TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በአሁኑም የወንዶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር ወርቅ ሊገኝ አልቻለም። ዛሬ በተካሄደው ውድድር ሶስተኛ ደረጃ ይዞ ያጠናቀቀው አትሌት ሰለሞን ባረጋ ለኢትዮጵያ ነሃስ አገኝቷል። ሀገራችን ኢትዮጵያ በወንዶች 10000ሜ ወርቅ ያመጣችው እኤአ በ2011 በዴጉ የዓለም ሻምፒዮና በአትሌት ኢብራሂም ጄይላን አማካኝነት ነበር። ከዛ በኃላ በወንዶች ዘርፍ ወርቅ ተገኝቶ አያውቅም። ከኢብራሂም ጄይላን…
" ህዝቡን ይቅርታ ነው የምንለው " - አትሌት ሰለሞን ባረጋ

አትሌት ሰለሞን ባረጋ ለቪኦኤ በሰጠው ቃል በውድድሩ ውጤት ብዙም ደስተኛ እንዳልሆኑ ገልጾ ፤ ስለተገኘው ውጤት " ይቅርታ " ጠይቋል።

" ብዙም ደስተኛ አይደለንም ፤ ወርቅ ነበር አስበን የመጣነው ፤ የአየሩ ሁኔታ ተፅእኖ አድርጎብናል ብዬ አስባለሁ፤ በአጠቃላይ ደስተኛ አይደለንም " ሲል ገልጿል።

የቡድን ስራ እና ታክቲክን በተመለከተም ፤ " የተሰጠን ሁለት ሁለት ዙር እንድንሄድ ነበር ከ15 ዙር በኃላ ያንን ልናደርግ ነበር ያሰብነው በሪሁ ትንሽ ቀደም ብሎ ወጣ ሩጫው ስለተያዘ ይመስለኛል ፤ ያን ከ15 ዙር በኃላ ብናደርግ በሪሁም የተሻለ ውጤት ያመጣ ነበር ፤ በሰራነው ልክ አይደለም ያገኘነው " ብሏል።

መጨረሻው ላይ ብር ሜዳሊያ ተገኘ ተብሎ ሲጠበቅ እንዴት ሶስተኛ ደረጃ ይዞ እንዳጠናቀቀ የተጠየቀው ሰለሞን " እኔ የጨረስኩ መስሎኝ ነበር ልጁን እያየሁት ነበር ስክሪን ላይ ጨርሼ የቆምኩ ነው የመሰለኝ እኔም በጣም ነው ያዘንኩት፤ ወርቁን ባጣ እንኳን ሁለተኛ የመሆን እድል ነበረኝ ፤ መጨረሻ ላይም የመደናቀፍ ነገርም በተጨማሪ ድካምም ነበር " ሲል አስረድቷል።

ሰለሞን ባረጋ ፤ " ለኢትዮጵያ ህዝብ ይቅርታ ነው የምለው ፤ የተሻለ ሰርተን ፊትለፊታችን ኦሎምፒክ አለ ለዛ ጥሩ እንዘጋጃለን " ብሏል።

የቡድን መሪ አትሌት ገዛኸኝ አበራ በበኩሉ ፤ አትሌቶች ከሚገባው በላይ የተዘጋጁበት እንደነበር ገልጿል።

" በእርግጠኝነት ወርቅም ብርም እናመጣለን ብለን አስበን ነበር የገባነው ፤ ነገር ግን ትልቁ ነገር እኛ ጋር ክረምት ነው እዚህ ደግሞ ኃይለኛ በጋ ነው ዛሬ ደግሞ በተለየ መልኩ ሙቀቱ 34 ዲግሪ የደረሰበት ነበር በዚህም በጠበቅነው ልክ ውጤት አልመጣም " ብሏል።

በውድድሩ ነሃስ እና ዲፕሎማ አግኝተናል ያለው ገዛኸኝ ፤ " ይሄ ውጤት ህዝቡም እንደተከታተለው በጣም መስዕዋትነት የተከፈለበት ፣ ስትራቴጂ የተነደፈበት አንዱን ውስጥ አስገብቶ እየተቀባበሉ ይሂዱ ባልነው መሰረት አድርገዋል ፤ እውነት ለመናገር ከአቅም በላይ ነበር፤ አትሌቶቻችን የቻሉትን ሁሉ አድርገዋል ደስ የሚል ውጤት ተመዝግቧል " ሲል አስረድቷል።

" የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይ ወርቅ እንጂ የለመደው ብር እና ነሃስ ቅር ይለዋል። የተወዳደሩበትን የአየር ሁኔታ ግንዛቤ ውስጥ ያስገባልን ፤ በአየር ሁኔታው ምክንያት ወርቅም ብርም አጥተናል፤ በቀረው ውድድር ጥሩ ውጤት እናመጣለን " ሲል ገልጿል።

አሰልጣኝ ም/ኮሚሽነር ሁሴን ሽቦ ደግሞ ለውድድሩ በቂ ዝግጅት ተደርጎ እንደነበር ነገር ግን በአየር ሁኔታው ምክንያት የሚፈለገው ውጤት እንዳልመጣ ገልጸዋል።

" አጋጣሚ የቀን ጉዳይ ሆኖ ወርቅ እና ብር ማምጣት አልቻልንም " ያሉት አሰልጣኝ ም/ኮሚሽነር ሁሴን ፤ ይሄ የሆነበት ምክንያት ውድድሩ የተደረገው በጠራራ ፀሀይ መሆኑና ሙቀቱም 34 ዲግሪ ስለነበር እንደሆነ ገልጸዋል።

የትላንቱ የሴቶች ውድድር ሙቀቱ 23 ዲግሪ እንዲሁም ምሽት 4 ሰዓት ገደማ በመደረጉ ትልቅ ውጤት መመዝገቡን ጠቁመዋል።

" ልጆቼ (የ10 ሺህ ሜትር ወንድ አትሌቶች) ማድረግ የሚገባቸውን አድርገዋል፤ ለኔ ጀግኖች ናቸው ፤ ነገም ሌላ ቀን ነው መልሰን የኢትዮጵያን ህዝብ እንደምንክስ እርግጠኛ ነኝ " ብለዋል።

ቃለመጠይቅ በቪኦኤ - ፅሁፍ በቲክቫህ ቤተሰብ የተዘጋጀ።

ፎቶ ፡ @tikvahethsport & VOA

@tikvahethiopia
#ኤክሶደስ_የፊዝዮቴራፒ_ልዩ_ክሊኒክ

በውቢቷ ባህርዳር አዲስ ቅርንጫፍ ከፍተናል ፤ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች፦
- ለአንገት፣ለትክሻ፣ለወገብ ህመም
- ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ   ችግር
- ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር
- ለፊት መጣመም
- ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል
- ለስፖርታዊ ጉዳቶች
- ከህፃናት የእድገት ውስንነት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ የእንቅስቃሴ ችግሮች
- በአጠቃላይ ከነርቭ፣ ከጡንቻ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች

አድራሻችን፦ ቁጥር 1_ አዲስ አበባ 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን ፤ ቁጥር 2_ ባህርዳር ቀበሌ 14 አልዋቅ ሆቴል አጠገብ ስልክ ቁጥር 0979099909 / 0911039377
በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://publielectoral.lat/ExodPhysioClinic
#SamComputer

በሚገርም ፍጥነት ፣ ቅለት እና ከ 10 ሰሀት በላይ የባትሪ ቆይታ ያላቸዉ  ዘመናዊ ላፕቶፖች አሉን ፦ https://publielectoral.lat/samcomptech

በፈለጉ ሰዓት እየመጡ መቀየር የሜችሉበትን እድል አመቻችተናል።

የቻናላችን ቤተሰብ በመሆን ተጨማሪ መረጃዎችን ያግኙ። https://publielectoral.lat/samcomptech

ለጌመሮች፣ ለዴዛይነሮች ፣ለተማርዎች፣ ለቤሮ ሰራተኞች በቅናሽ እና ከአንድ አመት ዋስትና ጋር እናቀርባለን።

@sww2844
ስልክ 0928442662/ 0940141114
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ይጎብኙ 🖼  . . .  #ይምረጡ

በ13 ቡድን የተከፈሉና 80 ወጣቶች #በሰላም ዙሪያ ያላቸውን ሀሳብ ክህሎታቸውን ተጠቅመው የገለጹበት የስዕል ኤግዚቢሽን ለተመልካቾች ክፍት ተደርጓል።

ጎብኚዎች የስዕል ሥራዎቹን፣ የተወዳዳሪዎቹን ሀሳብ እንዲሁም የወደዱትን ሥራ ላይ ድምጽ የሚሰጡበት የዲጂታል ኤግዚቢሽን ሲሆን በተመልካች እና በዳኞች በሚሰጥ ድምጽ አሸናፊዎች የሚለዩ ይሆናሉ።

ሪድም ዘ ጀኔሬሽን ባዘጋጀው በዚህ የስዕል ውድድር ፦
- አንደኛ ለሚወጣው ቡድን የ60,000 ብር፤
- ሁለተኛ ለሚወጣው ቡድን የ40,000 ብር፤
- ሦስተኛ የሚወጣው ቡድን ደግሞ የ25,000 ብር 
- በማኅበራዊ ሚዲያ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ላገኘው የሥዕል ሥራ የ10,000 ብር ሽልማት ያገኛሉ።

የሥዕል ስራውን ይጎብኙ፤ ለወደዱት ሥዕል ድምጽ ይስጡ 👉 https://redeem.tikvahethiopia.net/
#እንድታውቁት #ለጥንቃቄ

" በካፒታል ገበያ አዋጅ መሰረት የቀረበ የአክስዮን ሽያጭ " በሚል የሚቀርቡ ማስታወቂያዎች እውቅና  የላቸውም ተብሏል።

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ፤ አንዳንድ ኩባንያዎች " በካፒታል ገበያ አዋጅ መሰረት የቀረበ የአክስዮን ሽያጭ " በሚል የሚያስነግሩት ማስታወቅያ እውቅና የሌለው ነው ሲል አሳውቋል።

አንዳንድ ኩባንያዎች " በካፒታል ገበያ አዋጅ መሰረት የቀረበ የአስክሲዮን ሽያጭ " በሚል ማስታወቂያ እያስነገሩ አክሲዮን እየሸጡ እንደሆነ ደርሼባቸዋለሁ ያለው ባለስልጣን መ/ቤቱ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክሯል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የአክስዮን ሽያጮችን መመዝገብና ማጽደቅ እንዳልጀመረ ገልጾ አሁን ላይ የአክስዮን ምዝገባ የሚያደርግበትንና የደንበኛ ሳቢ መግለጫ የሚያጸድቅበትን የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ላይ እንደሚገኝ አስገንዝቧል።

አክስዮን ሻጭ ኩባንያዎችም የአክስዮን ሽያጭ ሂደቱ በባለስልጣኑ ታይቶ ባልጸደቀበትና ባልተመዘገገበበት ሁኔታ ሽያጩ በካፒታል ገበያ አዋጅ መሰረት የተዘጋጀ እንደሆነ በማስታወቅያ ማስነገር ህብረተሰቡን የሚያሳስት ነው ብሏል።

የዚህ አይነት አሳሳች የሆኑ የአክስዮን ሽያጭ ማስታወቅያዎችን በማንኛውም መንገድ በሚያስነግሩ ኩባንያዎች ላይ የባለስልጣን መ/ቤቱ በካፒታል ገበያ አዋጅ አንቀጽ 106 በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት መሰረት አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ የሚወስድ መሆኑንም አስጠንቅቋል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።)

Via @TikvahethMagazine
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥቆማ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተለያዩ የሥራ መደቦች ሰልጣኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። ✓ ሰልጣኝ አብራሪ/ፓይለት (Trainee Pilot) ✓ ሰልጣኝ የአውሮፕላን ቴክኒሽያን (Trainee Aircraft Maintenance Technician) ✓ ሰልጣኝ የአውሮፕላን ሜካኒክ (Trainee Aircraft Mechanic) ✓ ሰልጣኝ የበረራ አስተናጋጅ (Trainee Cabin Cors) …
#ማስታወሻ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተለያዩ የሥራ መደቦች ሰልጣኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ምዝገባው ዛሬ ይጀምራል።

የስልጠና መጠሪያዎች ፦
✓ ሰልጣኝ አብራሪ/ፓይለት (Trainee Pilot)
✓ ሰልጣኝ የአውሮፕላን ቴክኒሽያን
(Trainee Aircraft Maintenance Technician)
✓ ሰልጣኝ የአውሮፕላን ሜካኒክ (Trainee Aircraft Mechanic)
✓ ሰልጣኝ የበረራ አስተናጋጅ (Trainee Cabin Cors)
✓ ሰልጣኝ የመንገደኛ አገልግሎት ኢጀንት (Trainee Customer Service Agent) ናቸው።

አመልካቾች ለምዝገባ ፤ የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውንና ኮፒው፣ የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ካርድ፣ የልደት ካርድ፣ የታደሰ የቀበሌ የነዋሪነት ማረጋገጫ ካርድ እና አንድ ጉርድ ፎቶግራፍ ማሟላት አለባቸው።

አመልካቾች ከተዘረዘሩት የሥራ መደቦች ውስጥ ማመልከት የሚችሉት በአንዱ ብቻ ነው።

ምዝገባእ ከነሐሴ 15 ጀምሮ እስከ 19/2015 ዓ.ም ድረስ ብቻ ነው የሚቆየው።

የምዝገባ ቦታ፡-
- አዲስ አበባ በኦንላይን (አዲስ አበባ)
- አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (አዳማ)
- አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣ (አምቦ)
- አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ (አርባምንጭ)
- አሶሳ ዩኒቨርሲቲ፣ (አሶሳ)
- ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ (ባህርዳር)
- ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ፣ (ደ/ብርሃን)
- ደብረ ማርቆስኦኒቨርሲቲ፣ (ደ/ማርቆስ)
- ወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ (ደሴ)
- ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ፣ (ድሬዳዋ)
- ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ፣ (ፍቼ)
- ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ (ጋምቤላ)
- ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ (ጎንደር)
- ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ (ሀረር ካምፓስ ሀረር)
- ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ (ሀዋሳ)
- ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ (ጅግጅጋ)
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ (ጅማ)
- መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣ (መቐለ)
- ወለጋ ዩኒቨርሲቲ፣ (ነቀምቴ)
- ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ፣ (ሚዛን ቴፒ)
- ሮቤ ቲቺንግ ኮሌጅ፣ (ሮቤ)
- ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣ (ሰመራ)
- ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ (ወልቂጤ)

ዕድሜ ፣ ቁመት ፣ ክብደትና ሌሎች መረጀዎችን ከላይ በተያያዘው የተቋሙ ይፋዊ ማስታወቂያ ይመልከቱ።

More ፦ https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies?fbclid=IwAR1ZLHg_fw9VhghmXo-oOL9ykrsCmq3vcUISCzYl8QtRPPg5fnW4VW_Yfig

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
ቴሌግራም ላይ በኮፕ ቻፓግራም https://publielectoral.lat/ChapagramBot ገንዘብ መላላክ ተቻለ!
የታሰሩት የምክር ቤት አባላት የት ናቸው ?

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተያዙ የም/ቤት አባላት ታስረውበት ከነበረው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የማቆያ ቦታ እንደሌሉ እና ያሉበትን ቦታ ማወቅ እንዳልቻሉ ከጠበቆቻቸው አንዱ ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት በሰጡት ቃል ተናግረዋል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እንዲሁም በምክር ቤቱ የመንግሥት ወጪ፣ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ እና የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባሉ ዶ/ር ካሳ ተሻገር ዛሬ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ለቤተሰቦቻቸው ቢገለጽም፣ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀርተዋል።

በተጨማሪ እስካሁን ድረስ ቤተሰቦቻቸውም ይሁን ጠበቆቻቸው ሁለቱ ታሳሪዎች ያሉበትን ቦታ እንዳላወቁ ጠበቃ ሔኖክ አክሊሉ ተናግረዋል።

ጠበቃ ሔኖክ ምን አሉ ?

" ዛሬ ፍርድ ቤት እንደሚያቀርቧቸው ከቤተሰቦቻቸው ሰምተን ፍርድ ቤት ተገኝተን ነበር፤ አልቀረቡም።

በኋላ ላይ ስናጣራ ይገኙበት በነበረው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ውስጥ እንደሌሉ እና ለጊዜው ያላረገገጥነው ቦታ እንደተወሰዱ ሰምተናል።

ቤተሰቦቻቸውም ወደ እስር ቤቱ አስገብተውላቸው የነበሩ ንብረቶችን መውሰድ እንደሚችሉ ተነግሯቸዋል። በሐዘን እና በከፍተኛ የስሜት መሰበር ላይ ይገኛሉ።

አንዳንድ ቤተሰቦቻቸውም ሌላ እርምጃ ሊወሰድባቸው ይችላል በሚል የመረበሽ ስሜት ውስጥ ናቸው።

11፡00 ሰዓት ላይ ሊነጋጋ ሲል ነው የወጡት'፣ 'ወደ አዋሽ ተወስደዋል'  ከሚል ያልተረጋገጠ ወሬ በስተቀር የት እንዳሉ አናውቅም።

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተጠርጥረው በእስር ላይ ከነበሩ ሌሎች ግለሰቦች መካከል ዛሬ ፍርድ ቤት የቀረቡ ነበሩ ፤ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ የተነገራቸው በፖሊስ ነው።

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አሳሪው አካል ተጠርጣሪዎችን ፍርድ ቤት የማቅረብ ግዴታ የለበትም።

ሆኖም ፍርድ ቤት ቢያቀርባቸውም፣ ባያቀርባቸውም በእስር ላይ እስካሉ ድረስ በጠበቃ እንዲሁም በቤተሰባቸው የመጎብኘት መብት አላቸው።

ፍርድ ቤት የሚያቀርቧቸው ከሆነም በጠበቆች ተወክለው የሕግ ድጋፍ የማግኘት መብት ስላላቸው ያሰራቸው አካል ለጠበቆች የማሳወቅ ግዴታ አለበት።

እስካሁን ድረስ ከጠበቆቻቸው እንዳይገናኙ ተከልክለዋል። ያሉበትን ቦታ እና ሁኔታም ቤተሰቦቻቸውም ሆኑ ጠበቆቻቸው አናውቅም።

በሕግ ጥላ ሥር ያሉ ሰዎችን ያለምንም እውቅና ወደ ሌላ ቦታ ማዛወር ሕገ ወጥ ነው። በሕግ አግባብ ይዣቸዋለሁ የሚለው የመንግሥት ተቋም ያሉበትን ሁኔታ የማሳወቅ ግዴታውን እየተወጣ አይደለም።

የምክር ቤት አባላቱ ያለ መከሰስ መብታቸው ሳይነሳ መታሰራቸው ሕጋዊ አይደለም በማለት አካልን ነጻ የማውጣት ክስ መሥርተው ጉዳዩን እየተከታተሉ ነው። በቀጣይ እነዚህ ግለሰቦች የት እንዳሉ የማሳወቅ ግዴታ ያለበትን መርማሪ ቦርዱን እንጠይቃለን።

አንድን ሰው አስገድዶ መሰወርም ሆነ ያለበትን አለማሳወቅ ዓለም አቀፍ ወንጀልም ነው፣ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም ቢሆን የተከለከለ ተግባር ነው። ቤተሰቦቻቸውም ምን ዓይነት ሁኔታ ላይ እንዳሉ የማወቅ መብት አላቸው። "

Via BBC AMAHRIC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ሲዳማ

የሲዳማ ክልል መንግሥት ፤ " የተሰጣቸውን የመንግስትና የህዝብ አደራ ወደ ጎን በመተው በሙስናና ብልሹ አሰራር ላይ ተሳትፈዋል " ባላቸው አመራሮች ላይ የፖለቲካ ውሳኔ መተለለፉን አሳወቀ።

ክልሉ እኚሁ አመራሮች እንደየሥራቸው ከህግ ተጠያቂነት አያመልጡም ብሏል።

የሲዳማ ክልል ፕሬዝዳንት  አቶ ደስታ ሌዳሞ በሰጡት መግለጫ ፤ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ያልተወጡና በብልሹ አሰራር ላይ የተሳተፉ አመራሮችን በክልሉ ማዕከል ሀዋሳ ከተማ ሲደረግ በቆየው አካላዊ ግምገማ የፖለቲካ ውሳነ መተላለፉን ገልጸዋል።

" ማንም ባጠፋው ጥፋት ልክ ከህግ አግባብ እንዲጠየቅም ይደረጋል " ብለዋል።

ፕሬዜዳንቱ ባለፉት ለ10 ቀናት ሲካሄድ ከርሟል ባሉት የሲዳማ ክልል የፓርቲና የመንግሥት ሥራዎች አፈጻጸም ግምገማ ላይ በአፈፃፀም ላይ ዝቅተኛ ዉጤት ያስመዘገቡ ዘርፎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ግምገማ መደረጉን ገልጸዋል።

በብልሹ አሰራር ላይ የተሳተፉ አካላት ላይ ፖለትካዊ እርምጃ የተወሰደ መሆኑና የህግ ተጠያቂ እንደሚሆኑ አመልክተዋል።

አቶ ደስታ ፤ በሀዋሳ ከተማ ላይ ከፍተኛ ሌብነትና ብልሹ አሰራር በመታየቱ ያለውን ሁነታ በመሸሽ ስብሰባ ረግጠው ወጥቶ የሄዱ አመራሮች መኖራቸውን አንስተው በዚህ ብቻ የምተወው አይደለም ተጠያቂነት ይቀጥላል ብለዋል።

የትኞቹ አመራሮች ስብሰባ ረግጠው እንደወጡ በስም ጠቅሰው አልተናገሩም።

በተደረገ ማጣራት 97 ሰዎች በተለይ በመዳበሪያ ግብዓት ጋር ተያይዘው ከአራት ወረዳ ፦
- ከቀበሌ ልቀመምበር ጀምሮ፣
- ስራ አስኪያጅዎች፣
- የልማት ሰራተኞች፣
- የመጋዘን ጠባቂዎችና ሀላፊዎች ሁለት ወረዳ አስተዳደር ጨምሮ ለህዝብ የሚደርሰውን በማስተጎያጉል በዝርፊያ ጉዳይ ተሳታፊ መሆናቸው ተለይቶ ተጠያቂ እንዲሆኑ አድርገናል ብለዋል።

የክልሉ ፕሬዜዳንት የሁለት ወረዳ አስተዳደሮችን ጨምሮ ተይዘዋል ያሏቸውን 97 ሰዎች በስም አልገለፁም።

ፕሬዜዳንቱ ፤ " በግምገማ መድረኩ 25 ግለሰቦች በብልሹ አሰራር በህግ ቁጥጥር ስር ሆነዋል " ያሉ ሲሆን በተጨማሪም 10  አመራሮች ከሀላፊነት እንድነሱ ተደርገዋል ሲሉ አሳውቀዋል።

እነዚህ በቁጥጥር ስር ውለዋል የተባሉት አመራሮች ስም በይፋ አልተገለፀም ፤ በተጨማሪ ከኃላፊነት ተነሱ የተባሉትንም አመራሮች በግልፅ ስማቸውን አልተናገሩም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሰሞኑን ከክልሉ ግምገማ ጋር በተያያዘ የሀዋሳ ከንቲባ ረ/ፕሮፌሰት ፀጋዬ ቱኬ ከኃላፊነት መነሳታቸውንና በህግ እንዲጠየቁም ውሳኔ መተላለፉን ሌሎች በርካታ አመራሮች ላይ መሰል እርምጃ እንደሚወሰድ የክልሉን ብልፅግና ፓርቲ ዋቢ በማድረግ መዘገቡ አይዘነጋም።

የክልሉ ነዋሪዎችም በክልሉ ያለው እጅግ ህዝብን የሚያማርር ብልሹ አሰራር፣ ሙስናና ዘረፋ ስር የሰደደ መሆኑን በመግለፅ እያንዳንዱ አመራር ከታች እስከ ላይ እንዲጣራ መጠየቃቸውም ይታወሳል።

የሲዳማ ክልል በሙስና እና በብልሹ አሰራር በቁጥጥር ስር ዋሉ፣ ከኃላፊነታቸውም እንዲነሱ ተደረጉ ስላላቸው አመራሮች ይፋዊ ዝርዝር የሚያወጣ ከሆበ ተከታትለን እናሳውቃለን።

@tikvahethiopia
#ኣሸንዳ

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የ #ኣሸንዳ በዓል ሲከበር እና ሲዘከር የተጀመረውን ሰላምን በማጠናከር እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል።

ይህን ጥሪ ያቀረበው ዛሬ የኣሸንዳ በዓል ምክንያት በማድረግ በሰጠው መግለጫ ነው።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ፤ " ኣሸንዳ ፣ ማርያ ፣ ዓይኒ ዋሪ የነፃነት የእኩልነት ተምሳሌት ፤ የሴቶች የአብሮነትና የአንድነት ምልክት በመሆን ፤ የትግራይ ክብርና እሴቶች በቅብብሎሽ የትውልዶች ማስተሳሰርያ ገመድ እንዲሆኑ የራሱ አስተዋፅኦ አድርገዋል እያደረገም ይገኛል " ብሏል።

ባለፉት አመታት በነበረው ጦርነት ምክንያት የትግራይ ሴቶች እንደ አሸንዳ የመሰሉ የአደባባይ በአላት በደስታና ፌስታ ሊያከብሩት ይቅርና ፀሃይ ወጥታ ሳለች ጨልሞባቸው ደግሞ ለመተረትክ የሚከብድ ግፍ እንደደረሰባቸው ገልጿል።

" ይሁን እንጂ ግፉ እንዲቆም በፅናት በመታገላችሁ እና በማታገላችሁ ቢያንስ አሁን ለተደረሰው ደረጃ ለመድረስ መተኪያ የሌለው ተግባር ፈፅማቹሃል " ያለው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፤ " አስተዳደሩና ህዝቡ በናንተ ኩራት ይሰማዋል " ብሏል።

በዓሉ ሲከበር እና ሲዘከር የተጀመረው ሰላም በማጠናከር ፣ የህዝብ ጥያቄዎች እና ፍላጎቶች ፣ በሰላማዊና ፓለቲካዊ ትግል ለመመለስ በሚደረገው ትግል አሁንም እንደትናንት በፅናት እንደምትታገሉ በመታመመን ነው ብሏል።

" ያለው ሁኔታ ከባድ ነው " የሚለው አስተዳደሩ " ተፈናቃይ ወገኖች አጅግ በከፋ የኑሮ ሁኔታ ላይ ነው ያሉት ፣ በአማራና ኤርትራ ታጣቂ ሃይሎች ስር የሚገኝ ህዝባችን ማለቅያ የሌላቸው ግፎች እየተፈፀሙበት ነው ፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጥር ህዝባችን በረሃብ አለንጋ እየተገረፈ ይገኛል " ብሏል።

የትግራይ ሴቶች ይህን የመሰለ ከባድ ሁኔታ ተቋቁማችሁ የአሸንዳ ፣ ማሪያ ፣ ዓይኒ ዋሪ በዓል ለማክበር መቻላችሁ መንፈሳዊ ጥንካሬአችሁ ብርቱና ከፍተኛ መሆኑ ማሳያና ማረጋገጫ ነው ሲል ገልጿል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ጥያቄዎች በሰላማዊና ፓለቲካዊ ትግል እንዲመለሱ እጅግ እልህ አስጨራሽ ትግል እያካሄደ መሆኑን ገልጾ " አሁንም ተፈናቃይ ወገኖች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ፣ በትግራይ መሬት የሚገኙ የአማራና የኤርትራ ታጣቂዎች ለቀው እንዲወጡ ፣ የተቋረጠው ሰብአዊ አርዳታ እንዲጀምር ፣ ወንጀለኞች በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ያላሰለሰ ትግል አካሂዳለሁ " ብሏል።

@tikvahethiopia