TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ኢሬቻ2011

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ #ለኢሬቻ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኦሮሞ ህዝቦች እንኳን በፍቅርና #በአንድነት ለሚከበር የኢሬቻ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን ብለዋል፡፡

ኢሬቻ የገዳ ስርዓት አካልና የምስጋና የሰላም ቀን ነው፣ የኦሮሞ ምኞት ፍቅር፣ ብልጽግና፣ ባህሉ ደግሞ አብሮነት ነው፤ ኦሮሞ ለምለም ይዞ ለፈጣሪ #ምስጋና ያቀርባል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡

የኦሮሞ ህዝብ የሚተዳደርበት #የገዳ ስርዓት ለዘመናዊ ዴሞክራሲ መሰረት የሆነና ታናሽ ታላቅን አክብሮ ከተላቅ የሚመር፣ ታላቅ ደግሞ ታናሽን በማብቃት ስርዓትን የሚያስቀጥል ስርዓት መሆንም ዶ/ር ዐቢይ ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዘንድሮን የኢሬቻ በትግል የተገኘውን ለውጥ የሚናስቀጥልበት፣ በፍቅር፣ በአንድነትና በእኩልነት አገር የሚንመራበትና የገዳ ልምዶችን የሚንቀስምበት ጊዜ በመሆኑ ደስታችንን ድርብ ያደርገዋል ብለዋል፡፡

ዶ/ር ዐቢይ የዘንድሮ ኢሬቻ ባህላችንንና አንድነታችንን የምናጠናክርበት፣ የአባገዳዎች መልዕክት #የምንሰማበትና የምንተገብርበት ይሆናል የሚል ተስፋም አለን ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዘንድሮ የኢሬቻ በዓል በፖለቲካ አለላካከት #ልዩነቶቻቸን ሳይገድቡን በፍቅርና በአንድነት አብሮ ለመስራት የሚንመራረቅበት እንደሚሆን ተስፋ እንዳላቸውም ገልጸዋል፡፡

አሸናፊ ሀሳብ በመያዝ አንድነታችንን አጠንክረን፣ ለሰላም፣ የሕግ የበላይነትን ለማስከበር፣ ለፌዴራሊዝምና ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ አብረን መስራት አለብን ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡

ሰላማችንን ማስጠበቅ በእጃችን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ሰላማችንንና ባህላቸን በመጠበቅና በማስጠበቅ አገርን መገንባት አለብን፤ በኢሬቻ በዓል ላይ ሰላማችንን በማስጠበቅ ለዓለም ምሳሌ መሆን አለብንም ብለዋል፡፡

ዘመኑ በፍቅርን አቅፈን ጥላቻን የምናሸንፍበት ዘመን እንዲሆንልን እመኛለሁ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፡፡

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኢሬቻ2011⬆️

የጋሞ ወጣቶችን የጋሞ የሀገር ሽማግሌዎች የኢሬቻ በአልን ከኦሮሞ #ወንድሞቻቸው ጋር ለማክበር ጉዞ ጀምረዋል። ይንን ጉዞ የኦሮሚያ መንግስት ባቀረበው ግብዣ መሰረት የጋሞ ጎፋ ዞን ጥያቄውን ተቀብሎ ነው ጉዞ የተደረገው።

©ፋሪስ ንጉሴ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኢሬቻ2011⬆️

የሲዳማ ወጣቶች(ኤጄቶዎች) የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል ከኦሮሞ #ወንድሞቻቸው ጋር ለማክበር ወደ ቢሾፍቱ ተጉዘዋል።

©አብዲ ከባቱ(ዝዋይ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኢሬቻ2011 እንኳን ለ2011 የኢሬቻ በአል በሰላም በፍቅርና በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን!
Baga Ayyaana Irreechaa 2011'n isiin ga'e baga geessan.

#ኢትዮጵያዊነት ይለምልም!
#ኢሬቻ የኔም ነው!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኢሬቻ2011⬆️ሚሊዮኖች ተሳታፊ በሆኑበት በዘንድሮው ታላቁ የኢሬቻ በዓል ላይ የተለያዩ የአገሪቱ #ብሄር_ብሄረሰቦች ተሳታፊ ነበሩ፡፡

©የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኢሬቻ2011 በሰላም ተጠናቋል!

Ofkollee Jirra!
Ayyaanni Irreechaa guddichi bara 2011 bakka Oromootni fi ummatni obbolaa miliyoonotaan lakkaawaman argamanitti haala miidhagaa ta'een nagaan kabajamee xumuramee jira!
Baga Gammadne!

የዘንድሮው ታላቁ #የኢሬቻ በዓል በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተሳታፊዎች የኦሮሞ ህዝብ ወዳጆች እና ወንድም ሕዝቦችን በማሳተፍ እጅግ ደማቅ በሆነ ስነ ስርዓት በሰላም ተጠናቋል። እንኳን ደስ አለን!

ምንጭ፦ አቶ አዲሱ አረጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኢሬቻ2011⬆️የመልካ አቴቴ ኢሬቻ በዓል በዛሬው ዕለት ተከብሯል። የኢሬቻ በዓል በቡራዩ መልካ አቴቴ፣ በገላን ጨፌ ቱማና በሰበታ መልካ ሰበታ ነው የተከበረው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia