TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ለጥንቃቄ

በአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክ/ከተማ በተለያየ ቦታ እየተንቀሳቀሱ የመኪና ስፖኪዮ በመስረቅ ወንጀል የተጠረጠሩ 4 ግለሰቦች (ታዳጊ ልጆች) በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።

ተጠርጣሪዎቹ ሚያዚያ 23 እና 24/ 2016 ዓ.ም ወረዳ 2 ጋዜቦ አደባባይ እና ወረዳ 9 አካባቢ ነው የተያዙት ተብሏል።

ተጠርጣሪዎቹ #ከመስቀል፣አደባባይ ወደ #ቦሌ በሚወስደው መንገድ ላይ የትራፊክ መብራቶችና ተሽከርካሪ በሚቆምባቸው ሌሎች ቦታዎች ላይ በመንቀሳቀስ ስፖኪዮ ሲሰርቁ እንደነበር ፖሊስ አመልክቷል።

በዚህ የወንጀል ድርጊት ለይ ተሳትፈው የተገኙት ህፃናቶች መሆናቸውን ገልጿል።

በዚህ መነሻ በተደረገ ምርመራ ለህፃናቱ ስምሪት የሚሰጡ የተደራጁ ወንጀለኞች መኖራቸውን ፖሊስ ማረጋገጡን አሳውቋል።

" አንዳንድ ህፃናት መኪና የሚጠብቁ እንዲሁም ደግሞ እርዳታ የሚፈልጉ መስለው በመቅረብ የወንጀል ተግባራት እንደሚፈፅሙ አሽከርካሪዎች ተገንዝበው በትራፊክ መብራቶችም ሆነ የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው ሌሎች ቦታዎች ላይ ሲቆሙ እና በዝግታ ሲያሽከረክሩ ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል " ሲል ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ🚨

" በከፍተኛ ሁኔታ የሚንቀሳቀስ #የጅብ_መንጋ ተከስቷል ማህበረሰቡ ሊጠነቀቅ ይገባል " - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሠላምና ጸጥታ ቢሮ

ከሰሞኑ በማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል በምሽት አንዳንዴም በቀን ጅቦች በሰው ላይ በተለይ በህጻናት እና ሴቶች እንዲሁም በአቅመደካሞች ላይ ጥቃት እያደረሱ ተነግሯል።

በደረሰን መረጃ በስልጤ ዞን 2 ሰዎች ሲሞቱ በሀዲያ ዞን እንዲሁም በሀላባ አካባቢ ሌሎች 2 የአካል ጉድለት ያደረሱ ጉዳቶች ተመዝግበዋል።

ከሟቾች አንዷ የ3 ዓመት ህጻን ናት። በስልጤ ዞን ላንፉሮ ወረዳ ነዋሪ የሆነችው ይህች ህጻን በእናቷ ጀርባ ላይ ታዝላ (እናትየው ከወፍጮ ቤት እህል አስፈጭታ ስትመለስ) በነበረበት ወቅት አድፍጦ ይጠብቅ በነበረ የተራበ ጅብ ተወስዳ ጉዳት ከደረሰባት በኃላ ህይወቷ አልፏል።

በአጠቃላይ ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ኃላፊ የሆኑትን አቶ ተመስገን ካሳን አነጋግሯቸዋል።

አቶ ተመስገን ፤ በዚህ አመት ከፍተኛ የጅብ መንጋ መፈጠሩን አመልከተዋል። መንጋው ሲበዛ ለረሀብ በመጋለጡ ወደ ሰዎች እንደሚሄድ ገልጸዋል።

እስካሁን በክልሉ የሁለት ሞትና በርካታ ለሞት ያላበቁ ጉዳቶች ሪፖርት እንደደረሳቸዉ ጠቅሰዉ ጉዳቱ በህጻናት ላይ የበረታ መሆኑን ተናግረዋል።

አሁን ላይ ባካሄዱት ግምገማ መንጋዉ ከፍተኛ ቁጥር ያለው እንደሆነ ገልጸዋል። ይህን ለማጥፋት ከሚመለከተዉ አካል ጋር እየተነጋገሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ማህበረሰቡ ግን የራሱን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ🚨

“ በጀኔተር ላይ በተነሳ የእሳት አደጋ የ1 ሰው ሕይወት አልፏል ” - አቶ ንጋቱ ማሞ

ትላንት ምሽት 3:03 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ማርያም ማዞሪያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በእሳት አደጋ የ1 ሰው ሕይወት ማለፉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና ሥራ አመራር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያው አቶ ንጋቱ ማሞ በሰጡት ቃል፣ “ ኤሌክትሪክ በመቋረጡ ጀነሬተር ለማስነሳት ነዳጅ በመጨመር ላይ የነበረ የ26 ዓመት የሆቴል ሠራተኛ በጀነሬተሩ ላይ በተነሳ የእሳት አደጋ ወዲያው ሕይወቱ አልፏል ” ብለዋል።

“ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች በስፍራው ፈጥነው ቢደርሱም በጀነሬተሩ ላይ በተፈጠረው ከፍተኛ እሳት አስቀድሞ ሕይወቱ  አልፏል ” ነው ያሉት።

አቶ ንጋቱ፣ “ በጄኔሬተር የነዳጅ ታንከር ውስጥ ነዳጅ ከተጨመረ በኋላ #ቫልቩ በአግባቡ መዘጋቱን ማረጋገጥ ፣ እንዲሁም ጄነሬተሩ አስቀድሞ አገልግሎት ሲሰጥ ከቆየና ግለት ካለ ነዳጅ ከመጨመር መቆጠብ ያስፈልጋል ” ሲሉ አስገንዝበዋል።

በሌላ በኩል ፥ የበዓል ስራዎች እንቅስቃሴዎች አሁንም ድረስ ያልጠተናቀቁ በመሆኑ ህብረተሰቡ ከኮሚሽን መስሪያ ቤቱ እየተላለፉ ያሉ የጥንቃቄ መልዕክቶች እንዲተገብር አሳስበዋል።

የእሳትና ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች ሲያጋጥሙ ፣ እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎት ማህበረሰቡ በኮሚሽኑ ስልክ #በ939 ላይ ፈጥኖ ደውሎ እንዲያሳውቅ ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪ መረጃ ፤ የአዲስ አበባ ፖሊስ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በስሊንደር ፍንዳታ ምክንያት የ1 ሰው ህይወት ማለፉን ገልጿል።

የድሮው ቄራ አካባቢ ትላንት ቀን 9:30 በአነስተኛ መጠጥ ቤት ውስጥ ድስት ተጥዶበት በነበረ ስሊንደር ላይ በተፈጠረው ፍንዳታ ዕድሜው 30 ዓመት የሚገመት 1 ሰው ህይወቱ ያለፈ ሲሆን በ3 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ህክምና ተወስደዋል።

ፖሊስ በበዓል ወቅት የምንጠቀማቸውን ምግቦች ስናበስል #ከሲልንደር_አጠቃቀም ጋር በተያያዘ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ_ከጠቀማችሁ

1. በአዲስ አበባ ከተማ የሜትር ታክሲ አገልግሎት የምትሰጡ ወንድም እህቶቻችን እባካችሁ ጥንቃቄ አድርጉ።

ማክሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ገደማ ወደ ጎተራ ማሰለጫ መውረጃ ወይም በተቃራኒ ወደ ቄራ የሚወስደው መስቀለኛ መንገድ አካባቢ አንድ አገልግሎት ሰጪን 3 ተሳፋሪ መስለው የገቡ ወንበዴዎች መሃል አስፓልት ፣ በብዛት መኪና በሚመላለስበት መንገድ ላይ ከውስጥ እቃ ይዘው ሲሮጡ መመልከቱን አንድ የቤተሰባችን አባል መልዕክት አጋርቶናል።

ሹፌሩ ከመኪና ውስጥ አልወረደም ነበር። ምናልባት ቢወርድ ሌላ የነሱ ተባባሪዎች መኪናውን ይዘው ለመጥፋት አስበውም ሊሆን ይችላል ብሏል።

እነዚህ 3 ሰዎች ሁለቱ ከኋላ አንዱ ከፊት የነበሩ ሲሆን በፍጥነት የመኪናውን በር ከፍተው እቃ ይዘው ሲሮጡ ነው የተመለከታቸው።

" ፈጣሪ ነው የሚጠብቀን ነገር ግን በተለይ ምሽት ላይ ስንሰራ የምንጭናቸውን ሰዎች ፦
- ማንነት፣
- ስልክ ቁጥር ፣
- የምንሄድበትን ቦታ ፣
- የሰዎቹን ሁኔታ ድርጊታቸውን፣
- ንግግራቸውን በደንብ እንከታተል። ውስጣችን ጥሩ ስሜት ካልተሰማውም ይቅርብን " ብሏል።

ህይወታቸውን ለማሻሻል፣ ቤተሰባቸውን ለመደገፍ ፣ ልጆቻቸውን ለማኖር ሲሉ ብርድ እና ፀሀይ እየተፈራረቀባቸው ቀን ፣ ምሽት ፣ ለሊት ሳይሉ የሚሰሩ ወገኖቻችንን ፈጣሪ ከክፉ ይጠብቃቸው።

ዘራፊዎችም ዛሬ ላይ ተይዘው ነገ የሚለቀቁ ከሆነ ከወንብድና ተግባራቸው ስለማይመለሱ እጅግ ጠንካራ ቅጣት ሊጣልባቸው ይገባል።

የሰረቁበትን ቀን እንዲረግሙ የሚያደርግ ቅጣት ሊጠብቃቸው ይገባል።

ሰው ለልጆቹ ፣ ለቤተሰቦቹ ለራሱ ህይወት ሲል ከባድ ዋጋ እየከፈለና በሰላም ጥሩ ሰራተኛ ዜጋ ሆኖ ሀገሩን ህዝቡን እያገለገለ ካለ በበቂ ሁኔታ ከወንጀል ሊጠበቅ ይገባዋል።

2. በመኪና ተደራጅተ የሚዘርፉ ዛራፊዎች አሁንም በከተማው አሉ።

በቅርቡ ፥ መካኒሳ አካባቢ አንድ ግለሰብ በገዛ ሰፈሩ ያውም ጠዋት ላይ በ " ቪትዝ " ተሽከርካሪ የመጡ ወንበዴዎች አንገቱን በማነቅ ንብረቱን ዘርፈው መሬት ላይ ጥለውት ጠፍተዋል።

" አውቶብስ ተራ " አካባቢ በተመሳሳይ አንድ ወጣት በ ' ቪትዝ ' ተሽከርካሪ ላይ በመሆንና ውሃ በመድፋት " ና እንጥረግልህ " በማለት ለመዝረፍ ሙከራ አድርገዋል ፤ ምንም እንኳ ክፉ ሃሳባቸው ባይሳካም።

እነዚህ ባለመኪና ወንበዴዌች ምናልባት ብዙ ቦታ መሰል ተግባራትን እየፈጸሙ ይሆናል።

ከወራት በፊት ሩወንዳ አካባቢ ለሊት በ ' DX መኪና ' ተደራጅተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ወንበዴዎች አንድን ግለሰብ ሞባይል ስልክ በገጀራ አስፈራርተው መዝረፋቸውን ነግረናችሁ ነበር።

መኪና የምታከራዩ ወይም መኪና ለሰው የምትሰጡት ሰዎችም ጥንቃቄ አድርጉ ማነው ፣ ለምን አገልግሎት እየተጠቀመ ነው የሚለውን አጣሩ።

ፖሊስ ይህንን ጉዳይ ከምንጩ ለማድረቅ መስራት አለበት።

በከተማው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመንገድ ትራፊክ መብራት ላይ ስርቆት በጅጉ ቀንሷል። ይህ አበረታች ተግባር ጭራሽ መኪና ይዘው ለዝርፊያ በተሰማሩ አካላት ላይም መቀጠል አለበት።

ሰዎች ቀንም ይሁን ማታ ሳይሳቀቁ መንቀሳቀስ እንዲችሉ መደረግ አለበት። ህግ ቀን ቀን ብቻ የሚሰራ ማታ የማይሰራ እስኪመስል ድረስ ዘራፊዎች የሚያደርጉን እንቅስቃሴ መገታት መቻል አለበት።

3. የጸጥታ አካላትን የሚመስል ልብስ ለብሰው የሚዘርፉም አሉ።

አንድ የቤተሰባችን አባል በመንገዱ የገመጠውን አጋርቶናል።

ድርጊቱ የተፈጸመው በዚህ ወር  አለርት ሆስፒታል አካባቢ ነው።

መኪናውን እያሽከረከረ በሚሄድበት ወቅት የጸጥታ ኃይል ልብስ የሚመስል የለበሱ በግሩፕ የተሰባሰቡ ሰዎች (8-10) ድቅድቅ ያለ ጨለማ ውስጥ ሆነው ሊያስቆሙት ይሞክራሉ።

ነገር ግን እውነተኛ እና ትክክለኛ የጸጥታ አካላት ሰዎች እንዳልሆኑ ይጠረጥራል። ምክንያቱም ከዚህ ቦታ በፊት (ብዙም ሳይርቅ) ሌላ የደህንነት ፍተሻ ተፈትሾ ነበር።

እንዚህ ሰዎች ቁም ያሉት ቦታ ድቅድቅ ጨለማ እና የሚያስፈራ ስለነበር ወደፊት ትቷቸው ሲሄድ ሁለት የተጎዱ ሰዎች መሬት ላይ ተኝተው ተመልክቷል። ሌላ መኪና ስላልነበረና ለህይወቱም በመስጋቱ በፍጥነት ከቦታው ርቆ ሄዷል።

ምናልባት እነዚህ ሰዎች ለፍተሻ ብለው መኪናቸውን አስቁመዋቸው ዘርፈዋቸው ሊሆን እንደሚችል ጥርጣሬውን ገልጿል።

የፖሊስ የደህንነት ፍተሻ በጣም አስፈላጊ ቢሆንም ከየትኛውም አካል ፍቃድ ሳያገኙ ለመሰል እንቅስቃሴ የሚሰማሩ ካሉ አጥንቶ እርምጃ መውሰድ ይገባል። የማያዳግም አስተማሪ ቅጣትም መቀጣት ይገባል።

ሌላው የየትኛውም የሀገሪቱ የጸጥታ ልብስ በሲቪል ሰዎች / አባል ባልሆኑ ሰዎች እየተለበሰ በማኛውም መንገድ ሚዲያ ላይም ጭምር መታየት የለበትም። ሁሉም ሰው ለፍቶ ነው የክብር ልብሱን የሚለብሰውና ማንም እየተነሳ የጸጥታ ልብስ እየለበሰ መታየት ሌላውም ይህን እንዲለማመድ መደረግ የለበትም ፤ ልብሱም መከበር አለበት።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

#ቲክቫህኢትዮጵያ
#አዲስአበባ

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ🚨

“ በተለይ እንቅስቃሴያቸውንና ኑራቸውን አፋፍ ሥር ያደረጉ ነዋሪዎች ጥንቃቄ ያድርጉ " - ኮሚሽኑ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 በተለምዶ ሰላም ሰፈር አካባቢ 4 ሜትር ከሚገመት ከፍተኛ ቦታ በተከሰተ የአለት ናዳ 3 ሰዎች መሞታቸውን የእሳትና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል።

አደጋው የደረሰው ዛሬ ነው።

የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች ባደረጉት ጥረት የ8 ሰዎች ሕይወት ማትረፍ ተችሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦
- የአደጋው ምንስኤ ምንድን ነው ?
- ይህ አደጋ በከተማዋ ሲከሰት ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ?
- ማህበረሰቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት? የሚሉ ጥያቄዎችን ለኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ አቅርቧል፡፡

አቶ ንጋቱ ምን ምላሽ ሰጡ ?

“ እንዲህ አይነት አደጋዎች በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ መሆኑ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ሜትሮሎጅ ኢንስቲትዩትም የመሬት መንሸራተት፣ ጎርፍ አደጋ ሊያጋጥም ስለሚችል ጥንቃቄ ይደረግ የሚል መረጃ ሲያስተላልፍ ነበር፡፡

ያልተጠበቀ ዝናብ ያጋጥማቸዋል የተባሉ ከተሞችን ሲጠቅስም አዲስ አበባም እዛ ውስጥ ተጠቅሳለች፡፡

በእርጥበት ምክንያት ናዳ፣ የአፈር መደርመስ ሊኖር ስለሚችል በተለይ እንቅስቃሴያቸውንና ኑራቸውን አፋፍ ሥር ያደረጉ ነዋሪዎች ጥንቃቄ ያድርጉ፡፡

ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች ላይ መፍትሄ ለመስጠት በሚደረገው ጥረትም የመፍትሄው አካል መሆን ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ ሰዎችን ከቦታው ማንሳት ሊያስፈልግ ይችላል።

አዲስ አበባ ላይ የአለት ናዳ አደጋ አጋጥሞ አያውቅም፣ አላስታውስም፡፡ በእርግጥ ደረጃቸውን ያልጠበቁ፣ የአደጋ ደህንነት መስፈርት ሳይጠብቁ አፋፍ ላይ የተሰሩ ቤቶች ተንደው የሰው ሕይወት ጠፍቶ ያውቃል።

ጠሮ መስጂድ የሚባለው (አዲስ ከተማ ፍለ ከተማ ውስጥ) ሰባት ሰዎች ሕይወታቸው ያለፈበት ሁኔታ ነበር ከኮንስትራክሽን ጥራት ጋር በተያያዘ፡፡

ይሄኛው (የአሁኑ የአለት አደጋ) እዛው መሬቱ ጋር ተያይዞ የበቀለው አለት ከዝናብ ብዛት በመሬት መሸርሸር የሚያጋጥም ነው፡፡

የአለት አደጋውን መስንስኤ ማጣራት የሚጠይቅ ነው ግን ከክረምቱ ወቅት ጋር የሚያያዝ ሊሆን ይችላል ብለን እንገምታለን፡፡ አደጋ የደረሰባቸው መኖሪያ ቤቶቹ ከታች ነው ያሉት፤ አለቱ ደግሞ አፋፍ ላይ ነው ያለው፡፡ በግምት ወደ 4 ሜትር ከፍታ አለው፡፡

ብዙ ጊዜ አፋፍ ላይ ተንጠልጥለው ያሉ ቤቶች ላይ የመውደቅ እድልም አለው፡፡ የሰዎቹም የአኗኗር ሁኔታ፣ የቤቱ አቀማመጥና ደረጃ አስተዋጽኦ አድርጓል። ”


#TikvaEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ

“ የኢትዮ ቴሌኮም ነጻ ዳታ ሽልማት ለሁሉም አሮጌ ሲም ካርድ ተጠቃሚዎች ” በሚል ሰሞኑን ነጻ ሜጋ ባይት ለማግኘት “ ሊንክ ጠቅ ያድርጉ ” የሚል መልዕክት በማኅበራዊ ሚዲያዎች አማካኝነት ወደተለያዩ ግለሰቦች እየተላከና እየተዘዋወረ ነው፡፡

ይሄው ከሥሩ ሊንክ የተቀመጠበት የሚዘዋወረው መልዕክት ፡-
➡️ 6 ወር ለቆየ ሲም፣ 10GB
➡️ 1 ዓመትና ከዚያ በላይ፣ 20GB
➡️ ከ5 አመት በላይ ለቆየ ሲም፣ 50GB ነጻ ሽልማት ኢትዮ ቴሌኮም እየሰጠ መሆኑን የሚገልጽ ነው፡፡

አንዳንድ ሊንኩን የከፈቱ ሰዎችም፣ “ ስንከፍተው መረጃዎት እየተበረበረ ነው ይላል፡፡ ጉድ ተሰርተናል ” ሲሉ የተስተዋሉ ሲሆን፣ ብዙዎች ደግሞ ይህን ጉዳይ ኢትዮ ቴሌኮም ያውቀዋል ? በማለት እየጠየቁ ነው፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ የሚዘዋወረውን መልዕክት ተቋሙ ያውቀዋል? ትክክለኛስ ነው? ሲል ኢትዮ ቴሌኮምን ጠይቋል፡፡

የተቋሙ ቺፍ ኮሚዩኒኬሽን ኢፊሰር አቶ መሳይ ውብሸት ምን ምላሽ ሰጡ ?

“ የኛ ቲምም ቼክ አድርጎታል፡፡ Phishing የሚሉት የማጭበርበር መልዕክቶችን የሚልኩ ናቸው፡፡

ታማኝ ከሆኑ ካምፓኒዎች የሚላኩ መልዕክቶችን በማስመስልና የሰዎችን መረጃ የሚወስዱ Phishing  ብለን የምንጠራቸው የሳይበር ጥቃት መንገዶች ናቸው፡፡

እኛ ያስቀመጥነውም እንሰጣለን ያልነው ሽልማትም የለም፡፡ የላክነውም መልዕክት የለም፡፡ የኛ የሴኩሪቲ ቲምም እየተከታተለ ነው፡፡

ሊንክ ልከው እርሱን ንኩ ነው ‘ንኩ’ የሚሉት የእድሉ ተጠቃሚ ለመሆን፡፡ ግን ፐርሰናል መረጃዎችን የመውሰድና ላልተገባ ነገር ሰዎችን ለመዳረግ የሚያደርጉት ጥረት ነው፡፡

ዌብሳይቶቹን የኛ ቲሞች ሞኒተር እያደረጉ ሰዎች ላይ ጥቃት እንዳይደርስ ቁጥጥር እያደረጉ ነው፡፡

ሳይቶቹን የመዝጋት ሥራዎች እየተሰሩ ነው በቅንጅት፡፡ ስህተት እንደሆነ፣ የኛ እንዳልሆነ ሰው እንዲያውቅ እናደርጋለን፡፡

ይኛው መልኩን ቀይሮ የሰውን መረጃ ለመውሰድ ሆነ እንጂ ብዙ ጊዜ በተለይ ቴሌግራም አካባቢ ላይ ተከታይ ለማግኘት በኢትዮ ቴሌኮም፣ በቴሌ ብር እየተከፈቱ ደንበኛ ለማብዛት የሚደረጉ ጥረቶች አሉ፡፡

ይሄም ኢንቴንሽኑ ሌላ ቢሆንም ያው ነው፡፡ ከእኛም ብቻ አይደለም ምንጩን ስናጣራው ከሌላ አገር ውስጥ የሚመጣ፣ ወደ ሌላ አገር ሪፈር የሚያደርግ ነው ሊንኩ፡፡

የትልልቅ ተቋማት መልዕክት በማስመስል ሊንኮችን አስቀምጠው አጓጊ ሽልማቶችን እየሰጡ የሰዎችን መረጃ የማጭበበርበር ነገር ነው የሚፈጠረውና Phishing በተለያዬ በኢሜይል፣ በቴክስት፣ በጥሪ መልክም ሊመጣ ይችላል፡፡

ሰዎች ሊንኩን ባለመንካት ከእንደዚህ አይነት አሳሳች መልዕክቶች ራሳቸውን ይጠብቁ፡፡ እንዲህ አይነት ጉዳይ ሲገጥማቸውም በ9090 በነጻ ደውለው በዚያ እንዲያሳውቁንም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ”
ብለዋል፡፡

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) በበኩሉ፣  “ የኢትዮ ቴሌኮም ነጻ ዳታ ስልማት ለሁሉም አሮጌ ሲም ካርድ ተጠቃሚዎች ” በሚል መልዕክቶች ወደ ተለያዩ ግለሰቦች እየተላኩ መሆኑን እንዳረጋገጠ አስታውቋል፡፡

አስተዳደሩ፣ “ መልዕክቱ የግለሰቦችን ሚስጥራዊ መረጃዎችን የማጥመድ ጥቃት (Phishing Attack) መሆኑን ማረግገጥ ችያለሁ ” ብሎ፣ ግለሰቦች ሊንኩን ባለመክፈት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia