎች ሁለት ሰዎች መቁሰላቸውን የቦርደዴ ጤና ጣቢያ ባልደረባ የሆኑስት ሲስተር ሐይማኖት ተስፋዬ አስረድተዋል። ሲስተር ሐይማኖት «ለሊት በዚያው በተኙበት ነው የገደሏቸው። ሰባት ሰው ሞቷል። አሁን ሰባት እሬሳ አለ። እየተፈለጉም ያሉ አሉ» ብለዋል።

የኦሮሚያ ክልል የኮምዩንኬሽን ቢሮ ከአንድ ሰዓት ገደማ በፊት በፌስቡክ ገጹ ባወጣው መረጃ በቦርደዴ ወረዳ በተፈጸመው ጥቃት ሰባት ሰዎች መገደላቸውን ገልጿል።

ሲስተር ሐይማኖት ከሞቱት ሰባት ሰዎች ባሻገር ሌሎች ሁለት ሴቶች መቁሰላቸውን ተናግረዋል። «ሁለት የቆሰሉ ሴቶች ነበሩ። ወደ አሰቦት ሆስፒታል ልከናቸዋል» ብለዋል።

ሲስተር ሐይማኖት እንዳሉት ጥቃቱ ከተፈጸመ በኋላ የገቡበት ያልታወቀ ሰዎች በመኖራቸው #ፍለጋ እየተካሔደ ይገኛል። ጥቃቱ ከተፈጸመ በኋላ ከአዲስ አበባ ወደ ሐረር እና ድሬዳዋ የሚወስደው መንገድ ለረዥም ሰዓታት ተዘግቷል።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia