TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#አሳትፉን
#ህጉ_የኔም_ነው_ይመለከተኛል

ኤቲኤሞች ለአካል ጉዳተኞችተደራሽ ናቸው ?

በአዲስ አበባ ውስጥ የምናገኛቸው አብዛኛዎቹ ኤቲኤምዎች ለአካል ጉዳተኞች ሙሉ በሙሉ ተደራሽ አለመሆናቸውን ሲቪል ሶሳይቲ ሪሶርስ ሴንተር ከCSSP2 ጋር በመተባበር አዘጋጅቶ በላከልን መልዕክት አሳይቷል።

ይህ ሁኔታ እንዲስተካከልና ሁሉም አካል ጉዳተኞች የህዝብ አገልግሎት የማግኘት ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው እንዲከበር ጠይቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሳምሶን ተክለሚካኤል እስካሁን ያለበት አልታወቀም፤ የት ነው ያለው ? ኢትዮጵያ የኬንያ ባለስልጣናትን ናይሮቢ ውስጥ መሀል መንገድ ላይ ስለታገተው ሳምሶን ተክለሚካኤል ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠይቃለች። በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር መለስ አለም ኬንያ ለሚገኝ የሃገር ውስጥ ሚዲያ በሰጡት ቃለ ምልልስ የኬንያ የህግ አስከባሪ አካላት በንግድ ስራ ላይ የተሰማራው ሳምሶን ተክለሚካኤል የት እንዳለ እንዲሁም በምን…
ሳምሶን የት ነው ያለው ?

በኬንያ መዲና ናይሮቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከወራት በፊት ታፍኖ የተወሰደው አቶ ሳምሶን ተክለሚካኤል የት እንዳለ እስካሁን ድረስ አለመታወቁን በመቃወም ሰልፍ አካሂደዋል።

ከሦስት ወራት በፊት ከናይሮቢ ጎዳና ላይ ባልታወቁ ሰዎች ከመኪናው እንዲወርድ ተደርጎ ከተወሰደ በኋላ እስካሁን ያለበት ያልታወቀው በንግድ ሥራ የሚተዳደረው አቶ ሳምሶን ጉዳይ ያሳሰባቸው ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ እንዲሁም ሌሎችም በናይኖቢ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት ናቸው ሰልፉን ያካሄዱት።

- ፍትሕ ለሳሚ !
- ሳሚ የት ነው ?
- ባለቤቴ ሳሚ የት ነው ?
- ጓደኛዬ ሳሚ የት ነው ?
- አጎቴ ሳሚ የት ነው ? የሚሉና ሌሎች መፈክሮችን ይዘው ኢትዮጵያውያኑ ሰልፍ ወጥተዋል።

የአቶ ሳምሶን ባለቤት ወ/ሮ ሚለን ሃለፎምን ጨምሮ የሃይማኖት አባቶች እና ወጣቶች በናይሮቢ አደባባይ ወጥተው ድምጻቸውን አሰምተዋል።

አቶ ሳምሶን በዚህ ዓመት ኅዳር መጀመሪያ ላይ ነበር በናይሮቢ ከተማ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ከመንገድ ላይ በኃይል ከተወሰደ በኋላ እስካሁን ድረስ ያለበት አልታወቀም።

ከሳምንታት በፊት ለኬንያ ሚዲያዎች ቃላቸውን የሰጡት በኬንያ የኢትዬያጵያ አምባሳደር መለስ አለም ፥ "የኬንያ መንግሥት እና የሕግ አካላት ሳምሶን የት እንዳለ እንዲያሳውቁን ጠይቀናል" ማለታቸው አይዘነጋም።

አቶ ሳምሶን ታፍኖ የተወሰደ ሰሞን የኬንያ ፖሊስ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለው እንደሆነ የገለጸ ቢሆንም፤ እስከ ዛሬ ግን ከኬንያ ፖሊስ ሆነ ከኬንያ መንግሥት በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም።

መረጃው የቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፕ/ር መሰፍን አርአያ ወልደተንሳይ ማናቸው ? የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮችን ሹመት ዛሬ ፀድቋል። የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ሆነው የተመረጡት ደግሞ ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ናቸው። • በሕክምና የዶክተሬት ዲግሪ ( MD) ፣ ከፓቭሎቭ ዩኒቨርሲቲ ሩሲያ፤ • በሳይኮቴራፒ ፍልስፍና የፒኤች ዲ ዲግሪ (PhD)፣ ከኦማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሰዊድን፤ • ስፔሻላይዝድ ድፕሎማ፤ በሳይኮሎጂካል ሜድስን እና ሳይካትሪ፣…
#አገራዊ_ምክክር

የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰብሳቢ ፕ/ር መስፍን አርአያ ከሹመቱ በኃላይ የተናገሩት ፦

" አስራ አንዳችንም ገና በሚገባ መተዋወቅ አለብን። እዚህ ውስጥ በተለይ አስሩ በጣም ብዙ ልምድ ያላቸው ናቸው። ደስ ብሎኛል ሴቶች አሉ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ፤ ወጣቶች አሉ።

በእርግጥ በተወካይነቱ ላይ ኢትዮጵያ ከ86 ብሄረሰቦች በላይ ነው ያሏት ስለዚህ 86ቱንም ወደዚህ ማምጣት ሳይሆን 86ቱና ከዚያ በላይ ያሉትን ወደ መግባባት መድረኩ ማምጣት ስለሆነ ትልቁ ስራ እንግዲህ በጋራ ስንገናኝ ስራ ስንከፋፈል የምናየው እና የምናውቀው ይሆናል።

ይሄ ኃላፊነት ከሌሎች ኃላፊነት ለየት ሚያደርገው የመግባባት አጀንዳዎች በጣም ብዙ ናቸው። ስለዚህ እነዚህ አጀንዳዎች ነቅሶ ወደ ጠረጴዛ በማምጣት አጀንዳዎቹ ላይ በትክክል በጋራ፣ በኢትዮጵያዊነት ላይ ፣ መብትን በማስከበር ላይ ፣ ባህልን ፣ ቋንቋን እና ሌሎችንም የሚመለከታቸውን ነገሮች በማስከበር ላይ ትልቅ ብሄር ትንሽ ብሄር ሳንል ሁላችንም በጋራ መስራቱ ላይ ብዙ ነገር ስለሚጠበቅብን ይሄ ትልቅ ኃላፊነት ነው ብዬ አስባለሁ፤ ደግሞም ነው ይሄ ነው ከበድ ያደርገዋል ብዬ የማስበው።

በጋራ ከሰራን ወደ መፍትሄ የማንደርስበት ምክንያት የለም። ሁሉም ነገር ሰልችቶናል ሰላም ማጣቱና መጎዳቱ እና መብት በማስከበር ሂደቱ ላይ የደረሰብን ብዙ ጉዳዮች ስላሉ እነኛን በጋራ እንፈታለን ብዬ አስባለሁ።

ሀገርን በመገንባቱ ሂደት፣ ህዝብን ወደመግባባቱ በማምጣት ሂደት ሚዲያዎች ትልቅ ቦታ አላቸው ፣ፖለቲካ ፓርቲዎች ፣የሃይማኖት አባቶች ፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ አባገዳዎች እና ሌሎችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ወጣቶች በተለይ በዚህ ስራ ላይ ከጎናችን ሆነው ይረዱናል ያግዙናል ወደ መፍትሄ ያመጡናል ብዬ አስባለሁ "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#አገራዊ_ምክክር

የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክትል ሰብሳቢ ወ/ሮ ሂሩት ገብረስላሴ ከሹመቱ በኃላ የተናገሩት ፦

"... ሌላ ዓለም ላይ ሰርቻለሁ። ሌላ ዓለም ላይ ያለኝን እውቀት ፣ ያለኝን ልምድ ተጠቅሜ ነው ኢትዮጵያ ላይ ሲሆን ሀገሬ ስለሆነ እንደ ሚሽንም ነው ከፍተኛ ስሜትም አለው። ከእኔም ከሁላችም ከፍተኛ ቁርጠኝነት ይኖራል ብዬ አስባለሁ።

ትልቅ ኃላፊነት ነው የተሰጠን ፤ ትልቅ ክብርም ነው ግን የተሰጠን ለዛ ብቁ ሆነን ለመገኘት ማድረግ ያለብንን ጥረት እናደርጋለን።

... የዚህች ሀገር ችግር የህዝቦች ችግር አይደለም የኤሊቱ ፣ ተምሪያለሁ ባይ ፣ አንድ ቦታ ደርሻለሁ ባይ የኤሊቱ ችግር ስለሆነ ለኤሊቱ ነው ጥሪ ማቅረብ ያለብን ኤሊቱ ላይ ነው በጣም መሰራት ያለበት ህዝቡ መኖር ነው የሚፈልገው፤ በሰላም መኖር ነው የሚፈልገውና የህዝቡ ችግር አይደለም። ስለዚህ ማሸነፍ የሚኖርብን ኤሊቱን ነው።

እዚህች ሀገር ላይ ኤሊት መሆን ማለት እኮ Privileged የሆነ status አለህ ማለት ነው። የተሻለ ትምህርት አግኝተሃል ፣ የተሻለ ኑሮ ኖረሃል ፣ የተሻለ Experience አለህ ተብሎ የሚገመት የማህበረሰብ ክፍል አስቸጋሪ ሆኖ ሊቀጥል አይገባውም ፤ አይችልም።

እኔ ይመስለኛል እግዚአብሔር ከረዳን አንድ ቦታ እንደርሳለን። "

@tikvahethiopia
#ITena

• በስትሮክ፣ በአደጋ፣ እና በሌሎች በሽታዎች ምክንያት ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል ለተፈጠረ አለመንቀሳቀስ (Paralysis)
• እድሜ በመግፋት ለሚፈጠሩ ጉድለቶች እንደ አልዛይመርስ፤ ዲሜንሻ
• ከተለያዩ ቀዶ ጥገናዎች ለማገገም
• በሙሉ (Coma) ወይም በከፊል የንቃተ ህሊና መቀነስ ላላቸው ታካሚዎች እንክብካቤ
• ለካንሰር እና ተከታታይ የህክምና ክትትል ለሚያስፈልጋቸው ታካሚዎች

👉በ 0901222233 ይደውሉልን

Telegram FB IG LinkedIn Twitter 🌍

🏥 አድራሻችን ጀሞ ከ ጀሞ ሞል 200m ገባ ብሎ፡፡
#አሁን

የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ አስቸኳይ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከህዝብ ተወካዮች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ማብራሪያ ለመስጠት በምክር ቤቱ ተገኝተዋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት የምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ይገኛሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አሁን የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ አስቸኳይ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከህዝብ ተወካዮች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ማብራሪያ ለመስጠት በምክር ቤቱ ተገኝተዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ይገኛሉ። @tikvahethiopia
የምክር ቤት አባላት ምን ጠየቁ ?

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ ከፓርላማ አባላት በርካታ ጥያቄ ተነስቶላቸው በአሁን ሰዓት ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።

ከፓርላማ አባላት መካከል አቶ ክርስቲያን ታደለ መንግስት በእነ አቶ ስብሃት ነጋ ላይ የተነሰረተውን ክስ ያቋረጠው ከህግ አግባብና ከህገመንግስቱ በሚጣረስ መልኩ ስለሆነ ማስተካከያ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

አቶ ክርስቲያን ፥ " መንግስት መጀመሪያ ዜናውን ሲነግረን በ #ምህረት ነው የተፈቱት ያለ ሲሆን እነ አቶ ስብሃት ነጋን የመሰለ ሰው በሰው ልጆች ላይ ግፍ ፈፅሟል፣ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈፅሟል ተብሎ የተጠረጠረን ወይም የከሰሰውን ሰው በምህረት መልቀቅ እንደማይችል ሲረዳ በፍትህ ሚኒስትሩ በኩል ይቅርታም ምህረት አይደለም የክስ ማቋረጥ ውሳኔ ነው በሚል ማብራሪያ ሰጥቷል " ሲሉ አስታውሰዋል።

አክለውም ፥ " መንግስት የሰራውን ሀገር ያወቀው ፀሀይ የሞቀውን ስህተት ለማረም እድል አለው " ያሉት አቶ ክርስቲያን " ይህን እድል ለመስጠት ነው ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩን የምጠይቀው። እነዚህ ሰዎች እኔ በምወክለው የአማራ ህዝብ ተደራጅተው ያደረሱበት ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት የህሊና መጉሳቆል ለመዘርዘር በቂ ጊዜ የለኝም " ብለዋል።

የፍትህ ሚኒስቴር ያሳለፈው የክስ ማቋረጥ ውሳኔ ከህግ የሚጣረስ በመሆኑ ውሳኔውን ውድቅ በማድረግ ክሱ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መንግስትና በም/ቤቱ በአሸባሪነት በተፈረጀው ህወሓት መካከል ድርድር እየተደረገ እንደሚገኝ በተለያየ ሚዲያ እየተሰማ መሆኑን ያነሱት የፓርላማው አባል፦

• ምን ያህል እውነት ነው ?
• እውነት ከሆነ ማን ከማን ጋር ነው እየተደራደረ ያለው ?
• በማን አደራዳሪነት ?
• ህወሓት አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀ ስለሆነ መንግስት የሚያደርገው ድርድር ከህጋዊነቱ እንዴት ይታያል ?
• የድርድሩ ማህበራዊ፣ ህጋዊ እና ሞራላዊ ቅቡልነት የሚረጋገጠው ድርድሩ ግልፅ እና አሳታፊ ሲሆን ነው ድርድሩ በኢትዮጵያ ህዝብ በተለይ ቀጥተኛ ተጎጂ በሆኑት የአፋር እና የአማራ ህዝብ የሚያሳድረው ስሜቱ ተጢኗል ወይ ? ሲሉ ጠይቀዋል።

እንዲሁም በጦርነቱ የደረሰው ውድመት በአማራ እና አፋር ለማካካስ የፀደቀው የድጎማ በጀት አንድ ተቋምን ጠግኖ ወደነበረበት የሚመልስ ባለመሆኑ ባለበጀት ክልሎች እና የፌዴራል መንግስት በልዩ ሁኔታ ሀገር ለማዳን ሲሉ ከፍተኛና ቀውስ ላስተናገዱ ክልሎች ለምን በበቂ ሆኔታ በጀት መደገፍ አልቻሉም ? ሲሉ ጠይቀዋል።

አቶ ክርስቲያን ታደለ ፤ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር እና ከምዕራብውያን ሀገራት ጋር ያላት ወቅታዊ የዴፕሎማሲ ግኝኑነት ምን ይመስላል ? ሀገራዊ የሰህንበት ሁኔታው ባልተቀለበሰበት ሁኔታና በተለያዩ ምክንያቶች በቂ ወታደራዊ አመራሮች ባልተፈሩበት ሁኔታ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮኖችን በአምባሳደርነት መሾሙ ያለው ተገቢነት ላይ ማብራሪያ ይሰጥ ሲሉ ጠይቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አሁን የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ አስቸኳይ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከህዝብ ተወካዮች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ማብራሪያ ለመስጠት በምክር ቤቱ ተገኝተዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ይገኛሉ። @tikvahethiopia
የምክር ቤት አባላት ምን ጠየቁ ?

ኡስታዝ ከሚል ሸምሱ ፦

" እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ ሀገራችን ከሌሎች ሀገራት ያላትን ዲፕሎማሲ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለማሻሻል እና ዲፕሎማሲውም የሀገራትን የጋራ ጥቅም ያስጠበቀ እንዲሁም የሀገሩን ክብር እና ሉዓላዊነት በጠበቀ መልኩ እንዲጎለበት ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ።

ሆኖም ግን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የሀገራትን የፖለቲካ አስተላለፍ በመከተል ወዳጅ የነበሩ ሀገራት ጎራቸውን የቀየሩበት ሁኔታዎች ይስተዋላሉ።

እንደማያሳያም በርካታ ዜጎች በተለያዩ ሀገራት ለእስር ተዳርገው ለአላስፈላጊ እንግልት እና ስቃይ እንዲሁም ለሞት እየተዳረጉ ይገኛሉ ለምሳሌ በሳዑዲ አረቢያ ፣ እንዲሁም በኤምሬት አንዳንድ ቦታዎች ያለው ችግር መጥቀስ ይቻላል።

እንዘህ ዜጎች ከእስር ተፈተው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ በመንግስት ጥረት እየተደረገ ቢሆንም በምብ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ቢገለፅልን "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አሁን የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ አስቸኳይ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከህዝብ ተወካዮች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ማብራሪያ ለመስጠት በምክር ቤቱ ተገኝተዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ይገኛሉ። @tikvahethiopia
" ነዳጁንም ቦቴውንም ውረሱት ብለናል " - ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እየሰጡት ባለው ማብራሪያ " ነዳጅ ከኢትዮጵያ አውጥተው ወደ ጎረቤት ሃገር ወስደው የሚሸጡ ዘራፊዎች አሉ " ብለዋል።

" ከራሳችን አልፍ ጎረቤት ሀገር ልንደጉም አንችልም " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " የሁሉም ክልል ሚሊሻዎች ልዩ ሃይሎች ፤ፖሊሶች ከሃገር የሚወጣ ነዳጅ ካገኛችሁ ነዳጁንም ቦቴውንም ውረሱ ብለናል " ሲሉ ለምክር ቤቱ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia