ከድሬደዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን የተሰጠ መግለጫ፦

ከትላንት ህዳር 8ቀን 2011አ.ም ከሰአት በሃላ እና ህዳር 9ቀን እረፋድ ላይ በቀበሌ 09 ፖሊስ መሬትና #መጋላ_ጨብጡ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ፖሊስ አሁን ላይ መነሻ ምክንያቱን እያጣራው ያለው ግጭትና ሁከት የተፈጠረ ሲሆን በዚህም ግጭት በህክምና ጭምር የተረጋገጠ በስለት ጉዳት ጉዳት ደርሶበት የ1ሰው ህይወት ሲያልፍ በ2 ቤቶች ላይ ቀጠሎ እንዲሁም በሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል።

ፖሊስ ከፌደራል ፖሊስና ከመከላኪያ ጋር በመሆን ግጭቱ ወደ 01 ቀበሌ መልካ ጀብዱ የመስፋፋት አዝማሚያ መታየቱን ተከትሎ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስ ለመቆጣጠርም ችሏል።

በአሁን ወቅት ችግሩ በተፈጠረባቸው አካባቢዎች ተገቢው ፀጥታን #የማረጋገጥና ሰላምን የማስፈን ስራ እየተሰራ ሲሆን ተፈጥሮ የነበረውን
ግጭትና ሁከትም አሁን ላይ ለማስቆምና #ለመቆጣጠር ተችሏል።

በመሆኑም መላው ህብረተሰብ ወደ ግጭት ሁከትና መረበሽ ሰዎችን እንዲያመሩ ከሚያደርጉ አንዳንድ ማህበራዊ የሚዲያ ገፆችና
ያልተረጋገጠ መረጃ ከሚሰጡ ዘገባዎች እራሱን በመጠበቅ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ የአካባቢውን ሰላምና ፀጥታ ከፀጥታ ሀይሉ ጋር በመሆን የማረጋገጥ ተግባር አጠናክሮ እንዲቀጥል ፖሊስ ጨምሮ ጥሪውን ያቀርባል።

ህዳር 9/2011 አ.ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia