TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Kenya

የኬንያው ፕሬዝዳንት ተቃውሞ በተደራጀባቸው ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ቀርበው ከወጣቶች ጋር ተወያዩ።

ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ያዘጋጁትን የፋይናንስ ሕግ ውድቅ እንዲያደርጉ ያስገደዳቸው የወጣቶች ተቃውሞ የተደራጀበት ማኅበራዊ ሚዲያ መድረክ ላይ ለውይይት መቅረባቸው ታሪካዊ ነው ተብሏል።

ሩቶ ትላንትና ከሰዓት በ ' X ' ስፔስ ላይ ቀርበው ከህዝብ ለሚነሳው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።

' X ' ላይ ከተቃዋሚ ወጣቶቹ ጋር ለጥያቄ እና መልስ መቅረባቸው ፍጹም ያልተጠበቀ እንደነበር ተነግሯል።

ፕሬዝዳንቱ በውይይቱ ቀጥተኛ እና መሸፋፈን ያልታየባቸው ጠንካራ ጥያቄዎች ቀርበውላቸው ነበር።

መጀመሪያ ውይይቱ በጽህፈት ቤታቸው ይፋዊ ገጽ አስተናጋጅነት ሊካሄድ ነበር በኋላ ባገጠመ እክል ከፕሬዝዳንቱ ተቃዋሚዎች አንዱ በሆነ ኦሳማ ኦቴሮ በተባለ ግለሰብ ገጽ ገብተው ነው ምላሽ የሰጡት።

የውይይቱ ተሳታፊዎች ያለ ከልካይ የፈለጉትን ሲጠይቁ፣ ፕሬዝዳንቱ ሲናገሩ መሃል ላይ እየገቡ ሲመላለሱና ማብራሪያ ሲጠይቁ ነበር።

ተቃዋሚዎቹ ምን አሏቸው ?

መንግስታቸው እስካሁን ያስመዘገበውን ነገርና ባህሪያቸውን በተመለከተ አንስተው አብጠልጥለዋቸዋል።

በርካታ ሰላማዊ ተቃዋሚዎች በፖሊስ በጭካኔ መገደላቸውን አመልክተው " በሽብርተኛ አገር ውስጥ ነው እንዴ ያለነው? " በማለት ጠይቀዋቸዋል።

የመረጣችሁ ሰው በመሆኑ ቅድሚያ ለሰው ግድ ሊሰጣችሁ ይገባል ብለዋቸዋል።

ከዩኒቨርስቲ ተመርቆ ሥራ አጥ የሆነ አንድ የውይይቱ ተሳታፊ " በካቢኔዎት ውስጥ ብቃት የሌላቸው በርካታ ባለሥልጣናት አሉ " ብሏቸዋል።

➡️ ሙሰኛ እና የተቀመጡበት ቦታ የማይገባቸው በርካታ ሰዎች በመንግስት ውስጥ እንዳሉ ነግረዋቸዋል።

የተገደሉ ወይም የተጎዱትን ሰዎች ቤተሰቦች ለማነጋገር ሞክረዋል ወይ? ሲሉም ጠይቀዋል።

አንዳንዶች ውሸታም እና ሐዘኔታ የሌላቸው በሚል ከሰዋቸዋል።

ፕሬዝዳንቱ ምን መለሱ ?

● በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ባለሥልጣናትን በሙሉ ለማባረር ቃል ገብተዋል።

● " እውነት ነው ፤ አንዳንድ ባለሥልጣኖቻችን አስጸያፊ ድርጊቶችን እንደሚያሳዩ እስማማለሁ ፤ እራሳቸውን እንዴት እንደሚያስተካክሉ እኔም ጉዳዩን በግሌ አንስቼላቸዋለሁ። ከዚህ የበለጠም አደርጋለሁ " ብለዋል።

● በተቃውሞው የተገደሉ ሰዎችን አሃዝ በማጋነን አንዳንዶችን " ግድየለሽ " ሲሉ ከሰው ቁጥሩ 25 መሆኑን ተናግረዋል።

● በጥይት የተገደለ የ12 ዓመት ህፃን እናት ማነጋገራቸውን ገልጸዋል።

● በተቃዋሚዎች ላይ ሲተኩስ በካሜራ እይታ ውስጥ የገባ የፖሊስ አባል ክስ እንዲመሰረትበት እንዳዘዙ ተናግረዋል።

NB. የኬንያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሟቾች ቁጥር ከ40 በላይ እንደሆነ አሳውቋል።

● ሩቶ አምባገነን እንዳልሆኑ ተናግረዋል። " እኔ ፕሬዝዳንት ነኝ ትክክል !! ግን ፕሬዜዳንቱ ፍጹም ስልጣን የለውም ለዛም ነው ዴሞክራሲያዊ ሀገር የሆነው ቼክ ኤንድ ባላንስ አለ። ፕሬዝዳንቱ አምባገነን አይደለም " ብለዋል።

● ረቂቅ ሕጉን ማንሳታቸውን በማረጋገጥ ፣ ሕጉን በተመለከተ ግን የተሳሳተ ግንዛቤ መፈጠሩን ጠቅሰዋል። የሕጉ ዓላማ የኬንያውያንን ንግድ ማጠናከረ ነበር በማለተ የተካተቱትን ዕቅዶች ጠቃሚነት አብራርተዋል።

ታሪካዊ ነው በተባለውና ምንም አይነት ቁጥጥር ባልነበረው የ ' X ' ህዝባዊ ግልጽ ውይይት መድረክ ላይ ከ150,000 በላይ ሰዎች ታድመው ነበር። 

ከዚህ በፊት አንድ ፕሬዝዳንት ይህን ያህል በይፋ ወጥቶ እራሱን በማጋለጥ ከሕዝቡ በቀጥታ ለሚቀርቡለት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጠበት ጊዜ ባለመኖሩ ምክንያት ነው ታሪካዊ የተባለው።

ፕሬዝዳንት ሩቶ ሁልጊዜ በሚያስቆጡ እና ጠንከር ያሉ ጉዳዮችን በሚመለከት ክርክር ውስጥ ሲሳተፉ ይታያል።

በፖለቲካ ሕይወታቸው ፈታኝ ጥያቄዎችን እና ሁኔታዎችን ከመጋፈጥ ወደ ኋላ ሲሉም ታይተው አይታወቅም።

በመገናኛ ብዙኃን ዘንድ ከቀደምት ፕሬዝዳንቶች በበለጠ በራቸው ክፍት መሆኑ ይነገራል።


#BBCNEWS
#Kenyans
#CitizenTV

@tikvahEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Africa #Kenya

" በሙስና የተዘፈቀውን ካቢኔዎትን ይበትኑ ! " - የኬንያ አብያተ ክርስቲያናት ብሔራዊ ምክር ቤት

ምንም እንኳን ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ የፋይናንስ ረቂቅ አዋጁን ቢሰርዙም ተቃውሞው ቀጥሏል።

የኬንያ አብያተ ክርስትያናት ፕሬዜዳንቱ ካቢያናቸውን እንዲበትኑ ጠይቀዋል።

የቤተክርስቲያን መሪዎች እና በርከታ ኬንያውያን ሩቶ በሀገሪቱ የተንሰራፋውን ሙስና እንዲያጸዱ ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ።

የኬንያ አብያተ ክርስቲያናት ብሔራዊ ምክር ቤት ፥ " የሩቶ አስተዳደር በመጥፎ አመራር እና የሙስና ክሶች ተጨማልቋል " በማለት የታቅውሞውን ድምጽ ተቀላቅሏል።

ምክር ቤቱ ፥ ሩቶ ሚኒስትሮቻቸውን እንዲያባርሯቸው ጠይቋል።

" ፕሬዚዳንቱ በራሳቸው አንደበት ካቢኔያቸው ብቃት እንደሌለው ተናግረዋል። ኬንያውያንም የፕሬዜዳንቱ ካቢኔ ምንም ብቃት የለውም እያሉ ነው። በተጨማሪ አብዛኛዎቹ የካቢኔ አባላቶች ሙስና ውስጥ የተዘፈቁ ናቸው። ኬንያውያን ካቢኔውን የመበተኛ ጊዜ አሁን ነው እያሉ ነው " ሲል ገልጿል።

በኬንያ የፋይናንስ ረቂቁ ባስነሳው ተቃውሞ ቢያንስ 40 ሰዎች መገደላቸው፤ 380 ሰዎች መጎዳታቸው ፣ ታቃዋሚዎችም ፓርላማውን በመውረር የምክር ቤት አባላት እንዲሸሹ ከሆኑ በኃሏ ሩቶ ረቂቁን ውድቅ አድርገው ነበር።

ሩቶ ከቀናት በፊት ፦
- ቁልፍ ሚኒስትሮችን እና የመንግስት ተቋማትን ማዋሃድ
- የመንግስት መኪናዎች ለ12 ወራት እንዳይገዙ መከልከል
- የመንግስት ባለስልጣናትን አላስፈላጊ የውጭ ጉዞ ማገድን ጨምሮ የተለያዩ የወጪ ቅነሳ እርምጃዎችን ይፋ አድርገው ነበር።

ነገር ግን ተቃውሞው ቀጥሎ ፕሬዜዳንቱ በመስና ተዘፍቋል የተባለውን ካቢኔ እንዲባትኑ ግፊት እየተደረገ ነው።

የኬንያ ፖለቲካ ተንታኝ ዲስማስ ሙአኮ " ፍርድ ቤት አንዳቸውንም በምንም ነገር ጥፋተኛ እስካላላቸው ድረስ ፕሬዜዳንት ሩቶ ሰዎች እንዲባረሩ ስለጠየቁ ብቻ የካቢኔ አባሎቻቸውን የማባረራቸው እድል ዜሮ ነው " ብለዋል።

" ነገር ግን፣ በጣም ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው የኑሮ ውድነቱ ነው። የኢኮኖሚውን ሁኔታ በማሻሻል እና ለኑሮ ውድነቱ መፍትሄ በማምጣት የመንግስት እዳ በአብዛኛው ኬንያውያን ዜጎች ላይ የማይወድቅ መሆኑን ማረጋገጥ ከቻሉ ህዝቡም ተረጋግቶ እስከ 2027 ድረስ (የፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ) መጠበቅ ይችላል " ሲሉ አክለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከቪኦኤ ነው ያገኘው።

#Kenya

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Africa #Kenya " በሙስና የተዘፈቀውን ካቢኔዎትን ይበትኑ ! " - የኬንያ አብያተ ክርስቲያናት ብሔራዊ ምክር ቤት ምንም እንኳን ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ የፋይናንስ ረቂቅ አዋጁን ቢሰርዙም ተቃውሞው ቀጥሏል። የኬንያ አብያተ ክርስትያናት ፕሬዜዳንቱ ካቢያናቸውን እንዲበትኑ ጠይቀዋል። የቤተክርስቲያን መሪዎች እና በርከታ ኬንያውያን ሩቶ በሀገሪቱ የተንሰራፋውን ሙስና እንዲያጸዱ ጥሪ እያቀረቡ…
#Kenya #Update

ሩቶ ካቢኔያቸውን በተኑ።

ለሳምንታት በህዝብ ተቃውሞ ስትናጥ የከረመችው ኬንያ ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ የካቢኔ ሚኒስትሮቻቸውን በተኑ።

ሩቶ ዛሬ ነው ይህን እርምጃ የወሰዱት።

የፕሬዜዳንቱ እርምጃ በመላው ሀገሪቱ ለተነሳው የፀረ መንግሥት ተቃውሞ እንደምላሽ ነው የተወሰደው።

ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ ፥ የካቢኔያቸው ተቀዳሚ ዋና ጸሐፊ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ እንዲሁም ምክትል ፕሬዝደንት ራጋቲ ጋቻጉ ሲቀሩ ሌሎቹን ሚኒስትሮቻቸውን በሙሉ ማሰናበታቸውን ተናግረዋል።

ፕሬዝደንቱ እርምጃውን የወሰዱት የሕዝባቸውን ድምፅ በመስማት መሆኑን ተናግረዋል።

#DW
#CitizenTV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Kenya #Update ሩቶ ካቢኔያቸውን በተኑ። ለሳምንታት በህዝብ ተቃውሞ ስትናጥ የከረመችው ኬንያ ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ የካቢኔ ሚኒስትሮቻቸውን በተኑ። ሩቶ ዛሬ ነው ይህን እርምጃ የወሰዱት። የፕሬዜዳንቱ እርምጃ በመላው ሀገሪቱ ለተነሳው የፀረ መንግሥት ተቃውሞ እንደምላሽ ነው የተወሰደው። ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ ፥ የካቢኔያቸው ተቀዳሚ ዋና ጸሐፊ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ እንዲሁም…
" አዲስ እና ሰፋ ያለ መንግሥት ለመመሥረት ከሕዝቤ ጋር ውይይት አደርጋለሁ ! " - ሩቶ

የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ካቢኔያቸውን በመበተን ሚኒስትሮቻቸውን ከስልጣን ያባረሩት ሕዝቡ ያነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ መሆኑን አሳውቀዋል።

ሩቶ ፥ " ኬንያውያንን በመስማት ካቢኒዬን መርምሬ ነው የወሰንኩት " ብለዋል።

" አዲስ እና ሰፋ ያለ መንግሥት ለመመሥረት ከሕዝቤ ጋር ውይይት አደርጋለሁ " ሲሉም አሳውቀዋል።

ከሥራቸው የማይባረሩት ምክትል ፕሬዝዳንቱና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው የሚያገለግሉት የካቢኔው ዋና ፀሐፊ ሥልጣናቸው ላይ ይቆያሉ።

ሌሎቹ በጠቅላላ የካቢኔያቸው አባላት ሚኒስትሮች ተባረዋል።

የፋይናንስ ረቂቅ ሕጉን ተከትሎ ፥ " ግብር ሊጨመርብን አይገባም በቃን ! ፣ ተጨማሪ ግብር አንከፍልም፣ ሕጉ ኑሮው ያስወድድብናል " በማለት ወጣቶች በማህበራዊ ሚዲያ የጀመሩት ተቃውሞ ወደ አደባባይ ተቃውሞ ተሸጋግሮ የ39 ሰዎች ህይወት ከጠፋ በኋላ ሩቶ ሕጉን ሰርዘውታል።

ምንም እንኳን ሕጉ ሙሉ በሙሉ ቢሰረዝም ተቃውሞው አላበቃም።

ፕሬዜዳንቱ ባልተለመደ ሁኔታ ከተቃዋሚ ወጣቶች ጋር በኦንላይን (X) ምንም አይነት ገደብ የሌለው ግልጽ ሕዝባዊ ውይይት አድርገው ነበር ፤ ያም ቢሆን ሕዝባዊ ጥያቄውን አላስቆመውም።

ፕሬዜዳንቱ በሙስና የተዘፈቁ ሚኒስትሮችን ጠራርገው እንዲያባርሩና ካቢኔውን እንዲበትኑ ጥሪ ሲቀርብ ነበር።

ይህን ተከትሎ ዛሬ ፕሬዜዳንቱ ካቢኔያቸውን በትነዋል።  " የሕዝቤን ድምጽ በመስማት ነው እርምጃውን የወሰድኩት " ብለዋል።

#Kenya
#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" አዲስ እና ሰፋ ያለ መንግሥት ለመመሥረት ከሕዝቤ ጋር ውይይት አደርጋለሁ ! " - ሩቶ የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ካቢኔያቸውን በመበተን ሚኒስትሮቻቸውን ከስልጣን ያባረሩት ሕዝቡ ያነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ መሆኑን አሳውቀዋል። ሩቶ ፥ " ኬንያውያንን በመስማት ካቢኒዬን መርምሬ ነው የወሰንኩት " ብለዋል። " አዲስ እና ሰፋ ያለ መንግሥት ለመመሥረት ከሕዝቤ ጋር ውይይት አደርጋለሁ " ሲሉም አሳውቀዋል።…
የኬንያ ፖሊስ አዛዥ ሥራቸውን ለቀቁ።

በሀገሪቱ በተቀጣጠለው ፀረ መንግሥት ተቃውሞ በርካቶች መሞታቸውን ተከትሎ ጠንካራ ትችት የተሰነዘረባቸው የፖሊስ አዛዥ ጃፌት ኮሜ በዛሬው ዕለት የስንብት ደብዳቤ አስገብተዋል።

የኬንያ ፕሬዝደንት ጽሕፈት ቤትም የኮሜን የስንብት ደብዳቤ ፕሬዝደንት ዊልያል ሩቶ መቀበላቸውን አረጋግጧል።

ጽሕፈት ቤቱ አክሎም በቦታቸው ምክትል የኬንያ ፖሊስ አዛዥ የነበሩት ዳግላስ ካንጃ መተካታቸውን አስታውቋል።

በሀገሪቱ ላይ የተካሄደውን ፀረ መንግሥት ተቃውሞ ያደራጀው ጀነሬሽን Z በአጭሩ ጄን Z የተሰኘው የኬንያ ወጣቶች ስብስብ በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የኃይል እርምጃ ወስዷል ያሉት የኬንያ ፖሊስ አዛዥ ሥልጣናቸውን እንዲቀቁ ግፊት ሲያደርግ ነበር።

ሕዝባዊ ተቃውሞ የበረታባቸው የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ ትላንት ካቢኒያቸውን መበተናቸው ይታወሳል።

#DW
#Kenya

@tikvahethiopia