TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የውጭ ሐዋላ የቁጠባ ሂሳብ
===========
ደንበኞች ከውጭ ሀገራት የተላከላቸውን ገንዘብ ወይም በባንኩ የሚመነዝሩትን የውጭ ሀገር ገንዘብ የሚያስቀምጡበት የቁጠባ ሂሳብ ነው፡፡

የቁጠባ ሂሳቡ በርካታ ጥቅሞች አሉት፡፡

• ከመደበኛው የቁጠባ ሂሳብ እጥፍ ወለድ ያስገኛል፤
• ደንበኞች ገንዘብ ከውጭ ሀገራት ሲላክላቸው ወይም በባንኩ ሲመነዝሩ የአየር ሰዓት ስጦታ ያገኛሉ፤
• የሂሳቡ ባለቤቶች ለውጭ ሀገር ጉዞ የውጭ ምንዛሪ ፍላጎታቸው ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፤
• ደንበኞች ከባንኩ ጋር ከሚሠሩ ድርጅቶች ለሚያገኙት አገልግሎት ወይም ለሚገዙት እቃ በፖስ ሲከፍሉ ቅናሽ ያገኛሉ፤
• ሌሎችንም በርካታ ጥቅሞች ያገኛሉ፡፡

ሂሳቡን በአቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ ይክፈቱ፤ ለበለጠ መረጃ ወደ 951 ይደውሉ!

ይቆጥቡ፤ የበለጠ ያግኙ!

(የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)
#Update

የተሻሻለው የ " ንግድ ሕግ ማስፈጸሚያ መመርያ " ሊወጣ ነው !

ከስልሣ ዓመታት በኋላ ተሻሽሎ የወጣውን አዲሱን የንግድ ሕግ ማስፈጸሚያ መመርያዎች ውስጥ እና የመጀመርያው የሆነው በዚህ ዓመት ፀድቆ ሥራ ላይ እንደሚውል ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

የንግድ ሕጉ ማስፈጸሚያ ይሆናል የተባለው ይህ የመጀመርያው መመርያ የ " አክሲዮን ማኅበራት " ን የሚመለከት ነው፡፡

በዚሁ መሠረት ፤ " የአክሲዮን ማኅበራት ክትትል፣ ድጋፍና ቁጥጥር መመሪያ " በሚል የተዘጋጀው ረቂቅ መመርያ ተዘጋጅቶ በመጠናቀቁ በዚህ በጀት ዓመት ይፀድጋል ተብሎ ይጠበቃል።

መመርያው ምን ይዟል ?

- በንግድ ሕጉ ላይ " የመተዳደሪያ ደንብ ያስፈልጋል ? አያስፈልግም ? " የሚለውን ጉዳይ ለማብራራትና በቀላሉ በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎችና በሁሉም ፈጻሚ ተቋማት ወጥ በሆነ መንገድ እየተተረጎመ እንዲፈጸም ለማስቻል በሚረዳ መልኩ በመመርያው እንዲቀመጥ ተደርጓል፡፡

- መመርያው አክሲዮን ማኅበራት ሲደራጁ ገንዘብ ከሕዝብ የሚሰበሰብበት መንገድ ላይ ምን መሆን እንዳለበት በግልፅ ያመላክታል። ኅብረተሰቡ እንዳይበዘበዝ እንዴት መተዳደር እንዳለበት በዝርዝር የተቀመጡ አንቀጾችን አካቷል፡፡

አደራጆች የምሥረታ ሒደት ለማካሄድ የሚያስከፍሉት አስተዳደራዊ ወጪ የሚዋጣው ገንዘብ ከአምስት በመቶ መብለጥ እንደሌለት በረቂቅ መመርያው ተመላክቷል፡፡

በምሥረታ ሒደት ከፈራሚዎች አስተዳደራዊ ወጪን ለመሸፈን ገንዘብ የተሰበሰበ እንደሆነ፣ ማኅበሩ ሲመሠረት የምሥረታ ወጪን ለማኅበሩ ማስተላለፍ የሚቻለው የተሰበሰበው አስተዳደራዊ ክፍያ የምሥረታ ወጪውን ለመሸፈን ያልበቃ መሆኑን የምሥረታ ኦዲተር ካረጋገጠ ብቻ ነው።

በምሥረታ ኦዲተር ሪፖርት መሠረት ለአስተዳደራዊ ወጪ ከተሰበሰበው ገንዘብ ላይ ጥቅም ላይ ያልዋለ ቀሪ ገንዘብ ያለ እንደሆነ ማኅበሩ ሲመሠረት ፣ ለማኅበሩ ገቢ መደረግ ይኖርበታል። ይህም ቀድሞ ለአገልግሎት ተብሎ የተሰበሰበን ገንዘብ ከብክነት ያድናል።

- አደራጆች በአክሲዮን ምሥረታ ወቅት ከፈራሚዎች ሚሰበሰበውን መዋጮ በባንክ በዝግ ሒሳብ ሲያስቀምጡ በገበያው ላይ ካለው የወለድ ምጣኔ አንፃር ተመጣጣኝ የሆነ ወለድ እንዲያፈራ የማድረግ ኃላፊነት አለባቸው።

- የማኅበሩ ምሥረታ በስኬት የተጠናቀቀ እንደሆነ ዋና ገንዘቡና ያስገኘው ወለድ ለማኅበሩ ገቢ መደረግ አለበት።

- የግል አክሲዮን ማኅበር ሚመሠረተው በመሥራቾች እንደሚሆን ይደነግጋል። መሥራቾች በባለአክሲዮንነት ከሚያገኙት መብት ውጪ በመሥራችነታቸው ምክንያት የሚከፈላቸው የአገልግሎት ክፍያ አይኖርም።

- በአክሲዮኖች ላይ #ከአንድ_መቶ_ብር (100) ያነሰ ዋጋ የተጻፈባቸው አክሲዮኖች ያላቸው ማኅበራት፣ ይህ መመርያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሁለት ዓመት ውስጥ ቢያንስ ወደ አንድ መቶ ብር በማሳደግ መመሥረቻ ጽሑፋቸውን አሻሽለው ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።

- የአክሲዮን ኩባንያዎች የሚያደራጁ ሰዎች ያለባቸው ኃላፊነት ምንድነው የሚለውም በግልጽ የተቀመጠ ሲሆን በአዲሱ የንግድ ሕግ የአክሲዮን ኩባንያዎች የኤሌክትሮኒክስ ስብሰባ ማድረግ የሚችሉ በመሆኑ፣ ይህንን ለማስፈጸም ዝርዝር ጉዳዩ በዚህ መመርያ ተገልጿል።

" የቦርድ ስብሰባ " የሚደረግበት የኤሌትሮኒክ ዘዴ የተሰብሳቢዎችን ማንነት ለመለየት የሚያስችል ፤ የውይይቱን የድምጽ ቅጂ በትክክል መያዝ የሚችል መተግበሪያ ያለውና ፤ ሚስጢራዊነትንም መጠበቅ የሚችል መሆን አለበት።

በመመስረቻ ጽሑፍ ተቃራኒ ድንጋጌ ከሌለ በስተቀር እያንዳንዱ የቦርድ አባል በዳይሬክተሮች ቦርድ ስብሰባ ላይ በአካል የመገኘት መብት ያለው ሲሆን፣ የቦርድ ስብሰባን በኤሌትሮኒክ ዘዴ ለመሳተፍ ዳይሬክተሩ ጥያቄ ካላቀረበ በቀር፣ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊያስገድድ ወይም በአካል የመሳተፍ መብቱን ሊገድብ እንደማይችች ተቀምጧል፡፡

- ከመመርያው መውጣት በኋላ ብዙ አክሲዮን ያላቸው ኩባንያዎች በቀላሉ ስብሰባቸውን እንዲያካሂዱ ዕድል ይሰጣቸዋል።

- የአክሲዮን ዝውውሮችን በተመለከተ በዚህ መመርያ ግልጽ ድንጋጌ ያስቀመጠ ሲሆን፣ በተለይ የግለሰብ አክሲዮንን ለማስተላለፍ #የትዳር_አጋር_ስምምነት ቅድመ ሁኔታ መሆኑን ያስቀምጣል፡፡

"በግል የአክሲዮን ማኅበር" ውስጥ በግለሰብ የተያዘ አክሲዮንን ፦
- በሽያጭ ፣
- በስጦታ ፣
- በመያዣ
- በሌላ በማንኛውም መንግድ ለማስተላለፍ በሕግ ወይም ደግሞ በመመሥረቻ ጽሑፍ ከተገለጹት ቅድመ ሁኔታዎች በተጨማሪ አስተላላፊው በአስገዳጅነት ያገባ ከሆነ የትዳር አጋሩ ውል ለማዋዋል እና ሰነድን ለመመዝገብ ' ሥልጣን ባለው አካል ፊት ቀርቦ ' ስምምነቱን መግለጽ አለበት።

ያላገባ ከሆነ / ከሆነች አግባብ ካለው የአስተዳደር መሥሪያ ቤት ተገቢውን ማስረጃ ማቅረብ ይኖርበታል በሚል መመርያው ይደነግጋል፡፡

- ሁሉም የአክሲዮን ማኅበራት ይህ መመርያ ተፈጻሚ ከሆነበት ቀን ጀምሮ በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ድረገጽ ማበልጸግና በድረገጹ ላይ በሕጉ መሠረት ተገቢነት ያላቸውን መረጃዎች ማስቀመጥ አለባቸው። ይህንን ድንጋጌ የማይፈጽም የአክሲዮን ማኅበር የንግድ ፈቃዱ ሊታገድ እንደሚችልም ተደንግጓል፡፡

- አክሲዮን ለመሸጥ ስለሚወጡ #ማስታወቂያዎች በመመርያው ላይ ተቀምጧል።

ይህም ፤ " በማንኛውም በሕዝብ ማኅበር በምሥረታ ሒደት አክሲዮን ለመሸጥ በሚተላለፍ ማስታወቂያ ስለ ታሳበው የንግድ ሥራ አዋጭነት በጠቅላላው ከመግለጽ በስተቀር ስለሚያስገኘው የትርፍ መጠን በምን ያህል ጊዜ ለኢንቨስትምንት የተከፈለው ገንዘብ እንደሚመለስ ወይም ሌሎች በተጨባጭ ሊረጋገጡ የማይችሉ መረጃዎችን መስጠት አይቻልም " በሚል ተጠቅሷል፡፡

በማንኛውም #ዋና_ገንዘብ በማሳደግ ሒደት በግል ማኅበር ወይም በሕዝብ ማኅበር፣ ለሕዝብ አክሲዮን ለመሸጥ የሚደረግ ማስታወቂያ ማኅበሩ አስቀድሞ ያገኘውን ትርፍ የሚገልጽ ከሆነ፣ ያለፉትን ሦስት ተከታታይ ዓመታት የትርፍ ውጤት መግለጽ ግዴታ አለበት፡፡

ነገር ግን ማኅበሩ #ለወደፊት የሚኖረውን አትራፊነት በቁጥር ወይ በመጠን መግለጽ አይቻልም።

ሚኒስቴሩ (ንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር) ወይም አግባብ ያለው ሌላ የመንግሥት መሥሪያ ቤት አሳሳች ናቸው ብሎ ከወሰነ፣ አክሲዮን ለመሸጥ ለሕዝብ የሚተላለፉ ማስታወቂያዎች እንዲቋረጡ ለማዘዝ ይችላል።

.
.
.

መመርያው በአጠቃላይ ከአክሲዮን ምሥረታ ጀምሮ እስከሚፈርስበት ጊዜ ድረስ #ዝርዝር የአሠራር ጉዳዮችን በመተንተን የቀረበ ነው።

በአዲሱ የንግድ ሕግ መመርያ የማውጣት ሥልጣን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ነው፡፡

መመርያን ያዘጋጀው በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ሲሆን በተለይ #የሕዝብን_ገንዘብ ተቀብለው የሚያስተዳድሩ የአክሲዮን ማኅበራት ላይ መጠነኛና ቁጥጥር ለመዘርጋት የሚያስችል ነው፡፡

(ሪፖርተር ጋዜጣ የረቂቅ መመርያው ዝግጅት ተሳታፊ የሕግ ባለሙያ አቶ ፈቃዱ ጴጥሮስን ዋቢ በማድረግ ያወጣው)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ኢትዮጵያ

ልክ እንደ 2015 ዓ/ም በጀት ሁሉ በ2016 ዓ/ም በጀት ዓመት የአዳዲስ የመንግሥት ሰራተኞች ቅጥር እንደማይፈፀም ተነግሯል። ይህም ከምክር ቤት አባላት በኩል ጥያቄ አስነስቷል።

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ባለፈው ሳምንት ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ተወስኖ ወደ ፓርላማ የተላከውን የ2016 ዓ/ም የ801.65 ቢሊዮን ብር በጀት ረቂቅ ላይ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር።

በማብራሪያቸው ላይ የተያዘው በጀት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ1.9 በመቶ ብልጫ እንዳለው ገልጸው በጀቱ ሀገራዊ አቅምን የዋጋ ግሽበትን መከላከል ላይ ታሳቢ አድርጎ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።

በጀቱ ለሚፈለጉ የተለያዩ የልማት ስራዎች በቂ ባለመሆኑ አዳዲስ ፕሮጀክቶች እንደማይጀመሩ እንዲሁም አዲስ የመንግስት ሰራተኞች ቅጥር እንደማይፈፅም አሳውቀዋል።

አቶ አህመድ ሽዴ ፦

" የ2016 መደበኛ በጀት በየመስሪያ ቤቱ ያለውን አዲሱን አደረጃጀት ታሳቢ በማድረግ የበጀት አጠቃቀም በቁጠባ እና በውጤታማነት ላይ ያተኮረ እንደሚሆን እንዲሁም አዳዲስ የሰራተኞች ቅጥር እንደማይኖር ታሳቢ በማድረግ የተዘጋጀ መሆኑን መገንዘብ ተገቢ ነው "

የምክር ቤት አባላት ምን ጠየቁ ?

የምክር ቤት አባላት ለሚኒስትሩ ከጠየቁት ጥያቄዎች አንዱ ዘንድሮም የአዲስ ሰራተኞች ቅጥር አለመኖሩን በተመለከተ ነው።

ጥያቄ ከጠየቁ የምክር ቤት አባል መካከል አንድ አባል " አንድ የመንግስት ኃላፊነት ለዜጎቹ ስራ መፍጠር ነው ያ ማለት የመንግስት ስራ ብቻ መፍጠር አይደለም በተለያየ መንገድ ግን ስራ መፍጠር የመንግስት ኃላፊነት ነው አንዱ ክፍል ምናልባት መንግስት በራሱ ሊቀጥር ይችላል ይሄንን ዘግተን በዘለቄታዊነት ልንዘልቅ አንችልም። ስለዚህ እነዚህ ነገሮች መታሰብ ስላለባቸው ከገቢ አሰባሰባችን እና ከወጪ አጠቃቀማችን ጋር ውጤታማ የሆነ ነገር መሄድ አለብን " ብለዋል።

ሌላ አንድ የምክር ቤት አባል ደግሞ ፤ " በየዓመቱ አምናም እንደሚታወቀው በየመስሪያ ቤቱ አዳዲስ ሰራተኞችን መቅጠር አይቻልም በሚል ነበር በጀት የፀደቀው ዘንድሮም የቀረበው በየመስሪያ ቤቱ አዳዲስ ሰራተኞች መቅጠር እንደማይቻል ታሳቢ ተደርጎ ነው። እንደዚህ በየዓመቱ እያፀደቅን የምንሄድ ከሆነ አንደኛ የተማሩ ምሁራን ኃይሎችን ለስደት ልንዳርጋቸው እንችላለን ፤ ሁለተኛ የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ ሊቀጥል ይችላል እንደሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ፤ ሶስተኛ ምስኪን አርሶ አደሮች ብዙ መስእዋትነት ከፍለው ነው ልጆቻቸውን አስተምረው የሚያወጡት (ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት) " ስለዚህ የነዚህ ዕጣ ፋንታቸው ምንድነው ሲሉ ጠይቀዋል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ፤ " ስራ መፈጠር አለበት " የሚለው የሚያስማማ ሃሳብ ቢሆንም መንግሥት ግን በዋነኝነት የስራ ዕድል መፍጠሪያ አይደለም ብለዋል።

" መንግሥት ስራ መፍጠር አለበት በተቻለ መጠን ግን በዋነኛነት የግሉ ሴክተርን ኢንቨስትመንት በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ይኖርብናል " ሲሉ ለቀረበው ጥያቄ መልሰዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ምን አለ ?

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የተሰራጨው ዜና " ግነት የበዛበት ነው " አለ።

ዩኒቨርሲቲው በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ አውጥቷል።

በመግለጫው ፤ ከዩኒቨሲቲው እውቅና ውጪ ባልተፈቀደ ሁኔታ በቀን 03/10/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጠውን የ2015 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) " አንፈተንም  "በሚል  በዋናው ግቢ በዉስን ተማሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ተሞክሮ ነበር ብሏል።

" የተደረገውን ሙከራ ተከትሎ በጥቂት የማህበራዊ ሚዲያዎች የፀጥታ ችግር እንዳለና መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ ላይ መስተጓጎል እንዳለ በማስመሰል ሀሰተኛ መረጃዎች እየተሰራጨ  እንዳለ ለመገንዘብ ችለናል " ብሏል።

" በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጨው ዜና ግነት የበዛበት " ነው ያለው ዩኒቨርሲቲው " የተፈጠረውን መጠነኛ ያለመግባባት ለመፍታት የዩኒቨርሲቲው ደህንነት ከፌዴራል ፖሊስ፣ ከሀዲያ ዞን ፖሊስ፣ ከሌሞ ወረዳ ፖሊስ እንዲሁም ከሌሎች ከሚመለከታቸው የፀጥታ ኃይሎች ጋር በቅንጅት በመስራት በአስተማማኝ ሁኔታ ሠላማዊ የሆነ የመማር ማስተማር ሥራ ማስቀጠል ተችሉዋል " ብሏል።

" በዩኒቨርሲቲው የተማሪ ረብሻ፣ የንብረት ዉድመት እንዲሁም የጎላ የፀጥታ ችግር በሌለበት አንዳንድ ኃላፊነት የጎደላቸው ማህበራዊ ሚዲያዎች የሰላም አምባሳደር የሆነውን የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ስም ሆነ ብሎ ለማጠልሸት ጥረት ማድረጋቸው ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እናስገነዝባለን " ሲል ገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው ፤ ለተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች ባስተላለፈው መልዕክት በነበረው መጠነኛ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ በተማሪዎች ላይ " ምንም ዓይነት ጉዳት " ያለመድረሱንና ዩኒቨርሲቲው ወደተለመደው መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ መመለሱን አሳውቋል።

ተቋሙ ባወጣው መግለጫ ላይ በቪድዮ እና በፎቶ ስለተያዙት ማስረጃዎች ምንም ያለው ነገር የለም።

የተቋሙን ወቅታዊ መግለጫ የተመለከቱ ተማሪዎች መግለጫው ፍፁም የነበረውን ሁኔታ በትክልል የማይገልፅ ፣ የሆነውን ነገር ሁሉ ኢትዮጵያውያን በቪድዮ ያዩት መሆኑን አስረድተው ከልክ ያለፈ እርምጃ / ድብደባ በተማሪዎች ላይ የፈፀሙ አካላት በህግ ሊጠየቁ እንደሚገባ አመልክተዋል።

More : @tikvahUniversity

@tikvahethiopia
" ደም ስትለግሱ ሳትጎዱ ዉድ የሆነውን የማታውቁትን የሰው ልጅ መታደጋችሁን  እወቁት" - ዶ/ር ሰኢድ አንዳርጌ

" ደም ለጋሾች ደስ ይበላችሁ !

ትላንትና ምሽት አንዲት የስምንት ወር ነፍሰጡር እናት እጅግ ከፍተኛ እና ባልተጠበቀ ሁኔታ ደም መፍሰስ ስላጋጠማት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልግ ቀዶ ሕክምና ከአራት ሰዓት በላይ በአከናወነው በዚሁ ቅፅበት ደግሞ የ8 ሰዉ ደም ማግኘት በመቻላችን ሰበብ #እናትም #ልጅም መትረፍ  ችለዋል።

ከስራ ባልደረቦቼ  በተጨማሪ ይህን አጋጣሚ ሳያዩ ደምን የሚያክል ዉድ ስጦታ ለሚሰጡ ሁሉ በያሉበት ምስጋናዬ  ይድረሳችሁ።

ደም ስትለግሱ ሳትጎዱ ውድ የሆነውን የማታውቁት የሰው ልጅ መታደጋችሁን  እወቁት፤ ለዚህም ታላቅ ክብር ይገባችዋል ! "

(ዶክተር ሰኢድ አንዳርጌ)

Via ALI AMIN

@tikvahethiopia
በኤክሶደስ የፊዚዮቴራፒ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች ፦
- ለአንገት፣ ለትክሻ፣ ለወገብ ህመም ፣ ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ   ችግር
- ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር፣ ለፊት መጣመም፣ ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል
- ለስፖርታዊ ጉዳቶች፣ ከህፃናት የእድገት ውስንነት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ የእንቅስቃሴ ችግሮች
- በአጠቃላይ ከነርቭ፣ ከጡንቻ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች መፍትሄ ያግኙ ይዳኑ!

የስራ ሰዓት ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከጠዋቱ 2:30 እስከ #ምሽት 1:00 ሰዓት፤ አድራሻችን 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን። ስልክ ቁጥር 0979099909/ 0911039377
  √በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://publielectoral.lat/ExodPhysioClinic
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 20 ሺህ ሰራተኞችን ሊቀጥር ነው ?

ከሀሰተኛ መረጃ ተጠንቀቁ !

በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በማህበራዊ ትስስር ገፁ 20 ሺህ #ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን መቅጠር እንደሚፈልግ አስታወቀ ፤ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን የሚቀጥረው ትግራይ ፣ አፋር፣ ሶማሌ ክልሎችን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች የቴሌኮም አገልግሎቱን ለማስፋፋት በማቀድ ነው ፤ የስራ ቅጥሩ ዲግሪ አይጠይቅም 10ኛ እና 12ኛ ክፍል ያጠናቀቁ ማመልከት ይችላሉ " እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ፍፁም #ሀሰተኛ መሆኑን ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ገልጾልናል።

ከጥዋት አንስቶ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የተሰራጨውን የ20 ሺህ ሰራተኞች ቅጥር መረጃ በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለሚመለከተው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ክፍል " በየትኛው የማህበራዊ ትስስር ገፃችሁ ላይ ነው ይህ ያሳወቃችሁት ? መረጃው እውነት ከሆነስ በየትኛው መንገድ ነው ማመልከት የሚቻለው ? " ስንል ጥያቄ ያቀረብን ሲሆን መረጃው #ሀሰተኛ ነው የሚል ምላሽ ተሰጥቶናል።

" እኛ 20 ሺህ ሰራተኞች ለመቅጠር በየትኛውም የማህበራዊ ትስስር ገፃችን ላይ ጥሪ አላቀረብንም ፤ መሰል ሀሰተኛ መረጃዎች የሚሰራጩት ሆን ተብሎ ተመሳስለው በተከፈቱ #ሀሰተኛ_ገፆች ነው " ሲል የሚመለከተው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ክፍል ገልጾልናል።

በመሆኑም " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 20 ሺህ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን ሊቀጥር ነው " በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው።

@tikvahethiopia
" የመውጫ ፈተና የሥርዓተ ትምህርቱ አካል ሆኖ ይቀጥላል " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ከዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና እና ከ12 ክፍል ብሔራዊ ፈተና ጋር ሳይጋጭ እንደሚከናወን አሳውቋል።

በ208 የትምህርት ፕሮግራሞች የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና መዘጋጀቱንም ገልጿል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ኤባ ሚጀና ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በሰጡት ቃል ፤ " የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምረቃ፣ ከመውጫና ከ12 ክፍል ብሔራዊ ፈተና ጋር በማይጋጭ መልኩ እንዲከናወን የሚረዳ ዕቅድ ተዘጋጅቷል " ብለዋል።

የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ ፤ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ደግሞ ከሐምሌ 17 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ቀናት እንደሚሰጥ ዶ/ር ኤባ አስታውሰዋል።

ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎቻቸውን የምረቃ መርሃግብር ከመውጫ ፈተና በኋላ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲዎቹ ምርጫ የ12ኛ ክፍል ፈተና ሲጠናቀቅ ማካሄድ እንደሚችሉ ገልጸዋል።

ዶ/ር ኤባ ፤ በዘንድሮው ዓመት 180 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና እንደሚወስዱ ገልጸው ለ208 የመመረቂያ ፕሮግራሞች የሚውሉ የፈተና ዓይነቶች መዘጋጀታቸውን አሳውቀዋል።

" የመውጫ ፈተና የሥርዓተ ትምህርቱ አካል ሆኖ ይቀጥላል " ያሉት ዶክተር ኤባ፤ በተቀመጠው መመሪያ መሠረት ተፈትነው 50 በመቶና በላይ ያመጡ ተማሪዎች እንደሚያልፉ አስረድተዋል፡፡

የመውጫ ፈተናው ሙሉ በሙሉ በኦንላይን የሚሰጥ በመሆኑ የተማሪዎች ስም ዝርዝር ተልኮ ወደ ዳታ ማዕከል መግባቱን አመላክተዋል።

ለተማሪዎች ለፈተና የሚሆን ልዩ የመታወቂያ ቁጥር ይሰጣቸዋል ያሉት ዶክተር ኤባ፤ በተሰጣቸው ቁጥር መሠረት በኦንላይን መፈተን እንዲችሉ የሚረዳ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

በማዕከል ደረጃ የተዘጋጀውን የፈተና ሥርዓት ለመሞከር እንደ አገር ሞዴል ፈተና እንደሚሰጥ አስታውቀው፤ በዚህም ጉድለቶች ካሉ ለማስተካከልና ተገቢውን ጥንቃቄ ለማድረግ ዝግጅት መደረጉን ጠቁመዋል።

ለፈተናው መሳካት ከኢትዮ ቴሌኮም፣ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የተደራጀ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

ለመውጫ ፈተናው የሚውሉ ኮምፒዩተሮች፣ የኢንተርኔት አገልግሎትና ጄኔሬተሮች ዝግጅት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

@tikvahethiopia
ልዩ የቴሌብር ጥቅል እስከ 55% ከሚደርስ ቅናሽ ጋር!

በዘርፈ-ብዙ አገልግሎቱ ደንበኞቹን እፎይ ያሰኘው ቴሌብር በልዩ ቅናሽና ስጦታዎች ማንበሽበሹንም ቀጥሏል።

ከመደበኛ ጥቅሎቻችን እስከ 55% ቅናሽ የተደረገባቸውን ወርሃዊ የድምጽ እና ዳታ ጥቅሎች ከጥሪ ማሳመሪያ ስጦታ ጋር በቴሌብር ሱፐርአፕ በልዩነት ስናቀርብ ደስታችን ወደር የለሽ ነው!

በየትኛውም ቦታ በእጅዎ ላይ ያለ የቅርብ አለኝታ
ቴሌብር የዘመን ስጦታ!
#Hawassa

በሀዋሳ ከተማ በሚገኝ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው ሜላት መሀመድ ትላንት ሰኔ 5/2015 ዓ.ም ቀትር ላይ በሁለት ተሽከርካሪ በመጡ ግለሰቦች 'መጠለፏን' ቤተሰቧቿ ተናግረዋል።

የ14 ዓመት ከ 8 ወር ታዳጊዋ ሜላት ከትምህርት ቤት ወደ ወደ መኖሪያ ቤቷ በመመለስ ላይ እያለች በሀዋሳ ከተማ ሞኖፖል ተብሎ በሚጠራው አከባቢ " ቤት ልትደርስ ጥቂት ሜትሮች ሲቀራት " በሃይል ታግታ መወሰዷን የሜላት የቅርብ ዘመዶች ገልጸዋል።

የሜላት የአክስት ልጅ የሆነችው ትዕግስት ብስራት ስለሁኔታው ምን ትላለች ?

" እኔና እናቴ ለቅሶ ላይ ስለነበርን [ለሜላት] ቁልፉን አስቀምጠንላት ነበር. . .[ቁልፉን] ከስራ ቦታዬ ወደመኖሪያ ቤት ይዛ እየሄደች ነበር።

ከዚያ እንደጥበቃ የሚሰራልኝ ልጅ በግምት 6 ሰዓት ተኩል ይሆናል ደውሎ ‘ሁለት ዳማስ [መኪና] ቆሞ ነበር፣ እየጮኸች ልጅሽን አፍነው አስገቧት’ አለኝ " ብላለች።

የሜላት እናት ከዓመታት በፊት በማለፋቸው ምክንያት ከሶስት ዓመቷ ጀምሮ ከሷ ቤተሰቦች ጋር ነው ያደገችው።

ነገሩ ከተሰማበት ጊዜ ጀምሮ ከሌሎች ቤተሰቦቿ ጋር በመሆን ፍለጋ ላይ መሆናቸውን ትዕግስት ገልጻለች።

ትዕግስት ሀዋሳ ከተማ ውስጥ አንስተኛ ምግብ ቤት ያላት ሲሆን ፤ የአጋቾቹን ማንነ ለማጣራት ባደረገችው ሙከራ እሷ ጋር ምግብ የሚበሉ ልጆች መሆናቸውን አመልክታለች።

" ለሊቱን ሙሉ እየፈለኳቸው ነው። ወደ ቤት አልገባሁም " ስትልም ገልጻለች።

ትዕግስት " ጠላፊውን " እንድምታወቀውና ጥሩ ግንኙነት እንደነበራቸው የገለጸች ሲሆን ይህ የምግብ ቤት ደንበኛዋ የተለየ ምንም ነገር እንደማያሳይ ተናግራለች።

" ከሜላትና ከልጆቼ ጋር ያለኝ ነገር ያውቃሉ። " ያለችው ትዕግስት " ሲናገሯቸው እንኳን በጣም ነው የምቆጣው። አይደፍሩም. . . ሙሉ ቤተሰብ ለቅሶ ላይ ስለነበር አለመኖራችንን አይቶ ነው [ይህንን ያደረገው]” ብላለች።

ሌላኛው የሜላት የአክስት ልጅ እንዳልካቸው ብስራት ስለጉዳዩ ምን አለ ?

" ከዚህ በፊት ሜላት ‘ያስቸግረኛል’ ብላ የተናገረችው ሰው የለም

እኛ ግራ ገብቶኖናል። ማንም ፍንጭ የሚሰጠን አጣን።

በእንባ ጭምር ቤተሰቡ ጭንቅ ላይ ነው። " ብሏል።

እንዳልካቸውና ትዕግስት ከፖሊስ ጋር በመሆን ሜላትን እያፈላለጉ እንደሚገኙ ገልጸው " ጥሩ ትብብር እየተደረገልን ይገኛል " ብለዋል።

ሜላትን በኃይል ወደ ተሽከርካሪ እንድትገባ ሲደረግ የአካቢው ሰው ሊታደጋት መሞከሩንም ቤተሰቦቿ አመላክተዋል።

" [ሜላት] ስትጮህ ይዟት የጠፋውን መኪና የፊትለፊቱን መስታወት የአከባቢው ሰው ሰብሮበታል። ከዛ በኋላ እየበረረ አመለጠ " ሲል እንደላካቸው ገልጿል።

በሌላ በኩል ትዕግስት ፤ የጠለፏትን ሰዎች ማንነት ካጣራች በኃላ መረጃ ለመጠየቅ ወደ የቤተሰቧቻቸው ቤት ቢሄዱም ሊተባበሯት እንዳልቻሉ ገልጻለች።

ሜላት ከመጠለፏ አስቀድሞ ከእሷ ጋር የምትማርና ‘የጠላፊው’ ዘመድ ሜላትን አናግራታለች። " እሷም ቤቷ ሄደን አላገኘናትም። ሸሽተዋል " ስትል ትዕግስት ተናግራለች።

ትዕግስት " መርዳት የሚችል አካል እንዲረዳኝ በጣም እፈልጋለሁ ' ስትል በእንባ ተማጽናለች።

ሜላት የተወለደችው ያቤሎ ከተማ ሲሆን ከእናቷ ህልፈት በኃላ ወደ ጉጂ ዞን ዋደራ ሄዳ ዓመታትን ቆይታለች።

ከአራት ዓመታት በፊት ወደ ሀዋሳ ከተማ ከቤተሰቦቿ ጋር በማቅናት ትምህርቷን እየተከታተለች ነው።

ከጥቂት ቀናት በፊት በዛው በሀዋሳ ከተማ ፀጋ በላቸው የተባለች የባንክ ሰራተኛ በአንድ ግለሰብ ተጠልፋ ከቀናት በኃላ ነፃ መሆኗ የሚዘነጋ አይደለም።

Via BBC AMHARIC

@tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#አቢሲንያ_ባንክ

ስልካችሁን በመጠቀም የአፖሎ አካውንት ለመክፈት የሚጠበቅባችሁ ቀላል መመሪያዎች!

መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo

#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
#Safaricom

ቀናችንን በSamsung Galaxy S23 Ultra ፈካ እናድርግ። ጥራት ያለው ፕሮሰሰሩ እና ፍንክች የማይልው ባትሪው ስራችንን በነፃነት እንድንሰራ ይረዳናል።

ጥራትን ከተመጣጣኝ ዋጋ ጋር አጣምረው የያዙትን የGalaxy S23 ስልኮች ከጀሞ፣ መስቀል ፍላወር፣ እና ጋራድ በሚገኙ የሳፋሪኮም ሱቆች እንሸምት።

#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether