TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
⛽️ነዳጅ ቀድተው ለክፍያ ቴሌብር ሲሆን ምርጫዎ...

🛒ሁልጊዜ ኪስ አይሞላምና ለግብይት ክፍያ የጎደለን የሚሞላው ቴሌብር  እንደኪሴ እስከ 2000 ብር
🫰እንዲሁም እስከ 6,000 ብር የቴሌብር መላ የብድር ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ በደስታ እንገልጻለን!

በቴሌብር ሱፐርአፕ  http://onelink.to/fpgu4m ወይም *127#  የፋይናንሺያል አገልግሎት ስር እንደኪሴ እና መላ አገልግሎቶችን ያስጀምሩ
#Bank_of_Abyssinia

አቢሲንያ ባንክ ለዕድሮች ባዘጋጀው ዕድል ለመጠቀም አሁኑኑ ወደ ቅርንጫፎች ጎራ ይበሉ።

ለበለጠ መረጃ ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡፡ https://www.bankofabyssinia.com/saving-account/

#Edir #BankofAbyssinia  #BankingService  #DigitalEthiopia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
" ካለፈው ሃምሌ ወር አንስቶ በትንሹ 183 ሰዎች ተገድለዋል " - ተመድ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ቢሮ ዛሬ ማክሰኞ መግለጫ አውጥቷል።

ምን አለ ?

- በአንዳንድ የኢትዮጵያ ክልሎች ያለው የሰብአዊ መብት ሁኔታ መባባሱ በጣም ያሳስበናል ብሏል።

- ከሀምሌ ወር አስቶ በአማራ ክልል በተቀሰቀሰ ግጭት በትንሹ 183 ሰዎች መገደላቸውን ካሰባሰብነው መረጃ መረዳት ችለናል ሲል ገልጿል።

- አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀ በኃላ በመላው ኢትዮጵያ ከ1,000 በላይ ሰዎች መታሰራቸው መረጃ ደርሶናል ፤ ከታሰሩት መካከል ብዙዎቹ የፋኖ ደጋፊዎች ተብለው የተጠረጠሩ የአማራ ብሄር ተወላጅ ወጣቶች ናቸው ብሏል። ከነሃሴ መጀመሪያ አንስቶ የቤት ለቤት ፍተሻ ሲደረግ እንደነበር ፤ በአማራ ክልል ስላለው ሁኔታ ሲዘግቡ የነበሩ 3 ጋዜጠኞችም መታሰራቸውን ገልጿል።

- እስረኞቹ መሰረታዊ ነገሮች በሌላቸውና ምቹ ባልሆኑ የማቆያ ማዕከላት ውስጥ እንዲቀመጡ መደረጉ አመልክቷል።

- ባለሥልጣናት የጅምላ እስራት እንዲያቆሙ፣ ማንኛውም የነፃነት መነፈግ ድርጊት በፍርድ ቤት እንዲታይ እና በዘፈቀደ የታሰሩ እንዲፈቱ ጠይቋል።

- ባለሥልጣናት የታሰሩ ሰዎች ሁኔታ ዓለም አቀፍ ደንቦችን እና ደረጃዎችን የሚያከብሩ መሆናቸውን ማረጋገጥ እንዳለባቸው እንዲሁም የተመድ የሰብአዊ መብት ጽ/ቤት እና የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ተቆጣጣሪ አካላት ሁሉንም የእስር ቦታዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲያዩ እንዲፈቅዱ ጠይቋል።

- በተወሰኑ የአማራ ክልል ከተሞች የፌደራል ሃይሎች መኖራቸውን ተከትሎ የፋኖ ታጣቂዎች ወደ ገጠራማ አካባቢዎች ማፈግፈጋቸውን የገለፀው ተመድ ሁሉም ተዋናዮች ግድያ፣ ጥቃትና ሌሎች ጥሰቶች እንዲያቆሙ ጠይቋል። ቅሬታዎች በውይይት እና በፖለቲካ ሂደት መፍታት አለባቸውም ብሏል።

- በምዕራብ ትግራይ አወዛጋቢ ቦታዎች ከ250 የማያንሱ የትግራይ ተወላጆች በአማራ ፖሊስ፣ በአካባቢው ባለስልጣናት እንዲሁም በአካባቢው ታጣቂዎችና በታጠቁ የወልቃይት ተወላጆች ባካሄዱት ዘመቻ መታሰራቸውን ገልጿል። በኃላም ወደ ትግራይ ጊዜው አስተዳደር ስር ወዳለ አካባቢ በታጠቁ የወልቃይት ወጣቶች እየተወሰዱ ሳለ በመከላከያ ሰራዊት እጅ መግባታቸውና በኃላም መከላከያ ልየታ አደርጎ የትግራይ ተወላጆቹ ወደ ምዕራብ ትግራይ እንዲመለሱ ወይም እዛው በጊዜዊ አስተዳደሩ ስር ባለ አካባቢ እንዲሆኑ የሚል ምርጫ እንደሰጣቸው ገልጿል።

- በኦሮሚያ ክልልም የሰብአዊ መብት ረገጣ እና ወንጀሎች መቀጠላቸውን በማመልከትም በአሁኑ ወቅት በክልሉ ያለው ሁኔታ አሳሳቢ ነው ብሏል።

(የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ከነዳጅ ዋጋ 📈

ቤንዚን እና ናፍጣ ላይ በሊትር ከ5 ብር በላይ ጭማሪ ተደረገ።

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ጭማሪ ተደርጓል።

ከዛሬ ጀምሮ ለአንድ ወር የሚቆይ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ይፋ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ገልጿል።

ሚኒስቴሩ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ የዓለም ነዳጅ ዋጋ ከሚያዝያ ወር 2015 ጀምሮ እስከሰኔ ወር መጨረሻ ድረስ አንጻራዊ መረጋጋት እንደታየበት ገልጿል፡፡

በዚህም ፥ ላለፉት አራት ወራት በችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ለውጥ ሳይደረግ መቆየቱን አስታውሷል፡፡

ሆኖም ግን የዓለም ነዳጅ ዋጋ ከሐምሌ ጀምሮ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እያሳየ በመምጣቱ ዋጋውን ማሻሻያ ማድረግ ማስፈለጉ ተገልጿል፡፡

በዚሁ መሰረት ፦

1. ቤንዚን 👉 74 ብር ከ85 ሳንቲም በሊትር

2. ነጭ ናፍጣ 👉 76 ብር ከ34 ሳንቲም በሊትር

3. ኬሮሲን ብር 👉 76 ብር ከ34 ሳንቲም በሊትር

4. የአውሮፕላን ነዳጅ 👉 68 ብር ከ58 ሳንቲም በሊትር

5. ቀላል ጥቁር ናፍጣ 👉 62 ብር ከ22 ሳንቲም በሊትር

6. ከባድ ጥቁር ናፍጣ 👉 61 ብር ከ07 ሳንቲም በሊትር መሆኑ ተገልጿል።

ምንጭ፦ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከነዳጅ ዋጋ 📈 ቤንዚን እና ናፍጣ ላይ በሊትር ከ5 ብር በላይ ጭማሪ ተደረገ። የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ጭማሪ ተደርጓል። ከዛሬ ጀምሮ ለአንድ ወር የሚቆይ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ይፋ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ገልጿል። ሚኒስቴሩ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ የዓለም ነዳጅ ዋጋ ከሚያዝያ ወር 2015 ጀምሮ እስከሰኔ ወር መጨረሻ ድረስ አንጻራዊ መረጋጋት እንደታየበት ገልጿል፡፡ በዚህም…
በነዳጅ ምርቶች ላይ የተደረገው ጭማሪ ምን ያህል ነው ?

ላለፉት አራት ወራት ማለትም እስከ ትላንት ድረስ ቤንዚን በሊትር 69 ብር ከ52 ሳንቲም ሲሸጥ የነበረ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ ግን በሊትር 74 ብር ከ85 ሳንቲም እንዲሸጥ ተወስኗል።

ነጭ ናፍጣ በሊትር 71 ብር ከ15 ሳንቲም ሲሸጥ የነበረ ሲሆን ወደ 76 ብር ከ34 ሳንቲም ከፍ ብሏል።

የቤንዚን እንዲሁም የነጭ ናፍጣ ላይ የደረገው የዋጋ ጭማሪ ከ5 ብር በላይ ነው።

ኬሮሲን በሊትር 71 ብር ከ15 ሳንቲም ሲሸጥ የነበረ ሲሆን ከ5 ብር በላይ ጭማሪ ተደርጎ በሊትር 76 ብር ከ34 ሳንቲም ገብቷል።

የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 65 ብር ከ35 ሳንቲም የነበረው ከ3 ብር በላይ ጭማሪ ተደርጎ አሁን 68 ብር ከ58 ሳንቲም በሊትር ገብቷል።

ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 57 ብር ከ97 ሳንቲም የነበረው ከ4 ብር በላይ ጭማሪ ረደርጎ 62 ብር ከ22 ሳንቲም በሊትር ገብቷል።

ከባድ ጥቁር ናፍጣ ደግሞ በሊትር 56 ብር ከ63 ሳንቲም የነበረው 61 ብር ከ07 ሳንቲም ገብቷል።

ሚያዚያ ወር 2015 ላይ ጭማሪ ከተደረገ በኃላ እስከ ትላንት ድረስ የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ሳይደረግ ባለበት እንዲቀጥል ተወስኖ የነበረ ሲሆን የዓለም የነዳጅ ዋጋ በመጨመሩ ምክንያት አሁን ላይ የነዳጅ ዋጋ መጨመር እንዳስፈለገ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#Amhara

በአማራ ክልል ፤ ምንም እንኳን የትጥቅ ግጭቶች ከከተማ ወጣ ባሉ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ቀጥለው የነበር ቢሆንም ከሰሞኑን ግን እንደ ደብረ ታቦር እና ደብረ ማርቆስ ባሉ ትልልቅ ከተሞች ዳግመኛ የከተማ ውስጥ ግጭት ተደርጎ በርካታ ሰዎች መሞታቸው ታውቋል።

በደብረ ታቦር ካለፈው ቅዳሜ እስከ ሰኞ ድረስ በከተማ ውስጥ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በተደረገ የተኩስ ልውውጥ በርካታ ሲቪል ሰዎች መጎዳታቸውን ፣ ተቋማትም መጎዳታቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

በተለይ ባለፈው ቅዳሜ እና እሁድ፣ ሰኞም በነበረ ግጭት የንፁሃን ዜጎች ህይወት አልፎ እንደነበር በርካቶችም ቆስለው ወደብረ ታቦር ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ገብተው እንደነበር ታውቋል።

አንድ ስማቸው እንዲነገር ያልፈለጉ የሆስፒታሉ ምንጭ፤ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሆስፒታሉ በከባድ መሳሪያ ተመታ እየተባለ የሚሰራጨው ወሬ ሀሰት ነው ሲሉ ለቪኦኤ ተናግረዋል።

" ሆስፒታሉ ምንም አልተመታም ውሸት ነው ፤ የተወሰነ ተኩስ ሲለዋወጡ አንድ አስታማሚ በአጋጣሚ ሲያልፍ ተመቶ ቆስሎ እየታከመ ነው። ከዛ ውጭ ሆስፒታሉ አልተመታም ሌላውም ደህና ነው። አሉባልታ ነው በጣም ብዙ ሰው ይሄን ጠይቆኝ ነበር " ብለዋል።

በደብረ ታቦር የሚኖሩ አንድ ነዋሪ በከተማው በተደረገው የተኩስ ልውውጥ የሁለት ልጆች አባት የሆኑ መምህር ጓደኛቸው መገደላቸውን ገልጸው ቀብራቸው ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን መፈፀሙን ገልጸዋል።

እስካሁን ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ንፁሃን መገደላቸውን ተናግረዋል።

ትላንት ማክሰኞ ባለፉት ቀናት በነበረው ግጭት የተገደሉ ሰዎችን አንስቶ የመቅበር ስራ ሲሰራ እንደነበር ፣ ተኩስም እንደቆመ፣ እንቅስቃሴ ቆሞ ከተማው ጭር እንዳለ እኚሁ ነዋሪ ጠቁመዋል።

በደብረ ማርቆስ በተመሳሳይ ካለፈው ቅዳሜ አንስቶ ግጭት አገርሽቶ የከተማ ውስጥ የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ እንደነበር ነዋሪዎች የገለፁ ሲሆን ትላንት አንስቶ ግን ከከተማው ውጭ ከሚደረግ የተኩስ ልውውጥ ውጭ ከተማው ፀጥ እንዳለች መሆኑን ገልጸዋል።

በከተማው ከሰሞኑን በነበረው ግጭት የሰዎች ህይወት መጥፋቱን አመልክተዋል።

መረጃው የቪኦኤ ነው።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
" ይሄንን ሙሰኛ አስተዳደር በማስወገድ ሰላምን ለማስፈን ወስነናል " - የጋቦን ወታደሮች

በጋቦን መፈንቅለ መንግሥት ተደረገ።

ባሳለፍነው ቅዳሜ በአፍሪካዊቷ ሀገር ጋቦን ምርጫ ተደርጎ ነበር በዚህም ምርጫ ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎ ማሸናፋቸው ተነግሮ ነበር።

ነገር ግን የሀገሪቱ ወታደሮችየተካሄደውን ምርጫ ውጤት በመሻር ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎን ከስልጣን ገልብጠው መንበሩን መቆጣጠራቸውን አሳውቀዋል።

በአገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቭዥን ጣቢያ ' ጋቦን 24 ' ላይ ቀርበው ወታደራዊ አመራሮች ባስተላለፉት መልዕክት " የጋቦንን አስተዳደር ይዘናል " ብለዋል።

ቴሌቪዥን ጣቢያው ላይ ከቀረቡት ወታደሮች አንደኛው " ይሄንን ሙሰኛ አስተዳደር በማስወገድ ሰላምን ለማስፈን ወስነናል " ብሏል።

" አስተዳደሩ ኃላፊነት የጎደለውና ወዴት እንደሚሄድ የማይታወቅ ስለሆነ የአገሪቱን ማኅበራዊ ኑሮ በማመሳቀል ወደ ቀውስ ከቶናል " ሲልም ገልጿል።

በብሔራዊ ቴሌቭዥኑ የቀረቡት 12 ወታደሮች ሲሆኑ ፕሬዜዳንት አሊ ቦንጎ ያሸነፉበትን የምርጫውን ውጤት እንደሰረዙት ገልጸዋል።

የሀገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን እንዳለው ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎ ሁለት ሦስተኛ ድምጽ አግኝተው ነበር ምርጫውን ያሸነፉት።

ተቃዋሚዎች ግን ምርጫው ተጭበርብሯል ብለዋል።

በወታደራዊ አመራሮች ከሥልጣን ተወግዷል የተባለው የአሊ ቦንጎ ቤተሰብ ጋቦንን #ለ56_ዓመታት መርቷል ፤ ከነዚህ አመታት ውስጥ አሊ ቦንጎ ብቻቸው 14 ዓመት ሀገሪቱን መርተዋል።

አሊ ቦንጎ ከዚህ ቀደም 2019 ላይ መፈንቅለ መንግሥት ተሞክሮባቸው ከሽፎ ነበር።

በአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት መፈንቅለ መንግሥት ሲደረግ በተደጋጋሚ መሰማቱ ይታወቃል።

በቅርቡ እራሱ በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ኒጀር #ወታደሮች መፈንቅለ መንግሥት አውጀው ስልጣን እንደያዙ ናቸው።

ከዚህ ባለፈ ማሊ እና ቡርኪና ፋሶ በቅርብ ዓመታት በመፈንቅለ መንግሥት ምክንያት ታምሰው እንደነበር አይዘነጋም።

መረጃው ከቢቢሲ፣ አልጀዚራ፣ እና ከሌሎች መገናኛ ብዙሃን የተሰበሰበ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
መንግሥት የከለከለው ሰልፍ ... በሳምንቱ መጀመሪያ ሰኞ በአደባባይ ሊከበር የነበረው የሰራተኞች በዓል (ሜይዴይ) በመንግስት መከልከሉ ይታወሳል። በዚህ ዙርያ የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ምን አሉ ? አቶ ካሳሁን ፎሎ ፦ " የእኛ አላማ የነበረው የሰራተኛውን ጥያቄ ይዘን በመላው ከተማ ሳይሆን በመስቀል አደባባይ ብቻ ማክበር እና ጥያቄዎቻችንን በሰላም ማቅረብ…
#Update

ዛሬ ከሰዓት የኢትዮጵያ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚዎች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ጋር ተገናኝተው ተነጋገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኢትዮጵያ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር " መልካም የሥራ ግንኙነት ስለመፍጠር " መወያየታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት አሳውቋል።

ውይይቱን በተመለከተ ዝርዝር መረጃ ይፋ አልተደረገም።

ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) አንገብጋቢ ባላቸው የሠራተኞች ጥያቄዎች ላይ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድን አግኝቶ ማነጋገር #ግድ እና #ብቸኛ አማራጭ መሆኑን ገልጾ ነበር።

ኮንፌዴሬሽኑ ዘንድሮ የሜይ ዴይ በዓል ላይ በአዲስ አበባ ከተማ በአደባባይ ሊያነሳቸው የነበሩ ጥቄያዎች ሰልፍ እንዳያደርግ በመከልከሉ ጥያቄዎቹን ሳያቀርብ እንደቀረ ይታወሳል።

በኃላ ሊያነሳቸው የነበረውን ጥያቄዎችን በማካተት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በጻፈው ደብዳቤ፣ እሳቸውን ማነጋገር ለሠራተኞች ጥያቄዎች ምላሽ ለማግኘት እንደሚረዳ ገልጾ ነበር።

በወቅቱ በፃፈው ደብዳቤ በየጊዜው እያሻቀበ በመጣው የኑሮ ውድነት፣ የኢትዮጵያ ሠራተኞችና ቤተሰቦቻቸው መኖር የማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን ገልጾ ለዚህ ብቸኛው መፍትሄው ጠቅላይ ሚኒስትሩን  አግኝቶ ማነጋገር እንደሆነ ገልጿል።

ኢሠማኮ የሠራተኞች አንገብጋቢ የሚባሉ ጥያቄዎችን አስመልክቶ በተለያዩ መንገዶች ለሚመለከታቸው መንግሥታዊ አካላት ጥያቄ ቢያቀርብም፣ ምላሽ ሊያገኝ እንዳልቻለ በዛው ደብዳቤ ተመላክቷል።

ከዚህ ቀደም የሠራተኞች ጥያቄ የቀረበላቸው መንግሥታዊ አካላት ጥያቄውን ወደ ጎን የመግፋት አዝማሚያ እያሳዩ በመምጣታቸው፣ የኢሠማኮ አመራር " ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአነጋግሩን " ጥያቄ ለማቅረብ መገደዱን በወቅቱ በፃፈላቸው ደብዳቤው አስረድቶ ነበር።

#ማስታወሻ

ከዚህ ቀደም ኢሠማኮ ከሰራተኛው ጥያቄ ጋር በተያያዘ እንዳያደርግ በተከለከለው ሰልፍ ሊጠይቃቸው የነበሩ ጥያቄዎች ምን ነበሩ ?

1. በከፍተኛ የኑሮ ውድነት ሰራተኛው እየተቸገረ ነው፣ በተለይ ደግሞ ደሞዝ ተከፋዩ። መንግስት መፍትሄ ይስጠን። አብዛኛው ሰራተኛ በቀን አንዴም ለመብላት እየተቸገረ ነዉ።

2. የስራ ግብር ይቀነስልን።

3. የዛሬ አራት አመት ወጥቶ የነበረው የዝቅተኛ ደሞዝ ማስተካከያ አዋጅ እስካሁን ደንብ ሳይወጣለት ቆይቷል። ይህም ትኩረት ይሰጠው፣ በ600 ብር እየኖረ ያለ ሰው አለ፣ ኢንደስትሪ ፓርኮች ውስጥ ደሞዝ በአማካኝ ከ800 - 1,200 ብር ነው።

4. የአሰሪና ሰራተኛ ኤጀንሲዎች ከደምበኛቸው ከሚቀበሉት ክፍያ ለሰራተኛው 80 ፐርሰንት ከፍለዉ ቀሪውን 20 ፐርሰንት እንዲወስዱ በሚል የወጣዉ መመሪያ አለመከበር በኤጀንሲ በተቀጠሩ  ሰራተኞች ላይ ተመልካች ያጣ የጉልበት ብዝበዛ እየተካሄደ ነው፣ መንግስት ትኩረት ያርግበት የሚል ነው።

@tikvahethiopia
በተመጣጣኝ ዋጋ የቀረቡትን የሳፋሪኮም ቲክቶክ ጥቅሎችን በመጠቀም አዳዲስ ቪዲዮዎችን እየሰራን ለምንወዳቸው ሰዎች እንላክ፣ ዘና ፈታ እንበል!

አሁኑኑ ወደ *777# በመደወል ጥቅላችንን እንግዛ!

#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
" ይሄንን ሙሰኛ አስተዳደር በማስወገድ ሰላምን ለማስፈን ወስነናል " - የጋቦን ወታደሮች በጋቦን መፈንቅለ መንግሥት ተደረገ። ባሳለፍነው ቅዳሜ በአፍሪካዊቷ ሀገር ጋቦን ምርጫ ተደርጎ ነበር በዚህም ምርጫ ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎ ማሸናፋቸው ተነግሮ ነበር። ነገር ግን የሀገሪቱ ወታደሮችየተካሄደውን ምርጫ ውጤት በመሻር ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎን ከስልጣን ገልብጠው መንበሩን መቆጣጠራቸውን አሳውቀዋል። በአገሪቱ…
#Update

የጋቦን ወታደሮች አሊ ቦንጎን የቤት ውስጥ እስረኛ አድርገዋቸዋል።

መፈንቅለ መንግሥት የተደረገባቸው ፕሬዜዳንት አሊ ቦንጎ ካሉበት ቤት ውስጥ ሆነው " እርዱኝ " የሚል ይዘት ያለው መልዕክት ለወዳጆቻቸው በቪድዮ አሰራጭተዋል።

ምንጩ በትክክል ባልታወቀውና በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በተሰጨው ቪድዮ ፕሬዜዳንት አሊ ቦንጎ " በዓለም ዙሪያ ያሉ ወዳጆቻቸው ሁሉ ድምፅ እንዲያሱም " ተማፅነዋል።

" እዚህ ያሉ ሰዎች እኔን እና ቤተሰቦቼን አስረዋል ፤ ልጄ የሆነ ቦታነው ያለው፤ ባለቤቴ ሌላ ቦታ ነች ፤ እኔ ደግሞ አሁን ያለሁት በመኖሪያ ቤቴ ውስጥ ነው። ምንም እየተፈጠረ አይደለም ፤ ምን እየሆነ እንዳለም አላውቅም። " ብለዋል።

በመሆኑም በዓለም ዙሪያ ያሉ ወዳጆቻቸው ድምፅ እንዲያሰሙ ጥሪ አቅርበዋል።

ባሳለፍነው ቅዳሜ ዕለት በጋቦን ምርጫ ተደርጎ የነበር ሲሆን በምርጫው ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎ ማሸናፋቸው ተነግሮ ነበር።

ነገር ግን የሀገሪቱ ወታደሮች የተካሄደውን ምርጫ ውጤት በመሻር ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎን ከስልጣን ገልብጠው መንበሩን ተቆጣጥረዋል።

ወታደራዊ አመራሮች በሀገሪቱ ቴሌቪዥን ባስተላለፉት መልዕክት " የጋቦንን አስተዳደር ይዘናል " ብለዋል።

" ይሄንን ሙሰኛ አስተዳደር በማስወገድ ሰላምን ለማስፈን ወስነናል " ሲሉ ገልጸዋል።

" አስተዳደሩ ኃላፊነት የጎደለውና ወዴት እንደሚሄድ የማይታወቅ ስለሆነ የአገሪቱን ማኅበራዊ ኑሮ በማመሳቀል ወደ ቀውስ ከቶናል " ሲሉም ተናግረዋል።

ወታደሮቹ ፕሬዜዳንት አሊ ቦንጎ ያሸነፉበትን የምርጫውን ውጤት ሰርዘውታል።

በወታደራዊ አመራሮች ከሥልጣን ተወግዷል የተባለው የአሊ ቦንጎ ቤተሰብ ጋቦንን #ለ56_ዓመታት መርቷል ፤ ከነዚህ አመታት ውስጥ አሊ ቦንጎ ብቻቸው 14 ዓመት ሀገሪቱን መርተዋል።

@tikvahethiopia