TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
OPA🔝

#የኦሮሚያ_ሀኪሞች_ማህበር በዛሬው ዕለት የኦሮሚያ ጤና ቢሮ፣ የአትዮጵያ ሐኪሞች ማህበር ተወካይ እና አክቲቪስት #ጀዋር_መሃመድ በተገኘበት በኢሊሊ ሆቴል የመጀመሪያ ጉባኤ እና የምስረታ ክብረበዓል ተከናውኗል።

Oromiyaa Physcians Association(OPA) inaugration ceremony held @ Elili International Hotel!

©ዶክተር ሲሳይ ከOPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Fake News Alert‼️

"66ቱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ወታደራዊ እርምጃ (ቀጥታ #ተገደሉ)" በሚል በሶሻል ሚዲያው የተሰራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወንጀለኞች መሸሸጊያ የላቸውም...

#በኢትዮጵያ_ወንጀል_ሰርተው በውጭ አገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የትም ሆነ የት መሸሸጊያ ያላቸውን እጃቸውንም #አንጠልጥዬ ለኢትዮጵያ መንግስት አስረክባለሁ ሲል አለም አቀፍ የፖሊስ ተቋም ኢንተርፖል ማስተማመኛ ሰጠ፡፡

ትናንትና አዲስ አበባ የመጡት የኢንተርፖል ዋና ሀላፊ ዶ/ር ጀርጋን ስቶክ ከፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል እንዳሻው ጣሰው ጋር ከተነጋገሩ በኋላ ነው ወሬው የተሰማው፡፡

ከንግግሩ በኋላ መግለጫ የሰጡት ኮሚሽነር ጀነራል #እንዳሻው_ጣሰው በኢትዮጵያ ወንጀል ሰርተው በውጭ አገር የሚገኙ ኢትዮጵያንን ኢንተርፖል ለኢትዮጵያ አሳልፎ እንደሚሰጥ ማስተማመኛ ሰጥቷል ብለዋል፡፡

ኮሚሽነር ጀነራሉ በሰብአዊ ፍጡር ላይ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት የፈፀሙና ሀገር የዘረፉ ሰዎች ግማሾቹ በሀገር ውስጥ ግማሾቹ ደግሞ ባህር አቋርጠው በውጭ አገር እንደሚኖሩ ታውቋል ብለዋል፡፡

ይህንን ወንጀል ፈፃሚዎቹ የትም ይደበቁ የትም ይኑሩ ኢንተርፖል እጃቸውን አንጠልጥሎ ለኢትዮጵያ መንግስት እንደሚያስረክብ ሀላፊው አረጋግጠውልናል ሲሉ መናገራቸውን ከመንግስታዊ ምንጮች ስምቻለሁ ብሎ ሸገር ዘግቧል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ከሰሞኑ ባስተላለፉት መልዕክት በወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች ማንም ይሁን ማን ከየትኛውም ብሔር ገብተው ይደበቁ፣ የትኛውም ወገን ይጩህላቸው በወንጀል እስከተጠረጠሩ ድረስ ካሉበት አድነን ለህግ እናቀርባቸዋልን ማለታቸው
ይታወሳል፡፡

ምንጭ፦ ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፕሬዘዳንት ግርማ የቀብር ስነ ስርዓት...

የቀድሞ ፕሬዚዳንት #ግርማ_ወልደጊዮርጊስ የቀብር ስነ ስርዓት የፊታችን ረቡዕ እንደሚፈፀም ተገለፀ።

የቀብር ስነ ስርዓቱም የፊታችን ረቡዕ ታህሳስ 10 2011 ዓ.ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ከቀኑ 10 ሰዓት ከ30 ላይ የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት እንደሚፈፀመም ተነግሯል።

ከዛ ቀደም ብሎም ህዝቡ በተገኘበት ለአስከሬናቸው አሸኛኘት ስነ ስርዓት ይደረጋል የተባለ ሲሆን፥ ጊዜው እና ቦታው ወደፊት እንደሚገለፅም ታውቋል።

በአዋጅ ቁጥር 653/2009 አንቀፅ 11 ላይ በተደነገገው መሰረትም በመላው ሀገሪቱ የ1 ቀን ብሄራዊ ሀዘን የሚታወጅ ይሆናል። የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፊታችን ማክሰኞ ታህሳስ 9 2011 ዓ.ም በሚያደርገው ስብሰባው ብሄራዊ የሀዘን ቀኑን እንደሚያውጅ ይጠበቃል።

ይህንን ተከትሎም የሀገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ በመላው ሀገሪቱ እንዲሁም በውጭ ሀገራት በሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎች ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ የሚደረግ ይሆናል።

የቀብር ስነ ስርዓታቸውም ለክብራቸው እና ለሀገራቸው ላበረከቱት አስተዋጽኦ ሚመጥን መልኩ እንደሚከናወንም ተገልጿል።

ይህንን ለመፈፀምም 11 ዓባላት ያሉት ብሄራዊ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን፥ የኮሚቴው አባላትም ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር፣ ከፌደራል ፖሊስ እና ከሀገር መከላከያ የተውጣጡ መሆናቸውም ታውቋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቡሌ ሆራ🔝

ቡሌ ሆራ ከተማ ሰሞኑን ከነበረው አለመረጋጋት ተላቃ ወደሰላማዊ እና ወደቀደመው መደበኛ እንቅስቃሴዋ ተመልሳለች። የንግድ ተቋማት ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ ነው። የትራንስፖርት እንቅስቃሴም ወደነበረበት ተመልሷል።

ፎቶ፦ ገሜ(ቡሌ ሆራ TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወንጀል ነክ መረጃ‼️

#መሀመድ_ሁሴን 1ኛና #ዳኜ_አሰፋ 2ኛ ተከሳሽ በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ክልል ልዩ ቦታው አፍሪካ ካፌ ውስጥ ህዳር 10 ቀን 2008 ዓ.ም ከረፋዱ 05፡30 ሰዓት ሲሆን በ1996 ዓ.ምየወጣውን የወንጀል ህግ አንቀፅ 32/1/ሀ እና 692/1/ ስር የተመለከተውን በመተላለፍ በፈፀሙት አታላይነት ወንጀል ተከሰው ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

የክስ ዝርዝሩ እንደሚያስረዳው ተከሳሾች ለጊዜው ባልተያዘው ግብረ አበራቸው አማካኝነት የግል ተበዳይ አቶ ታዬ ጀቤሳን አግኝተው 1ኛ ተከሳሽ እኔ ጅንአድ ውስጥ ነው የምሰራው 400 ፍሬ ባለ25 ሊትር ዘይት ትወስዳለህ አብርንም እንሰራለን ህጋዊ ደረሰኝም እሰጥሀለሁ ክፈልና ትወስዳለህ በማለት ሲለው2ኛ ተከሳሽ ደግሞ ዘይቱ መኪና ላይ እስኪጫን ለመተማመኛ እንዲሆንህ ቼክ እሰጥሃለሁ በማለት 200,000 ሺህ ብር ከተቀበሉ በኋላ የተሰወሩ በመሆኑ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈፀሙት የአታላይነት ወንጀል በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አራዳ ምድብ ጽ/ቤት ዐቃቤ ህግ ክስ የመሰረተባቸው ሲሆን 2ኛ ተከሳሽ ደግሞ ደረቅ ቼክ ፅፎና ፈርሞ በመስጠቱ
ሁለተኛ ክስ መስርቶበታል፡፡

ዐቃቤ ህግ የተከሳሾችን ጥፋተኝነት ያስረዱልኛል ያላቸውን ሁለት የሰው ምስክሮችን በማቅረብ አሰምቶ የተከራከረ ሲሆን ተከሳሾችም ባለመከላከላቸው ጥፋተኛ ተብለዋል፡፡

በመጨረሻም የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት ህዳር 27 ቀን 2011 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሾችን ያርማል በማለት 1ኛ ተከሳሽ በ2 ዓመት ከ6 ወር እስራት እና 2000 ብር 2ኛ ተከሳሽ ደግሞ በ2ዓመት ከ3 ወር እስራትና በ2000 ብር እንዲቀጡ ወስኖባቸዋል፡፡

ምንጭ፦ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የሚኒስትሮች ም/ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 58ኛ መደበኛ ስብሰባ በሶስት ረቂቅ ደንቦችና በስድስት የስምምነት ረቂቅ አዋጆች ላይ ተወያይቶ እንደሚከተለዉ ውሳኔ አሳልፏል።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አብዱል በቁጥጥር ስር ዋለ‼️

ባለፉት ወራት በቤኒሻንጉል ክልል እየተንቀሳቀሰ ማሕበራዊ ሰላም #ሲያደፈርስ የነበረውና ከጸረ ሰላም ሃይሎች ጋር ተቀናጅቶ በርካታ ወንጀሎችን በመፈጸም የተጠረጠረው ግለሰብ ከትላንት በስቲያ #በፌደራል_ፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን ጉለሌ ፖስት ከምጮቼ ሠማሁ ብሎ ዘግቧል።

#አብዱል_ወሃብ የተባለውና የቤኒሻንጉል ነፃ አውጪ ግንባር ሊቀ መንበር የነበረው ይህ ግለሰብ ቀደም ሲል በኤርትራ ይንቀሳቀስ የነበረውን ግንባር ሲመራ ቢቆይም፤ በአገሪቱ በተፈጠረው ለውጥ ወደክልሉ ከተመለሰ በኋላ ለውጡን ለመቀልበስ ከሚፈልጉ ሃይሎች ጋር
በመቀናጀት በበርካታ ወንጀሎች ሲፈለግ መቆየቱን የጉለሌ ፖስት ምንጮች ጠቁመዋል።

አብዱል ወሃብ በትናንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር ከመዋሉ በፊት በፌደራልፖሊስ አባላቱ ላይ ተኩስ ከፍቶ ለማምለጥ ጥረት ያደረገ ሲሆን በተደረገው የተኩስ ልውውጥ ተመቶ በቁጥጥር ስር ውሏል ተብሏል።

እንደጉለሌ ፖስት ምንጮች ገለጻ ተጠርጣሪው #ለማምለጥ ባደረገው ጥረት የክልሉ ልዩ ሃይል የተወሰኑ አባላት ስልታዊ ድጋፍ ሲያደርጉለት እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ...

በያዝነው ዓመት መጀመርያ ላይ በሕዝቡ ላይ የሚደርሰውን እንግልት ለመከላከል ቄሮዎችን አደራጅታችኋል በሚል በቤኒሻንጉል ክልል እስር ቤት የሚገኙት ዘጠኝ አዛውንቶች እስካሁን ፍርድ ቤት ያለመቅረባቸውን የመረጃ ምንጮቼ ገልጸዋል ሲል ጉለሌ ፖስት ዘግቧል። በተለይ ኦቦ #ተስፋዬ_አመኑ እና ኦቦ #መላኩ_ቀጄላ የተባሉት አዛውንቶች በሕመም ላይ የሚገኙ መሆኑ በጣም አሳሳቢ እንደሆነባቸውና መንግስት አስቸኳይ እልባት እንዲሰጣቸው እኒሁ ወገኖች ጥሪ አቅርበዋል።

ምንጭ፦ ጉለሌ ፖስት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለድሬዳዋ ነዋሪዎች፦

"የተከበራችሁ የድሬዳዋ ነዋሪዎች ታህሳስ
7-2011 ዓም ክቡር ጠ/ሚ #አቢይ_አህመድ በተገኙበት ታቅዶ የነበረው የኢንዱስትሪ ፓርክ ምርቃት ላልተወሰነ ጊዜ #የተራዘመ መሆኑን እንገልፃለን!"

©የከተማው ከንቲባ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በእጃችን ላይ ስላለው #ሰላም ዘላቂነት በአንድነት ተጠንክረን ልንሰራ ይገባል ሲሉ የሰላም አምባሳደር እናቶች ገለጹ። የሰላም አምባሳደሮቹ የልኡካን ቡድን አባላት ዛሬ #ጋምቤላ ሲገቡ በክልሉ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወንጀል ነክ መረጃ‼️

ወንጀሉ የተፈጸመው በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ክልል ልዩ ቦታው ጉርድ ሾላ አካባቢ ሚያዚያ 9 ቀን 2007 ዓ.ም ሲሆን ተከሳሽ በ1996 ዓ.ም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 669/2/መ/ ስር የተመለከተውን ድንጋጌ በመተላለፍ ነው ክስ የተመሰረተበት፡፡

የክሱ ዝርዝር ሁኔታ እንደሚያስረዳው ተከሳሽ በቀለ በራሶ ኩኑሬ በ1ኛ ክስ ለጊዜው ካልተያዙ ግበረ-አበሮች ጋር በመሆን በላዮን ሴኩሪቲ ሰርቪስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር አማካኝነት ከህዳር 2007 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 9/2007 ዓ.ም በጥበቃ ሰራተኛነት #የጁፒተር_የንግድ_ስራ_ድርጅት ውስጥ ተቀጥሮ በሚሰራበት ወቅት የድርጅቱን የዕቃ ማስቀመጫ መጋዘን በተለያየ ጊዜ በተመሳሳይ ቁልፍ እየከፈቱ የተለያየ ሞደል ያላቸው ብዛታቸው 211 የሆኑ ኮር አይ3 ቶሸባ ላፕቶፖችን ጠቅላላ የዋጋ ግምታቸው 2,838,400 (ሁለት ሚሊዮን ስምንት መቶ ሰላሳ ስምንት ሺህ አራት መቶ) ብር የሚገመት ንብረት ከተወሰደው ውስጥ 60,000 (ስልሳ ሺህ ብር) የተከፈለው ስለሆነ በፈጸመው ከባድ የስርቆት ወንጀል በፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የልደታ የወንጀል ዘርፍና የፍታብሄር ፍትህ አስተዳደር የልዩ ልዩ ወንጀሎች ዳይሬክቶሬት የክስ መዝገብ ያስረዳል፡፡

በሁለተኛ ክስ ደግሞ በ2005 ዓ.ም የወጣውን በወንጀል ድርጊት የተገኘን ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ በማቅረብ እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 780/05 አንቀጽ 29/1/ሀ/ስር የተመለከተውን ድንጋጌ ከላይ በተገለጸው ቦታና ጊዜ ለጊዜው ካልተያዙ ግብረ-አበሮቹ ጋር በመሆን የጥበቃ ሰራተኛ ሆኖ ሲሰራ በተለያየ ጊዜ በተመሳሳይ ቁልፍ የድርጅቱን የንብረት ማስቀመጫ ክፍል ከፍተው ከሰረቁት ንብረት ውስጥ ከደረሰው 60,000 ብር ውስጥ 10,000 (አስር ሺህ ብር) ጨምሮበት ሰኔ በ19 ቀን 2007 ዓ.ም የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 1-ደ/ህ 07963 የሆነ ትራይ ሳይክል ባጃጅ በ70,000 /በሰባ ሺህ/ ብር ከአቶ ታረቀኝ ናኡሻ በ23/10/2007 ዓ.ም ገዝቶ ውሉን ሲጽፍ በአርባ ሺህ ብር እንደተገዛ አድረጎ በገዥው ስም ሊብሬ እንዲያሰሩ፣ ሊብሬ
በሰነድ ፈርመው እንዲቀበሉ፣ ውል እንዲዋዋሉ ስሙን ወደ ስማቸው እንዲያዛውሩ የሚልና ስለንብረቱ አጠቃላይ ውክልና የወሰደ ስለሆነ
በፈጸመው በወንጀል ድርጊት የተገኘን ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል ተከሷል፡፡

የፌደራል ዐቃቤ ህግም በጉዳዩ ላይ ተከሳሽ ለመርማሪ ፖሊስ የሰጠውን 7 ገጽ የቃል ማስረጃ፣ የሽያጭ የውል ስምምነት ሰነዶችን እንዲሁም የሰው ማስረጃን ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል፡፡

የግራ ቀኙን ክርክር የተመለከተው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 2ኛ ችሎትም ህዳር በ18 ቀን 2011ዓ.ም በዋለው ችሎት በ14 ዓመት ጽኑ እስራትና እና በ10,000 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

ምንጭ፦ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
ሀዋሳ‼️

በኢትዮጵያና ኬንያ ድንበር በሞያሌና ቱርካና ተደጋግመው የሚከሰቱ ግጭቶች "የአካባቢው ምጣኔ ኃብት #እንዲቀጭጭና በቀጣናው ውጥረት እንዲሰፍን አድርጓል" ሲል የምሥራቅ አፍሪካ በየነ መንግሥታዊ የልማት ድርጅት(ኢጋድ) አስታውቋል። በጉዳዩ ላይ እየተነጋገረ ያለው የኢትዮጵያና የኬንያ ድንበር ተሻጋሪ የዘላቂ ሰላም የምክክር መድረክ የሁለቱ አገሮች የመንግሥት ባለሥልጣናት በተገኙበት ትላንት ሃዋሳ ከተማ ውስጥ ተከፍቷል፡፡

ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
‹‹ወጣቶች የመልካም ተግባር አርአያ መሆን እንጂ በስሜት በመነሳሳት #አንድነትን በሚሸረሽሩ ተግባራት ላይ መሰማራትየለባቸውም!››

የትግራይ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር #ደብረጽዮን_ገብረሚካኤል

@tsegabwolde @tikvahethiopia