TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሲዳማ ባህል አዳራሽ🔝በሲዳማና ወላይታ ሕዝብ መካከል ተፈጥሮ የነበረውን ችግር ይፈታል ተብሎ የታመነበት የዕርቅና #ሰላም_ኮንፈረንስ በሀዋሳ ሲዳማ ባህል አዳራሽ በመካሄድ ላይ ነው።በዕርቁ ሥነ ሥርዓት ላይ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣የባህል ሽማግሌዎችና አባ ገዳዎች የተገኙ ሲሆን ፕሮግራሙም በተያዘለት መርሃ ግብር መሠረት ቀጥሎ ይገኛል።

ምንጭ፦ የሲዳማ ዞን ባህል፣ቱሪዝም የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update ለ18ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ የተካሄደው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ያለምንም ችግር በሰላም ነው የተጠናቀቀው።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ቤት ለእንግዳ'ን በተግባር🔝ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ 11ኛው የአፍሪካ ህብረት አስቸኳይ የመሪዎች ጉባዔ መጠናቀቅን ተከትሎ የሰጡት መግለጫ።

ምንጭ ፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዛሬ አስተያየት፣ ጥያቄዎች እና ሀሳቦችን በሰፊው የምንቀበልበት ቀን ነው። ማድረስ ትችላላችሁ @tsegabwolde ከታላቅ አክብሮት ጋር!!
TIKVAH-ETHIOPIA(ተስፋ ኢትዮጵያ)!

በሺዎች የሚቆጠሩ አስተያየቶችን አንብቢያለሁ አብዛኛው ገንቢ እና አበረታች ነው። የሚያኮራና እኔ እንዲህ ነኝ የሚያስብል ሳይሆን ተጨማሪ ሰዓት ጨምሬ አንገቴን አቀርቅሬ እንድውል የሚያደርገኝ ነው። ትልቅ ሀላፊነት ነው ያሸከማችሁኝ። በነገራችን ላይ በስድብ ያጠረገረጉኝም እንደውም ከአንዱ #ብሄር አስገብተውኝ ለመሳደብ፤ ሞራሌን ለመንካት የጣሩም አሉ ግን ይህ የሚጠበቅ ነገር በመሆኑ እየሳቅኩ እና ለሰደቡኝ ሰዎችም ፈጣሪ ማስተዋልን እንዲሰጣቸው እየለመንኩ ነው ያነበብኩት። በአጠቃላይ ሁላችሁንም ከልቤ ተንበርክኬ አመሰግናለሁ። እውነት ተስፋ ሆናችሁኛል። ምኖርለት ነገር እንዳለኝ አሳይታችሁኛል።

*ፀጋአብ ወልዴ* ሰው ነኝ ሲቀጥል ኢትዮጵያዊ #ብቻ ነኝ!! እኔ እራሴን ማስበው ፈጣሪ ለሰው ልጅ ሁሉ የፈጠረኝ አድርጌ ነው። የሰዎችን ብሄር፣ እምነት እና ባህል እጅግ በጣም አከብራለሁ። እኔ ግን ከሁሉም ነኝ! እኔ ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ፣ ሱማሌ፣ ሲዳማ፣ ወላይታ....ነኝ! የአንዱ ብቻ ሆኜ መኖር አልፈልግም። እንዲህ መኖር አትችልም ሰው ሆነህ መኖር አትችልም የሚለኝ አካል ከሀገሬ ያስወጣኝ።

እኔ እንደሰው የሁሉም ስቃይ እንዲሰማኝ፣ የሁሉም መከራ እንዲያሳዝነኝ፤ የሌላው ችግር የኔም ችግር እንደሆነ እንዲሰ ማኝ እፈልጋለሁ። ወዳጆቼ ከየትም ብሄር ይሁኑ እደሰው ስለማከብራቸው ቋንቋቸውን፤ ባህላቸውን እምነታቸውን አከብርላቸዋለሁ። እኔ ግን የሁሉም ሰው ልጅ ነኝ! ብሄሬ የሚያስጨንቀው ሰው ካለ ይህ ነው መልሴ እኔ ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ፣ ሲዳማ፣ ወላይታ፣ ከንባታ፣ ሱማሌ፣ ጉራጌ፣ ስልጤ...ሁሉም ነኝ!

ሰው ሆኜ ስለተፈጠርኩ የሰው ሁሉ ስጦታ ነኝ!! ይህን ለማለት ያስገደደኝ ብሄር ተኮር ስድብ ስላስተናገድኩ ነው።

ወደ ቻናላችን ስመለስ....

1. ቻናሉን የትኛውም ድርጅት እና ግለሰብ ስለማያግዘው አሁንም ወደፊትም በማስታወቂያዎች ብቻ ነው የሚዘልቀው። ቻናሉ ብቻ ሳይሆን ምርታቸውን የሚያስተዋውቁ አካላትም የስራ እድላቸው ይሰፋል።

🔹ብዙዎች የማስታወቂያ መብዛት ቅር እንዳሰኛችሁ ግልፃችኃል ማስታወቂያዎች ይቀነሳሉ ለዚህም ዝግጅት ተደርጓል። አሁን እየተሰራበት ያለውም አሰራር ስንቀይረው በቀን የሚቀርበው ማስታወቂ ቁጥር ለመቀነስ ይሞከራል።

2. መረጃ ከበፊቱ እጅግ በጣም በተሻለ ፍጥነት ይቀርባል። ምንጮች የመንግስት ሚዲያዎች፣የግል ሚዲያዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ እንዲሁም የTIKVAH-ETH የአይን እማኞች ይሆናሉ።

3. በየከተማው ያለ የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎች ከበፊቱ በተሻለ ይቀርባል።

4. በቀን የተመጠኑ መረጃዎች ይቀርባሉ። መረጃ ነው እየተባለ እያመጣሁ ከዚህ በኃላ አለጥፍም። ጥራት እና ለህዝብ ጠቃሚነቱን አይቼ አቀርባለሁ።

5. አሁንም ገለልተኛ ሆኖ የሁሉም ድምፅ ይቀርብበታል።

6. በፍፁም የየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት ልሳን ሆኖ አሰራም።

7. ዜናዎችን በፍጥነት ለማቅረብ ይሞከራል ። ፍጥነት ከጥንቃቄ ጋር ስለሆነ ወዲያው የሚሰራጩ መረጃዎች ችግር ፈጣሪም ስለሚሆኑ ጥንቃቄ ይደረጋል።

8. ከተለያዩ ገፆች መረጃዎችን ቀጥታ የማቀርበው በፌ ቡክ ያለውን የስድብ ኮሜንቶች እንድታነቡት ስለማልፈልግ ነው። ብዙ የtikvah ቤተሰብ አባላት ራሳቸውን ከፌስቡክ እያራቁ እንደሆነ ነግረውኛል።

የተጨመሩ፦

TIKVAH-ETH በአፕሊኬሽን ከሚተላለፉት ዜናዎች በተጨማሪ፦

.ምልከታዎች

.የውጭ ዜናዎች

.ጥቆማ

.ውይይት

. #UpdateSport የየዕለቱ ስፖርታዊ የሆኑ ጥቂት መረጃዎች

.የመዝናኛ ወሬዎች ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ

.የቴክኖሎጂ ዜናዎች

.ልዩ ልዩ፦ ድንቃድቅ እውነታዎች

.🔹ላስተዋውቃችሁ🔹ይህ የምትኖሩበትን አካባቢ የምትገልፁበት መንገድ ነው። ከተማችሁን ታስተዋውቋታላችሁ። 15 መስመር በመሆን ፅሁፍና በፎቶ!

.የሙዚቃ ምርጫ(ሀገራዊ እና እጅግ በጣም አስተማሪ የሆኑ ሙዚቃዎች እጠቁማችኃለሁ)

.ቲፕ

ከላይ የተጨመሩት ቻናሉን የበለጠ ማራኪ ለማድረግ ታሶቦ ነው። ትልቁ ስራ ከመላው ኢትዮጵያ ምን እየሆነ እንዳለ እና በየቦታው ያሉትን መረጃዎች መዳሰስ ነው።

ሌላው አዲሱ ነገር ከዚህ ቀደም በአማርኛ ከእናተ የሚላኩ መረጃዎች የሚቀርቡ ሲሆን በእንግሊዘኛ ፅሁፍ የሚቀርቡትን ግን የመቅረብ እድላቸው አነስተኛ ነው በመሆኑም #በድምፅ መረጃዎችን ላኩ!! በድምፅ መረጃ ማስተላለፍ መጀመራችንን ስናበስ በደስታ ነው😁

🔹ማስታውቂያ የምታስነግሩ፦

1.ህጋዊ ብቻ
2.ተጠያቂ
3.እናተም ብቻ ሳይሆን ተገልጋዩን የሚጠቅም
4.አገልግሎት ሰጪዎች
5.በስራ ላይ የማይንቀሳቀሱ እና እንደው ለጊዜው ብቻ የተከፈቱ ቻናሎች አይተዋወቁም

🔹የተሻሻለውም የማስታወቂያ ህግ እና የአሰራር ሁኔታ ድርጅቶች ማየት ትችላላችሁ።

(ኮንትራት ያልጨረሳሁትን አይመለከተም። እናተ ያላችሁ ኮንትራት ሲያልቅ አዲሱን አሰራር ማየት ትችላላችሁ)

ይህ ለማድረግ የተገደድነው ገዘንብ ለማግበስበስ እና ትርፋማ ለመሆን አይደለም ማስታወቂያዎችን ለመቀነስ ብቻ ነው!!

ቻናሉ ገንዘብ ለመሰብሰብ እና ለማግበስበስ የተቋቋመ አይደለም! ሰዎችን እናግዝ ሰርተን አብረን እንስራ!!

ሌሎቹም በተመለከተ፦

.TIKVAH-EDU ለአሁን 2 ቋንቋዎች ላይ ይሰራል። ከቋንቋ በተጨማሪ ሌሎች ትምህርት ነክ ጉዳዮች ያስተናግዳል።

.TIKVAH-AID ሁሉም የሚሳተፍበት እና እገዛ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች በግላቸው አካውንት የምናግዝበት ነው። እንዲሁም አነቃቂ የእንተጋገዝ መልዕክቶች የሚቀርቡበት ነው።

.TIKVAH-AID 2 ይህ በኛው አካውንት እያሰባሰብን ለሰዎች የተለያዩ ድጋፎች የምናደርግበት እና የተስማሙ ብቻ የገቡበት ነው።

.TIKVAH-UNIVERSITY በዩኒቨርሲቲዎች ዙሪያ ሰፊ ስራ ለመስራት የሚቻልበት በየግቢው ያሉ እንቅስቃሴዎች የሚቀርቡበት ነው። የተለያዩ ማዕበራት በዚህ ላይ ተሳታፊ ሁኑ! አድሚም ሆናችሁ የግቢያችሁን ሁኔታ እና እንቅስቃሴ ለሌሎች አጋሩ!

አመሰግናለሁ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከድሬደዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን የተሰጠ መግለጫ፦

ከትላንት ህዳር 8ቀን 2011አ.ም ከሰአት በሃላ እና ህዳር 9ቀን እረፋድ ላይ በቀበሌ 09 ፖሊስ መሬትና #መጋላ_ጨብጡ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ፖሊስ አሁን ላይ መነሻ ምክንያቱን እያጣራው ያለው ግጭትና ሁከት የተፈጠረ ሲሆን በዚህም ግጭት በህክምና ጭምር የተረጋገጠ በስለት ጉዳት ጉዳት ደርሶበት የ1ሰው ህይወት ሲያልፍ በ2 ቤቶች ላይ ቀጠሎ እንዲሁም በሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል።

ፖሊስ ከፌደራል ፖሊስና ከመከላኪያ ጋር በመሆን ግጭቱ ወደ 01 ቀበሌ መልካ ጀብዱ የመስፋፋት አዝማሚያ መታየቱን ተከትሎ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስ ለመቆጣጠርም ችሏል።

በአሁን ወቅት ችግሩ በተፈጠረባቸው አካባቢዎች ተገቢው ፀጥታን #የማረጋገጥና ሰላምን የማስፈን ስራ እየተሰራ ሲሆን ተፈጥሮ የነበረውን
ግጭትና ሁከትም አሁን ላይ ለማስቆምና #ለመቆጣጠር ተችሏል።

በመሆኑም መላው ህብረተሰብ ወደ ግጭት ሁከትና መረበሽ ሰዎችን እንዲያመሩ ከሚያደርጉ አንዳንድ ማህበራዊ የሚዲያ ገፆችና
ያልተረጋገጠ መረጃ ከሚሰጡ ዘገባዎች እራሱን በመጠበቅ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ የአካባቢውን ሰላምና ፀጥታ ከፀጥታ ሀይሉ ጋር በመሆን የማረጋገጥ ተግባር አጠናክሮ እንዲቀጥል ፖሊስ ጨምሮ ጥሪውን ያቀርባል።

ህዳር 9/2011 አ.ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በመስቃንና ማረቆ አካባቢዎች በተደጋጋሚ እየተፈጠሩ ላሉ #ግጭቶች መንግስት ዘላቂ #መፍትሄ እንዲያፈላልግ የግጭቱ ተጎጂዎች ጠይቀዋል። ከሰሞኑ በዚህ አካባቢ በተፈጠረዉ ግጭት የዜጐች ህይወት ሲያልፍ በርካቶች ከቀዬአቸዉ ተፈናቅለዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update ታንዛኒያ በእስር ላይ የሚገኙ #ኢትዮጵያዊያን በምህረት እንዲለቀቁ ተጠየቀ ወደደቡብ አፍሪካ ሲያመሩ በታንዛኒያ የተያዙ 224 ኢትዮጵያዊያን በአስር ላይ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ የዜጎቿን ደንነት መጠበቅ ቀዳሚ አጀንዳዋ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ አስታውቀዋል። ዶክተር ወርቅነህ ገበየህ ከአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ጎን ለጎን ከታንዛኒያ አቻቸው ዶክተር አውጉስቲን ማሂጋ ጋር በሁለቱ አገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ላይ ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው ይህንን ያስታወቁት።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በሲዳማና በወላይታ ሕዝቦች መካከል ያለውን #ትስስር ለማጠናከር የሚያግዝ የዕርቅና የሠላም ኮንፈረንስ ትላንት በሀዋሳ ሲዳማ ባህል አዳራሽ ተካሂዷል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትኩረት‼️

መንግስት የሚዛን ቴፒን ጉዳይ ለምን ለሌላው ህዝብ አይገልፅም?? ምንስ እየተሰራ ነው?? ተማሪዎች እስከዛሬ በአግባቡ ትምህርታቸውን መከታተል አልቻሉም። ችግሩን በዘላቂነት መፍታት ይገባል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
ሜጀር ጀነራል ተክለብርሃን‼️

የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ቀድሞ #ኢንሳ በሚል ምህጻረ ቃል የሚጠራው የመረጃ ቴክኖሎጂ መስሪያ ቤት የቀድሞ ኃላፊ ሜጀር ጀነራል ተክለብርሃን ወልደ አረጋይን በቁጥጥር ስር ያላዋለው በምርመራ መዝገቡ ውስጥ ስለሌሉ እንደሆነ አስታውቋል።

ምንጭ፦ VOA
@tsegabwolde