TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በነገው እለት #በሀዋሳ ከተማ በሚጀመረው11ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ የሚጠበቁ ጉዳዮች፦

▪️በነሐሴ ወር 2007 በመቀሌ ከተማ ተደርጎ በነበረው 10ኛ የኢህአዴግ ጉባኤ የተወሰኑ ውሳኔዎችን መሠረት በማድረግ ባለፉት ሦስት ዓመታት የተሠሩ ሥራዎች ሪፖርት ቀርበው ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በጥልቀት ከገመገመ በኋላ ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚያሳይ እና ለ12ተኛው ድርጅታዊ ጉባኤ የሚሆን ሰነድ እንደሚያዘጋጅ ይጠበቃል፡፡

▪️ሁሉም የግንባሩ አባል ፓርቲዎችና ድርጅቶች በቅርቡ ባካሄዷቸው ጉባኤዎች የመረጧቸውን አዳዲስ የማዕከላዊና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባሎቻቸውን በዚህ ጉባኤ በማሳተፍ አዲስ የኢህአዴግ ምክር ቤት ይመሠርታሉ፡፡

▪️ወቅታዊ የሀገሪቱ ሁኔታ በጥልቀት ይገመገማል፤ ለውጡን ለማስቀጠል አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ፤ የቀጣይ አቅጣጫዎች ይመላከታሉ፡፡

▪️ባለፈው መጋቢት ወር ጥልቅ ተሐድሶውን ተከትሎ የተቀመጡ አቅጣጫዎች እና በተደረገውን የአመራር ለውጥ የተሠሩ ተግባራት ይገመገማሉ፡፡

▪️አዲስ የኢህአዴግ ምክር ቤት መመሥረቱን ተከትሎ የድርጅቱን ሊቀ-መንበርና ምክትል ሊቀ-መንበር #ይመረጣል፡፡

የጉባኤው ተሳታፊዎች ከአራቱም ብሔራዊ ድርጅቶች የተወከሉ ከእያንዳንዳቸው 250 በአጠቃላይ 1000 በቀጥታ በምርጫውና በውሳኔዎች ዙርያ በድምጽ የሚሳተፉ ይሆናሉ፡፡

በልዩ ሁኔታ የ11ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ ተሳታፊዎች በታዛቢነት የሚገኙ ግን ድምጽ (የማይሰጡ ተሳታፊዎች፡-

-ሴቶችና ወጣቶች
-አጋር ድርጅቶች
-የተለያዮ የኅብረተሰብ ክፍሎች
-ማኅበራት
-ፌዴሬሽኖች
-ዩኒቨርሲቲዎች
-የፌዴራል ተቋማት ኃላፊዎች
-ልማታዊ ባለሀብቶች

የ11ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ መክፈቻ ላይ የሚሳተፉ፦

• የሠራዊት አመራሮች
• አርቲስቶች
• ስፖርተኞች
• ታዋቂ ግለሰቦች
• ተፎካከሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጥቅሉ አንድ ሺህ 900 ተሳታፊዎች ይኖራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia