TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ማስታወቂያ⬆️የዋቸሞ ዩኒ ቨርሲቲ እንዲሁም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የነባር ተማሪዎች የምዝገባ ቀን ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ተቋሞቹ ባወጡት ማስታወቂያ ገልፀዋል። 25/01/2011

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ሀዋሳ⬆️

#የሲዳማ የሀገር ሽማግሌዎች በ11ኛው የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ለመሳተፍ በሀዋሳ ከተማ ለሚገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድና ለጉባዔው ተሳታፊዎች የባህላዊ ቁርስ( #ቡርሳሜ ) ግብዣ አድርገዋል። የሀገር ሽማግሌዎቹ ከእንሰት የተዘጋጀውን ቡርሳሜ የተሰኘ ባህላዊ ቁርስ ከእርጎ ጋር ለተሳታፊዎቹ አቅርበዋል።

ምንጭ፦ አቶ ፍፁም አረጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ሀዋሳ⬆️

ኢህአዴግ #በሃዋሳ ከተማ ሲያካሂድ የቆየውን ጉባኤው በድል ማጠናቀቁን እና ዶ/ር #አብይ_አህመድ የኢህአዴግ ሊቀመንበር አቶ #ደመቀ_መኮንን ደግሞ የኢህአዴግ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው መመረጣቸው ያስደሰታችው መሆኑን ተከትሎ የሲዳማ ሽማግሌዎች እና የሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች በሃዋሳ ስታዲየም ዳኤ-ቡሹ በማለት ፍቅራቸውን በመግለጽ አሸኛኘት አድርገውላቸዋል። #የሲዳማ ሽማግሌዎችም ደማቅ በሆነው የቄጠላ ሥነ-ሥርዓት በመታጀብ መልካም የሥራ ዘመን ይሁንላችሁ በማለት ከልብ የመነጨ #ምርቃታቸውን አቅርበውላቸዋል።

ምንጭ፦ አቶ ፍፁም አረጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለትምህርት ሚኒስቴር‼️የተማሪዎች መግቢያ በፍኖተ ካርታ ውይይት ምክንያት በድጋሜ መራዘሙ ተገልጿል። ይህ ነገር የተሰማው ትላንት ነው። በተለይ በጥቅምት ወር የመጀመሪያዎቹ ቀናት ወደ ተቋማቸው የተጠሩት ተማሪዎች የአውሮፕላን እና የባስ ትኬት ቆርጠው ሲጠባበቁ ነበር። ይባስ ብሎም ከሩቅ አካባቢ ወደተቋማቸው ጉዞ የጀመሩም አሉ። ለመሆኑ ለነዚህ ተማሪዎች ምን የታሰበ ነገር አለ?? ትኬት የቆረጡ ተማሪዎችስ ገንዘባቸው ተመላሽ እንዲደረግ ይሰራል?? ከተለያዩ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጋርስ ውይይት ተደርጓል??

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስቸኳይ‼️ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ከጥቅምት 1-3 ብሎ የመግቢያ ቀን ቢያስቀምጥም ትምህርት ሚኒስቴር እንዲያራዝም በድጋሚ በማስታወቁ ላልተወሰነ ጊዜ የመግቢያ ቀኑ ተራዝሟል።

ምንጭ:-ከዩኒቨርሰቲው ኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከወላይታ ሶዶ⬆️

"የዓለም መምህራን ቀን 2018 "The right to Education means the right to a qualified teacher"በሚል መርህ ቃል በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ፕሬዝዴንት አቶ ዮሐንስ በንቲ እንዲህም የትምህርት ሚኒስቴር ተወካይ የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ኀላፊ ዶ/ር እሼቱ ከበደ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ መምህራን ፣ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የተመራረጡ ጥናታዊ ጽሁፎች አቅራቢዎች እንዲሁም የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ለ2 ቀናት የሚቆይ ኮንፈረንስ እየተካሄደ ይገኛል።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia