TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ለጥንቃቄ_ከጠቀማችሁ 1. በአዲስ አበባ ከተማ የሜትር ታክሲ አገልግሎት የምትሰጡ ወንድም እህቶቻችን እባካችሁ ጥንቃቄ አድርጉ። ማክሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ገደማ ወደ ጎተራ ማሰለጫ መውረጃ ወይም በተቃራኒ ወደ ቄራ የሚወስደው መስቀለኛ መንገድ አካባቢ አንድ አገልግሎት ሰጪን 3 ተሳፋሪ መስለው የገቡ ወንበዴዎች መሃል አስፓልት ፣ በብዛት መኪና በሚመላለስበት መንገድ ላይ ከውስጥ እቃ ይዘው ሲሮጡ መመልከቱን…
#AddisAbaba

“ የጫት መቃሚያ ፣ የሺሻ ቤቶች የወንጀል ድርጊት የሚዶለትባቸው ቤቶች ናቸው ” - ፓሊስ

በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ወንጀሎች እንደሚደርሱባቸው ነዋሪዎች ይገልጻሉ፡፡

አንዳንዶቹ እንደሚሉት ከሆነ፣ የጸጥታ አካላት ልብስ ለብሰው ጸጥታ አስከባሪ በመምሰል ወንጀል የሚፈጽሙ አሉ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፦

°  ተመሳስለው ወንጀል የሚሰሩ አካላት ላይ ምን አይነት ክትትል እየተደረገ ነው ?

°  ወንጀል በከተማዋ በምን ደረጃ ይገኛል ?

° ሕዝቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ? ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጠይቋል።

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ?

“ ሌባ የተለያዬ የወንጀል አፈጻጸም ስልት አለው፡፡ አንዱ የጸጥታ አካል መስሎ፣ ልብሱን በተለያዬ አይነት መንገድ ለማግኘት ሙከራ አድርጎና ለብሶ ወንጀል ሊፈጽም ይችላል፡፡

ይሄ በጣም ከበ ሁለት ጥፋት ነው፡፡

አንደኛው ህብረተሰቡ ፖሊስ ሊመስለው ከቻለ በፖሊስ ላይ ያለው አመኔታ ምንም ጥያቄ የለውም ይወርዳል፡፡ ሁለተኛው ጉዳት ደግሞ ወንጀሉ በፖሊስ ላይ ጫና/ሥራ ይፈጥራል፡፡

ስለዚህ ጥንቃቄ ማድረግና መረጃዎች በሚኖሩ ሰዓት ቶሎ መስጠት ያስፈልጋል፡፡

በተለይ በእንደዚህ አይነት ሁኔታዎች የሚፈጸሙ ወንጀሎች በጣም አደገኛ ናቸው፡፡ በጣም በጣም፡፡ ትልቅ ዋጋም የሚያስከፍሉ ናቸው፡፡

ወንጀል ፈጻሚውን በመያዛችን የጸጥታ አካላትን ልብስ ከየት አመጣህ ? ብሎ ለመጠየቅና ተባባሪ የሆነ አካል ካለ ተገቢ እርምጃ ለመውሰድ ምቹ ሁኔታ ይፈጥርልናል፡፡

ወንጀሉ ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድና ለህዝብ ግልጽ በማድረግ በእንደዚህ አይነት ወንጀል የተሰማሩ ሰዎች ሁለት፣ ሦስቴ እንዲያስቡ እናደርጋለን፡፡

ግን ሰው መረጃ በመስጠት ተባባሪ መሆን መቻል አለበት፡፡

መረጃ ማድረስ ብቻ ሳይሆን ፈጣን ማድረስ ነው መሆን ያለበት፡፡ አንዳንድ ጊዜ አንዳንድ ሰዎች ሰው መክሯቸው ' መረጃ ስጡ ' ተብለው ነው የሚናገሩት፡፡ ፈጣን ነው መሆን ያለባቸው፤ እንደዚያ ከሆነ ወዲያው በቁጥጥር ሥር እናውላቸዋልን፡፡

ወንጀሎች ከመፈጸማቸው አስቀድሞ ለመፈጸሙ ምክንያት የሆኑ ነገሮችን አስቀድሞ በማወቅ የማስወገድ ሥራ መሰራት አለበት፡፡

ለምሳሌ ፦ የወንጀል መንስኤ ብለን እኛ የምናያቸው የጫት መቃሚያ፣ የሽሻ ቤቶች የወንጀል ድርጊት የሚዶለትባቸው ቤቶች ናቸው፡፡

በዚህ በኩል ፖሊስ የሚወስደው በጣም ጠንካራ የሆነ እርምጃ አለ፡፡ ግን መረጃ ከመስጠት በኩል አሁንም ክፍተቶች አሉ፡፡ አንዳንዶቹ እንዳውም ለፖሊስ መረጃ ከመስጠት ይልቅ የመደበቅ ሁኔታ አለ፡፡

ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ሆነን ነው የወንጀል መከላከልን ሥራ የምንሰራው፡፡ ግን ግለሰቦቹ ወንጀል ከተፈጸመባቸው ወደ ሚዲያ ሳይሆን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ነው መሄድ የሚጠበቅባቸው፡፡ በትክክል የከተማውን የጸጥታ ሁኔታ ቼክ የምናደርግበትም አግባብ ያ ነው፡፡

ስለዚህ ወንጀል ሰዎች ላይ ሊፈጸም ይችላል፡፡ በተቻለ አቅም በከተማው ላይ የወንጀል ስጋት እንዳይኖር ነው እየተሰራ ያለው፡፡ በ2016 ዓ/ም አጠቃላይ የተቋማችን አፈጻጸም 31 ፐርሰንት ወንጀልን ቀንሰናል፡፡

አዲስ አበባ ትልቅ ከተማ በመሆኗ ለተለያዩ ወንጀል መፈጸሞች ምክንያት የሆኑ ነገሮች ሊያጋጥሙ ይችላሉ፡፡ ከክልል ከተሞችም በብዛት ሰዎች ይመጣሉ፡፡ ሰው ሥራ፣ ቋሚ አድራሽ ከሌለው ያለው አማራጭ አንድም መለመን ካልሆነም ወደ ዘረፋ የሚገባበት ሁኔታ ይኖራል፡፡

አጠቃላይ የከተማውን ነባራዊ ሁኔታ ተቋቁመው ከግምት ውስጥ በማስገባት የወንጀል መከላከልን ሥራ በመስራት ከተማዋ የጸጥታ ሁኔታ ላይ እንድትሆን ማድረግ እጅግ በጣም ትልቅ ሥራ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡

ከመደበኛ ሥራችን ጎን በጎን ኦፕሬሽናል የሆኑ ሥራዎችንም በመስራት በሌቦች ላይ ብቻ አይደለም በተቀባዮችም ጭምር ትልቅ ሥራ እየተሰራ ነው፤ በተለይ የመኪና እቃ ስርቆት በሚፈጽሙት፣ እቃውን በሚሸጡ፣ በሚደልሉ ላይ፡፡

በአዲስ ከተማና በልደታ ክፍለ ከተማ እንኳ በተሰራው ሥራ ወደ 71 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር አውለናል፡፡ እጅግ በርካታ ቁጥር ያለው የመኪና እቃም ይዘናል፡፡

ሆኖም በተለያዩ ቦታዎች ላይ ' ወንጀል ተፈጸመብኝ ' የሚል ሰው ሊያጋጥም ይችላል፡፡ እሱን ለመከላከል ደግሞ የምንሰራቸው ሥራዎች አሉ፡፡

ወንጀል የሚፈጽማባቸው አካላት ወደ ፖሊስ መጥተው ያመልክቱ፡፡ በርካታው ሰው ከዚያ ይልቅ ወደ ሚዲያ ይሄዳል፡፡ ወደ ሚዲያ አይሂድ ማለት አይደለም ግን ወደ ፖሊስ ቢመጣ ያለንበት የመከላከል አቅም የቱ ጋ ድርሷል ለማለት ይረዳናል።
"

#TikvahEthiopiaFamilyAA
#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
🔈#የዜጎችድምፅ

🔵 “ በጸጥታው ችግር  ታካሚዎች በሰው ጫንቃ ታዝለው ነው ሆስፒታል የሚሄዱት፡፡ ተሂዶም መድኃኒት የማይገኝበት ጊዜ አለ ” - ነዋሪዎች

⚫️ “ አቅራቢዎች በቂ የመድኃኒት አቅርቦት እያመጡ አይደለም ” - የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል

በአማራ ክልል፣ ባሕር ዳር ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች ከሆስፒታል ውስጥ መድኃኒት ስለማይገኝ ከግል ፋርማሲዎች በከፍተኛ ዋጋ ለመግዛት እየተገደዱ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ችግሩ የሚገጥማቸው በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ለህክምና ሲሄዱ መሆኑን ለአብነት ገልጸዋክ።

አንዳንዴም በጸጥታ ችግር መንገዶች ስለሚዘጋጉ ተመላላሽ ህክምና በወቅቱ መታከም እንዳልቻሉ አስረድተዋል፡፡

ከፍተኛ የሆነ ችግር ውስጥ ከገቡ ከዓመት በላይ እንዳስቆጠሩ ተናግረዋል።

በከተማዋ ተቋማት እንኳ ከሚከፈቱበት የሚዘጉበት ጊዜ እንደሚበዛ አስረድተዋል፡፡

በተለይ ደግሞ የጸጥታ ችግር በሚፋፋምበት ወቅት የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ሲለሚገደብ ታካሚዎች በሰው ጫንቃ ታዝለው ወደ ሆስፒታል እንደሚወሰዱ ጠቁመዋል።

በሸክም ተወስደው መድኃኒትና ሠራተኛ በሆስፒታሉ የማይገኝበት ወቅት እንዳል አስረድተዋል፡፡

በዚህም በተለይ ተመላላሽ ታካሚዎች መዳን እየቻሉ የመሞት እድላቸው እየሰፋ ነውና የሰላም ያለህ! ሲሉ ተማጽነዋል፡፡

ስማቸው እንዲነገር ያልፈቀዱ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ውስጥ የሚሰሩ አንድ ሀኪም፣ ታካሚዎች ሆስፒታሉ ውስጥ ‘ግላቭ ብቻ ነው ያለው ሌላውን ውጪ ነው የምንገዘው’ እንዳሏቸው ገልጸዋል።

“Ampicillin፣ Gentamicin፣ Vancomicin፣ Cefepime፣ Tretionin” የሚባሉ መድኃኒቶች በሆስፒታሉ ውስጥ እንደሌሉ፣ የ“Laboratory፣ CBC፣ Serum electrolyte፣Liver function test፣ CSF analysis፣ Echo፣ CT scan” አገልግሎቶች በተሟላ ሁኔታ እየተሰጡ እንዳልሆነም ገልጸዋል፡፡

በተለይ ከሳምንታት በፊት ትራንስፖርት ተቋርጦ ስለነበር ሠራተኞቹ ሥራ ለመግባት ተቸግረው እንደነበር፣ በዚህም ታካሚዎቹ ሰርጀሪ የሚሰራላቸው ቀኑ እየተራዘመ መሆኑን አልደበቁም፡፡

ለጉዳዩን ምላሽ የጠየቅነው የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል፣ “አቅራቢዎች በቂ የመድኃኒት አቅርቦት እያመጡ አይደለም፡፡ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከጸጥታውም ይሁን ካለው የገበያ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ማለት ነው” ብሏል፡፡

“ከዚያ በሻገር ግን ዛሬ ላይ መደበኛ ሥራችንን ለማስኬድ የሚያስችል ሰቶክም አለን፡፡ ችግሮችም ይኖራሉ ከአቅማችን በላይ በሆኑ ምክንያቶች” ነው ያለው፡፡

“በቂ ስቶኮች አንይዝም፡፡ ልናገኝ አንችልም፡፡ የ3፣ የ6 ወራት ብለን ልንገዛ አንችልም፡፡ እንገዛ ብንል በጀትም አይኖረንም አቅራቢም አናገኝም” ሲል አስረድቷል፡፡

ከጸጥታው ሁኔታ ጋር ተይይዞ ሠራተኞች አይገቡም ተብሎ ለቀረበው ቅሬታ ሆስፒታሉ ፥ “ ሠራተኞች ይገባሉ፡፡ መንገድ በተዘጋ ጊዜ በአምቡላንስ ነው የምናመጣቸው፡፡ ጦርነት በሚኖርበት ጊዜ ግን አስቸጋሪ ነው ” ሲል ገልጿል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#NewsAlert🚨

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የጭነት ተሽከርካሪዎችን እንቅስቃሴን ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 149/2016 አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።

ምን አለ ?

- መመሪያው የሚመለከታቸው የጭነት ተሽከርካሪዎች / የጭነት አቅማቸው ከ1 ቶን ወይም 10 ኩንታል በላይ የሆኑ ተሽከርካሪዎችን ነው።

- እነዚህ ተሽከርካሪዎች ጠዋት ከ1:00 ሰዓት እስከ 3:00 ሰዓት ድረስ እንዲሁም ከሰዓት 10:30 እስከ ምሽት 1:00 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ እንዳይችሉ ገደብ ተጥሎባቸዋል።

- በዋና መንገዶች ላይ ማቆም፤ ጭነት ማውረድና መጫን እንዲሁም መንቀሳቀስ በክልከላው የተካተቱ ናቸው።

- አዲሱ መመሪያ ከዚህ በፊት ከነበረው የሰዓት ገደብ ላይ በቀረቡ ቅሬታዎች ላይ ማሻሻያ ለማድረግ ታስቦ የወጣ እንደሆነ ተመላክቷል።

- አዲሱ መመሪያ ከመስከረም 2/2017 ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን ሲሆን እሁድ እንዲሁም የበዓል ቀናትን አይመለከትም።

የተቀመጡ የቅጣት እርከኖች ምንድናቸው ?

➡️ በተከለከለ ሰዓት በዋና ዋና መንገዶች ላይ የቆሙ የ10ሺ ብር ቅጣት፤

➡️ በተከለከለው የሰዓት ገደብ የተንቀሳቀሰ 20ሺ ብር የገንዘብ ቅጣት፤

➡️ በቅጣት ሂደቱ በድጋሜ የተቀጣ አሽከርካሪ የቅጣት እርከኑን በእጥፍ የሚቀጣ ይሆናል።

➡️ በተጨማሪ የቅጣት ወረቀት በመያዝ በዋና ዋና መንገዶች ላይ የሚንቀሳቀስ ትዕዛዝ ባለማክበር ተጨማሪ ቅጣት የሚተላለፍባቸው ይሆናል ተብሏል።

ቅሬታ ያላቸው በጹሑፍ ቅሬታቸውን ለባለሥልጣኑ በማመልከቻ ማቅረብ የሚችሉ ሲሆን የባለሥልጣኑ ውሳኔ የመጨረሻ ውሳኔ ይሆናል።

ይህ መመሪያ ቁጥር 149/2016 ከዚህ ቀደም የነበረውን መመሪያ ቁጥር 38/2013 እንዲሁም ሰርኩላሮች፣ ልማዳዊ አሰራሮች የሚሽር ነው።

ይህ መመሪያ ተግባራዊ የማይደረግባቸው የትኞቹ ተሽከርካሪዎች ላይ ነው ?

1ኛ. የሀገር መከላከያ፤ የፖሊስ እንዲሁም በጸጥታ አካላት ስም የተመዘገቡ ተሽከርካሪዎች፤

2ኛ. የድንገተኛ አደጋ ተሽከርካሪዎች፤

3ኛ. ነዳጅ የሚያመላልሱ ቦቴዎችን አይመለከትም።

ከዚህ ቀደም ወጥ አተገባበር ባልተስተዋለባቸው የውሃ አመላላሽ ቦቴዎች ላይ አዲሱ መመሪያ እንዴት ይመለከተዋል ? በሚል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላነሳው ጥያቄ ፥ በአዲሱ መመሪያ እንደሌሎች ከባድ ተሽከርካሪዎች እንደሚስተናገዱ ተገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#እንድታውቁት🚨

በአዲስ አበባ የጭነት ፣ ማሽነሪዎችን እና መሰል ተሸከርካሪዎችን እንቅስቃሴ ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 149/2016 ምን ይላል ?

- መመሪያው ወደ አዲስ አበባ ከተማ ክልል በሚገቡና በከተማ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ እንዲሁም ከተማዋን አቋርጠው በሚያልፉ የመጫን አቅማቸው ከ1 ቶን ወይም ከ1ዐ ኩንታል በላይ የሆኑ የተለያዩ የፈሳሽና የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች እና የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡

- ማንኛውም የጭነት ማመላለሻ ተሽከርካሪ እና የኮንስትራክሽን ማሽነሪ ከጠዋቱ 1፡00 እስከ 3፡00 ሰዓት ከሰዓት በኃላ ከቀኑ 10፡30 እስከ ምሽቱ 1፡ዐዐ ሰዓት ወደ ከተማ ውስጥ መግባትም ሆነ በከተማ ውስጥ መንቀሳቀስ፣ ጭነት መጫንም ሆነ ማራገፍ እንዲሁም በዋና ዋና የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው መንገዶች ላይ መቆም የተከለከለ ነው፡፡

- በዚህ መመሪያ መሠረት ወደ ከተማ መግባትም ሆነ በከተማ ውስጥ መንቀሳቀስ የተከለከለ የጭነት ተሽከርካሪ ወይም የኮንስትራክሽን ማሽነሪ ወደ ከተማ ለመግባት በእንቅስቃሴ ላይ እያለ የሰዓት ገደቡ ቢደርስበት በከተማዋ መግቢያ በሮች ላይ ከዋና መንገድ ወጣ ብሎ በሚገኝ ቦታ ላይ የአካባቢውን የትራፊክ እንቅስቃሴ በማያውክ መልኩ በመቆም የሰዓት ገደቡ እስኪያልፍ መጠበቅ አለበት።

- ማንኛውም የጭነት ተሽከርካሪ ወይም የኮንስትራክሽን ማሽነሪ በከተማ ውስጥ በእንቅስቃሴ ላይ እያለ በዚህ መመሪያ የተደነገገው የጊዜ ገደብ ቢደርስበት የአካባቢውን የትራፊክ እንቅስቃሴ በማያውክ መልኩ ከመንገድ በመውጣት መቆም አለበት።

- በዚህ መመሪያ የተደነገገው የሰዓት ገደብ #እሁድ እና #የበዓል_ቀናት ላይ ተግባራዊ የማይደረግ በመሆኑ ማናቸውም የጭነት ተሸከርካሪ ወይም የኮንስትራክሽን ማሽነሪ ወደ ከተማ ውስጥ መግባትም ሆነ በከተማ ውስጥ መንቀሳቀስ፣ ጭነት መጫን ሆነ ማራገፍ ይችላል፡፡

የሰዓት ገደብ የማይመለከታቸው ተሽከርካሪዎች የትኞቹ ናቸው ?

1. ሰሌዳቸው በሀገር መከላከያ ወይም በፖሊስ የተመዘገቡ የሀገር መከላከያ እና ሌሎች የፀጥታ ስራዎችን የሚያከናወኑ ከባድና ቀላል የጭነት ተሽከርካሪዎች፤

2. በህግ መሠረት የድንገተኛ አደጋ ተሸከርካሪዎች ተብለው የተለዩ የድንገተኛ አደጋ የሚሰሩ ቀላልና ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች፤

3. ነዳጅ የሚያመላልሱ ቦቴዎች

አስተዳደራዊ ቅጣቱ ምን ይመስላል ?

🔵 በተከለከለ ሰዓት ወደ ከተማ ውስጥ በመግባትና በዋና ዋና መንገዶች ላይ የቆመ ብር 10,000 (አስር ሺህ ) ይቀጣል፡፡

🔵 በዋና ዋና መንገድ ላይ የተንቀሳቀሰም ሆነ የጭነት መጫንና ማውረድ ተግባር የፈፀመ ወይም የኮንስትራክሽን ስራ የሰራ ብር 20,000 (ሃያ ሺህ) ይቀጣል፡፡

🔵 በመመሪያው ላይ የተደነገገወን የሰዓት ገደብ በመተላለፍ ከተቀጣ በኃላ ለሁለተኛ ጊዜ ጥፋቱን በመድገም የተገኘ ማንኛውም ሰው ከላይ የተገለፀውን ቅጣት በእጥፍ ይከፍላል፡፡

NB. በተከለከለው ሰዓት በከተማው ውስጥ ሲንቀሳቃስ በመገኘቱ ቅጣት የተጣለበት አሸከርካሪ ሰዓቱ ሳይደርስ የቅጣት ወረቀት ይዞ በተከለከለው ሰዓት እንዲንቀሳቀስ አይፈቀድለትም። የትራፊክ ተቆጣጣሪው ፍሰት በማያሰናክል ቦታ ላይ ተሸከርካሪው እንዲቆም በማድረግ ቅጣቱን እንዲከፍል ማድረግ አለበት፡፡

🗓 ይህ መመሪያ ከመስከረም 2 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
👏 #ሲፈን_ተክሉ የአዲስ አበባዋ ተማሪ ሲፈን ተክሉ በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተፈጥሮ ሳይንስ ከ600ው 575 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባለች። ሲፈን የኦግዝሌየም ካቶሊክ ትምህርት ቤት ተማሪ ናት። ተማሪዋ " ጌዜን ትምህርት ላይ ማሳለፌ ፣በቡድን ማጥናቴ ፣ የቤተሰብና የመምህራኖቼ ድጋፍ ለዚህ ስኬት አብቅቶኛል " ብላለች። ለቤተሰቦቿ 2ኛ ልጅ የሆነችው ሲፈን የስርዓተ ምግብ…
#ደሴልዩአዳሪትምህርትቤት👏

“ ትምህርት ቤቱ በአጠቃላይ ውጤት በኢትዮጵያ አንደኛ ፤ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ደግሞ ሁለተኛ ነው ” - የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት

በ2016 ዓ/ም አገር ዓቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በኢትዮጵያ በሁለተኛ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበው በአማራ ክልል፣ የይሁኔ ወልዱ ደሴ መታሰቢያ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ነው፡፡

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃሉን የሰጠው ትምህርት ቤቱ፣ የተመዘገበው ከፍተኛው ውጤት 574 መሆኑን ገልጿል፡፡

ይህን ውጤት ያስመዘገው ተማሪ ጌታቸው እያዩ ይባላል፡፡

ከዚህ ቀጥሎ በትምህርት ቤቱ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 562 መሆኑን ትምህትር ቤቱ ገልጿል፡፡

በትምህርት ቤቱ በሴቶች የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 546 ነው፡፡ ውጤቱ የተመዘገበው በሀያት አብዱ ነው።

የተመዘገበው ዝቅተኛ ውጤት ደግሞ 458 ነው፡፡

ትምህርት ቤቱ በአጠቃላይ ያስፈተናቸው ተማሪዎች ብዛት 65 ሲሆን፣ ከእነዚህ መካከል 45 ተማሪዎች ከ500 በላይ ውጤት አስመዝግበዋል ተብሏል፡፡

“ ትምህርት ቤቱ በአጠቃላይ ውጤት በኢትዮጵያ አንደኛ ነው፡፡ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ሁለተኛ ነው ” ሲል ትምህርት ቤቱ ለቲክቫህ ገልጿል፡፡

አክሎ፣ “ አጠቃላይ ውጤት የሚባለው፣ አንደኛ ትምህርት ቤቱ ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100 ፐርሰንት ሲያሳልፍ፣ ሁለተኛ ደግሞ የተማሪዎቹ ውጤት ተደምሮ ሲካፈል ነው፡፡ በዚህ ትምህርት ቤቱን ማንም ትምህርት ቤት አይበልጠውም አንደኛ ነው ” ብሏል፡፡

“ ትምህርት ቤቱ በአጠቃላይ ውጤት በኢትዮጵያ አንደኛ፤ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ደግሞ ሁለተኛ ነው ” ነው ሲል ገልጿል፡፡

የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት የሚገኝበት የአማራ ክልል ዘንድሮ በብዙ የሰላም እና ፀጥታ ችግር ውስጥ እያለፈ ያለ ክልል ነው።

ባለፉት ዓመታትም ክልሉ በጦርነትና የከፋ የፀጥታ ችግር ላይ ሆኖ እንኳን የሀገሪቱን ከፍተኛ ውጤቶች ያስመዘገቡ ተማሪዎች የወጡበት ነው።

ዘንድሮም ከሀገር ሁለተኛው ከፍተኛ ውጤት በዚሁ ክልል ተመዝግቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" እንደ ባሪያ ነው የምንታየው ፤ እባካችሁ ጭሁልን !! " - በማይናማር የሚገኙ ወጣቶች ማይናማር እና ታይላንድ ድንበር ላይ ከሚገኙ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የበየነ መረብ ማጭበርበር (Online Scam) ተግባራት ከሚፈጸምባቸው አንዳንድ ቦታዎች ቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክቶችን በቴሌግራም እየተቀበለ ይገኛል። እነዚህ ቦታዎች ላይ በርካታ የሀገራችን ወጣቶች ያሉ ሲሆን " ታይላንድ እንልካችኋለን " በሚል…
#Update

° " ብዙ አካላቸው የጎደለ ሰዎች አሉ፡፡ አካል እስከ ማጉደል ድረስ ነው ቅጣቱ " - ኢትዮጵያዊያን በማይናማር

° " መረጃው ትክክል ነው፡፡ ዜጎች ችግር ላይ ናቸው ተቋሙም ኃላፊነት ወስዶ ለወገኖቻችን ለመድረስ ጥረት እያደረገ ነው " - ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር

በማይንማርን ጨምሮ በአካባቢው የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን በከፋ ችግር ውስጥ እንደሆኑ ከወራት በፊት በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ድምጻቸውን አሰምተው እንደነበር ይታወሳል።

አሁንም ኢትዮጵያውያኑ የኢትዮጵያ መንግስት እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።

መጀመሪያ ከአገር ሲወጡ የተዋዋሉት የሆቴል ቤት ሥራ አስኪያጅ፣ ሀኪም እና የመሳሰሉትን ሥራዎች ሊሰሩና ዳጎስ ያለ ክፍያ ሊፈጸምላቸው እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

ይሁን እንጅ ከዚያ ከደረሱ በኋላ ሽፍታ ወዳለበት የማይናማር ክልፍ እንደወሰዷቸው፣ ጭራሽ ደመወዝ እንደማይፈጽሙላቸው ፣ ከውላቸው ውጪ ዶላር ማጭበርበር እንደሚያሰሯቸው አስረድተዋል፡፡

የሌሎች አገር ዜጎች በአገራቸው መንግስት አማካኝነት እየተለቀቁ ቢሆንም ኢትዮጵያዊያኑ ግን የከፋ ስቃይ ውስጥ እንደሆኑ ገልጸው መንግስት እንዲደርስላቸው በአንክሮ ጠይቀዋል፡፡

ቤተሰቦቻቸው በበኩላቸው፣ መንግስት የልጆቻቸውን ሕይወት እንዲያተርፍላቸው ተማጽነዋል፡፡

ኢትዮጵያዊያኑ በዝርዝር ምን አሉ ?

" እያንዳንዱ ሰው የግድ በቀን 17 ሰዓት መስራት አለበት፡፡ የተሰራበት ደመወዝ ግን አይከፈልም፡፡ ገቢ ካላስገባ ቅጣት አለ፡፡ አለንጋም አላቸው ይገርፋሉ፡፡ ጨለማ ቦታ ላይ ወስደውም ያስራሉ፡፡

በአንድ ጊዜ ሦስት 20፣ 20 ሊትር ጀሪካን ያሸክማሉ፡፡ ሁለቱን በሁለቱ ትክሻቸው፣ አንዱን በእግርና እግር መካከል እንዲሸከሙ የሚገደዱ ኢትዮጵያዊያን አሉ፡፡

በተጨማሪ ብዙ ሰዎች ባሉበት አካባቢ ፊት ለፊት እንደ ማሳያ ተደርገን እንገረፋለን፡፡ በቀን አምስት ሰዓት ብቻ ነው የሚታረፈው፡፡

እጅና ኮምፒዩተር ለአፍታ ከቦዘኑ፣ የሆነ ስህተት ከተሰራ ድብደባ አለ፡፡ ምንም ነጻነት የሌለበት አገር ነው፡፡

ብዙ አካላቸው የጎደሉ ሰዎች አሉ፡፡ አካል እስከማጉደል ነው ቅጣቱ፡፡ እግራቸው፣ እጃቸው፣ ሁሉ ነገራቸው የተጎዳ ሰዎች አሉ " ሲሉ አስረድተዋል።

ኢትዮጵያዊያኑን ካሉበት የከፋ ችግር ለማውጣት ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ ያቀረብንላቸው  የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ ለጉዳዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

" በማይናማር የሚገኙ ዜጎቻችን ጉዳይ ይታወቃል፡፡ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል በተለይ ሳወዝ ኤዢያ ካሉ ኤምባሲዎቻችን ውስጥ አንዱ ጃካርታ ነው፤ ኢንዶኖዢያ፡፡ ጉዳዩ እነርሱም ደርሷቸው እየጠከታተሉ ነው " ብለዋል።

" ይሄ መስመር በአጠቃላይ እንደ አዲስ የሕገ ወጥ ፍልሰት መንገድ ሆኖ ነው እየታዬ ያለው፡፡ እስከሁን ባልተለመደ ሁኔታ ወደዚህ አቅጣጫ ከዚህ ቀደም ከምናውቃቸው ትንሽ ወጣ ያለ ነው። ጉዳዩም ጥናት የሚፈልግ ሆኖ ነው የተገኘው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡

" ዜጎች የትም አገር፣ የትም ቦታ ይሁኑ የመጀመሪያው መዳረሻ ችግራቸውን ለመፍታት ውጪ ጉዳይ እንደመሆኑ መጠን ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ክትትል እየተደረገበት ነው " ብለዋል።

ኢትዮጵያዊያኑ የአካል ጉዳት ጭምር እየደረሰባቸው በመሆኑ በፍጥነት እንዲደረስላቸው እየጠየቁ እንደመሆኑ  ከኤምባሲዎቹ ጋር ያለው ንግግራችሁ ተስፋ አለው ? በምን ደረጃ ላይ ነው ? የሚል ጥያቄ ቲክቫህ ለአምባሳደሩ አቅርቧል።

አምባሳደሩ በምላሻቸው፣ " እንደ አጋጣሚ ሆኖ ኢትዮጵያ ማይናማር ውስጥ ኤምባሲ የላትም፡፡ ምንም አይነት ዲፕሎማሲክ ውክልና የለንም " ብለዋል።

" ስለዚህ ከእርቀት ሆነው ነው ይህን ነገር የሚከታተሉት፡፡ መረጃው ትክክል ነው፡፡ ዜጎች ችግር ላይ ናቸው። ተቋሙም ኃላፊነት ወስዶ ለወገኖቻችን ለመድረስ ጥረት እያደረገ ነው " ሲሉ አክለዋል።

በችግር ላይ እንደሆኑ የሚነገርላቸው
ከ3000 በላይ ኢትዮጵያዊያን እንደሆኑ ነው፡፡ ተቋምዎስ ስንት እንደሆኑ ያውቃል? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄም ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

" ቁጥር ልንሰጥ አንችልም፡፡ ነገር ግን ቁጥራቸው 3000ም ሆኑ ሦስት ኢትዮጵያዊያን ችግር ላይ እስካሉ ድረስ ችግራቸው ችግራችን ሆኖ ተቋሙ ዜጎችን ለመታደግ ይንቀሳቀሳል " ነው ያሉት።

ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba #ባጃጅ በአዲስ አበባ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት በሂደት ሙሉ በሙሉ መቋረጡ አይቀሬ እንደሆነ ተሰምቷል። በአዲስ አበባ ከተማ የባለሶስት እና አራት እግር ተሽከርካሪ ወይም ባጃጅ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች  የአሰራር ፣ የአጀረጃጀት፣ የአገልግሎት አሰጣጥና የዲሲፒሊን ቁጥጥር አፈጻጸም መመሪያ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጎ ነበር።                               …
#AddisAbaba

“ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ከተማው ጸጥታ ስጋት የሆኑ ባጃጆች አሉ ” - የኡ/ ትራንስፖርት ቢሮ

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ከአዲስ አበባ ውጪ መጥተው የሚሰሩ ባለሦስትና አራት እግር አሽከርካሪዎች የአዲስ አበባ መታወቂያ፣ የአዲስ አበባ ሰሌዳ እስከሚያሟሉና በማኅበር እንስከሚደራጁ ድረስ በከተማዋ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዳይሰጡ እንደሚደረግ ማሳወቁ ይታወሳል።

ቢሮው ይህን ያለው በእነዚህ የተሽከርካሪ አይነቶች ወንጀል እየተፈጸመ መሆኑን በመግለጽ ነው፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ጉዳዩን በተመለከተ ከወጣው መግለጫ በተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጥ ከከተማው ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራ ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡

Q. በታገዱት የትራንስፖርት አይነቶች ሥራ ተሰማርተው ቤተሰብ የሚያስተዳድሩ አሽከርካሪዎች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ለምን ሰፋ ያለ ጊዜ አልተሰጣቸውም ? ቀድሞ ማሳወቅ አይቻልም ነበር ?

አቶ ዳኛቸው ፦

“ አዲስ አበባ ዋና ከተማ እንደመሆኗ መጠን የሚበረታታውና የሚደገፈው ማስ ትራንስፖርት ነው፡፡ ከማስ ትራንስፖርት አንጻር አዲስ አበባ አውቶብስ ድርጅት አለ፡፡ ድጋፍ ሰጪ የምንላቸው ሦስት ቁጥር ታክሲዎች አሉ፡፡ ከዚያ ውጪ ቁጥር አንድ የምንላቸው ታክሲዎች አሉ፡፡

ከእነዚህም የበለጠ የሚበረታታውና የሚደገፈው ማስ ትራንስፖርቱ ነው፡፡ ከባጃጅ ትራንስፖርት ጋር ባለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አደራጅቶ ስምሪት መስጠት የሚችለው በአዋጁ መሠረት ራሱ የሰጠውን ታርጋ ብቻ ነው፡፡

ይሄ በአዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ክልሎችና ከተሞች በራሳቸው ታርጋ የሰጡት፣ የመዘገቡት ብቻ ነው አደራጅተው ማሰማራት የሚችሉት፡፡

ከባጃጂ ጋር ተያይዞ አዲስ አበባ ውስጥ ወደ 5,000 አካባቢ የሚጠጉ ባጃጆች በ93 ማኅበራት፣ እንዲሁም በ73 መስመሮች አካባቢ ላይ ታፔላ ወስደው እየተሰማሩ ነው ያሉት፡፡

አዲስ አበባ በዚህ ደረጃ አጣዳፊ ሥራውን ማሰማራት ተገቢነት የለውም፡፡

ከአዋጅ ውጪ ነው የሚል ቅሬታዎች በተደጋጋሚ ሲነሳ ነው የቆየው፡፡ ቅሬታውም ተገቢ ነው፡፡  ስለዚህ በዚህ ሰዓት ባጃጅን ማበረታታት፣ ማሰማራት አይደገፍም፡፡

በአንድ በኩል የአዲስ አበባ ታርጋ የላቸውም ኦልሞስት 99 ፐርሰንት፡፡ 243 ብቻ ናቸው የአዲስ አበባ ታርጋ ያላቸው ከ5 ሺዎቹ፡፡

አንደኛ ሕጉ መከበር አለበት፡፡ ስህተት በስህተት ላይ መደገም የለበትም፡፡ ሁለተኛ እነዚህ ባጃጆች አካባቢ ሌብነት ይካሄዳሉ፡፡

ህዝቡም እሮሮ ያቀርበል፡፡ ብዙ ቅሬታዎች ናቸው የሚቀርቡት፡፡ የጽንፈኛ ኃይልም አጋዢ ሆነው የሚሰሩ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ለከተማው ጸጥታ ስጋት የሆኑ ባጃጆች አሉ፡፡

ከተማ አስተዳደሩ ቅድሚያ የሚሰጠው ለከተማው ሰላም ነው፡፡ ስለዚህ እንዚህ ባጃጆች እንዲቆሙ ሳይሆን ወደ ሕግ እንዲመለሱ ነው፡፡ ወደ ሕግ እንዲመለሱ ሲደረግ ደግሞ አንደኛ መደረግ ያለበት አንደኛ ታርጋ ማውጣት ነው፡፡

ታርጋ ለማውጣት ደግሞ እዘዚህ ባጃጆች ታርጋ ያወጡበት ሂደው ክሊራንስ፣ ሊብሬ አምጥተው የአዲስ አበባ ታርጋ ወስደው እንዲደራጁና ወደ ስምሪት እንዲገቡ ማድረግ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ታርጋ ይወስዳሉ፣ ይዘጋጃሉ፣ ወደነበሩበት ይመለሳሉ”።


Q. ቢሮው አጣድፎ ውሳኔውን የወሰነበት ምክንያት ምንድን ነው? አጭር ጊዜ አልሆነም ወይ? ለሚለው ጥያቄ ቀጥታ ምላሽ እንዲሰጡ በድጋሚ ጠይቀናቸዋል፡፡

አቶ ዳኛቸው፦

“ ከተማ አስተዳደሩ ቅድሚያ የሚሰጠው ለከተማው ሰላም ነው፡፡ ትራንስፖርት ሰላምን መሆንን፣ ምቹ መሆንን፣ ተደራሽ መሆንን ይፈልጋል። ስለዚህ በባጃጆች አካባቢ ያለው ሌብነት፣ ዝርፊያ፣ ያለው የከተማውን ሰላም የማናጋት መጠቀሚያነት ከህዝብ በተደጋጋሚ እሮሮ የመጣበት ነው።

ሁለተኛ ታርጋ የሰጥዋቸው ክልሎች፣ ‘አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እኛ የሰጠነውን ካርታና ሊብሬ አደራጅቶ የማሰማራት ስልጣን የለውም ሕገ ወጥ ሥራ ነው እየሠራ ያለው’ የሚል ቅሬታ፣ ስሞታ፣ ክስ አለ፡፡

እውነት ነው በሰላማዊ መንገድ ሥራ የሚሰሩ ልጆች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ እነርሱንና ጤናማ ያልሆኑትን ለመለየት ወደ ሕጋዊ መስመር መመለስ ግድ ስለሆነ፡፡

ሰፊ ጊዜ የሚፈልግ ጉዳይ አይደለም፤ ምርምር አይደለም፡፡ ታርጋ ያወጡበት፣ መረጃቸው ያለበት ሂደው ማምጣት ነው፡፡ አብዛኛው ደግሞ መረጃ የሚያሳየው ሸገር ዙሪያ ነው፡፡

ምክንያቱም አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባጃጂ ታርጋ ሲሰጥ ስላልነበረ አብዛኛው ያወጡት እዚህ አካባቢ ናቸው። አማራ ክልልም ተጭነው የመጡ አሉ ይታወቃል፡፡ ሌሎች አካባቢዎችም ተጭነው የመጡ አሉ ይታወቃል፡፡

ዞሮ ዞሮ ግን ለምን ተጣደፋችሁ? ለሚለው ነገር የከተማውን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅ ማንኛውም ተሽከርካሪ ሕግ አክብሮ እንዲሰራ ለማድረግ ነው”፡፡


Q. አሽከርካሪዎቹ በከተማዋ ለመስራት እንደያሟሉ ከተጠየቁት መስፈርት አንዱ የአዲስ አበባ የነዋሪነት መታወቂያ መሟላት ነው፡፡ ይህን አገልግሎት ደግሞ ኤጀንሲው እየሰጠ አይደለም፡፡ መታወቂያውን የት አምጥው ያሟላሉ ተብሎ ነው እንዲህ የተደረገው ? ቢሮው ጉዳዩን አጢኖት ነበር ?

አቶ ዳኛቸው፦

“ ይሄ ጥያቄ ለምን Issue ሆኖ ይነሳል? የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መታወቂያ እየሰጠ አይደለም የሚለው መረጃ ስህተት ነው፡፡

ወሳኝ ኩነት ከከተማ ጀምሮ እስከ ወረዳ አደራጅቶ በቴክኖሎጅ ታግዞ ነዋሪው ግልጽ በሆነ መንገድ መታወቂያ እንዲያገኝ አመቻቾቶ መስራት ከጀመረ አመታት ተቆጥረዋል። "


Q. ከክልል ከተሞች በመሸኛ ለሚመጡት እየሰጠ እንዳልሆነ መረጃው እንዳለን ገልጸንላቸው፣ በድጋሚ ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠይቀናቸዋል፡፡
አቶ ዳኛቸው፦


“ አሁን እኛ እያወራን ያለነው ከክልል ሰው አዲስ አበባ ውስጥ መታወቂያ አውጥቶ ሥራ ይስራ እያልን አይደለም ያለነው፡፡ ግልጽ ነው አቅጣጫው ለምንድን ነው የአዲስ አበባ ነዋሪ መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈለገው ?

ዝርፊያዎች፣ ሌብነት፣ ተለያዩ ጽንፈኛ ኃይሎች መጠቀሚያ መሆን ማስቀረት ከተፈለገ የነዋሪነት ወታወቂያ የግድ ያስፈልጋል። ”
ብለዋል፡፡

ሌላ ጥያቄ እያቀረብንላቸው በነበረበት ወቅትም ማብራሪያቸውን መቅዳት እንድናቆም አስገድደው፣ ለጥያቄው ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ምላሽ ላልሰጠባቸው ሌሎች በርከት ያሉ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆነ በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትኩረት🚨 ዛሬም ድረስ የሰው ህይወት የሚቀጠፍባቸው የመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች ነዋሪዎች " በፈጣሪ ስም መፍትሄ ይፈለግልን ፤ ተሰቃየን ህይወታችን በሰቀቀን መግፋት ደከመን " ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርበዋል። " ተደጋጋሚ እርቅ ይፈጸማል ግን ሳይቆይ ያገረሽና ደም ይፈሳል፣ ሰው ይገደላል የምንገባበት አጣን ድምጻችን ይሰማ " ብለዋል። ከሰሞኑን በመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች…
🔈 #የነዋሪዎችድምፅ

በመስቃንና ማረቆ እየሆነ ያለው ምንድን ነው ?

በማረቆ እና መስቃን መካከል ለዓመታት በሚስተዋለው ግጭት ግድያና መፈናቀል ሊቆም እንዳልቻለ ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡

አሁንም ከፍተኛ የሆነ የበቀል ሥሜት ስላለ ሥጋት እንዳለባቸው ገልጸው፣ የሚመለከታቸው ባለድረሻ አካላት ለጉዳዩ እልባት እንዲሰጡት ጠይቀዋል፡፡

የማረቆ ልዩ ወረዳ ነዋሪዎች ምን አሉ ?

“ ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች በምሽት ንፁሃንን ይገድላሉ። ከሳምንት በፊትም ግድያ ነበር። በጣም ግራ የሚያጋባ ወቅት ነው፡፡

መገደሉ፣ መፈናቀሉ እየተለመደ መጣ፡፡ ምን እናድርግ ?

ነገሩ ለረጅም ጊዜ ትክክለኛ መፍትሄ ሳያገኝ የግጭት ቀጠና በመሆኑ ጉዳዩ እያሳሰበው ግማሹ የአይምሮ እና ለተለያዩ የህመም አይነቶች እየተዳረገ ይገኛል፡፡

የችግሩ ምንጭ የማረቆ ህዝብ የጠየቀው የ9 ቀበሌ የማካለል ጉዳይ ነው፡፡

ጥያቄው ለብዙ አመታት ሲሆን፣ በዚህ ረጅም ዓመት በህግ አግባብ ከክልል ምክር ቤት እስከ ፌደሬሽን ሲጠየቅ ቆይቷል፡፡

ግጭቱ ከተቀሰቀሰ ግን ከአምስት ዓመታት በላይ አስቆጥሯል፡፡

ለዚህ ግጭት ዋና ተጠያቂ ተብለው የሚወሰዱት ከጉራጌ ዞን እስከ ወረዳ ያሉ አመራሮችና የጸጥታ አካላት ናቸው።

በምሽት በሀሰተኛ ጥቆማና ጥርጣሬ ወጣቱን እያሳደዱት ስለሆነ ነገሩ ትኩረት ያስፈልገዋል ” ብለዋል፡፡

የምሥራቅ መስቃን ነዋሪዎች በበኩላቸው ፥ ከማረቆ ተፈናቅለው ወደ መስቃን የመጡ ወገኖች እንዳሉ ገልጸው፣ ችግሩ ያለው ሰላም ከማይፈልጉ ኃላፊነት ላይ ያሉ አካላት እንደሆነ አስረድተዋል፡፡

ግድያም በተለያየ ጊዜ እንደሚፈጸም ጠቁመዋል።

“ በማረቆ ተወላጆች ከስምንት በላይ ቀበሌዎች ተወስደውብናል ” የሚሉት ነዋሪዎቹ፣ ለዚህ ድርጊትም ኃላፊነት ላይ ያሉ አካላትን ተጠያቂ አድርገዋል፡፡

አንድ ስለጉዳዩ ያጫወቱን በምሥራቅ መስቃን የሚገኙ የእድሜ ባለጸጋ፣ “ ሁለቱ ብሔረሰቦች ተስማምተው መኖር እንዳይችሉ እያደረጉ ያሉት የፖለቲካ ትርፍ የሚፈልጉ አካላት ናቸው ” ብለዋል፡፡

በሁለቱ ወረዳዎች መካከል የሚስተዋለው የጸጥታ ችግር የተከሰተው በ2010 ዓ/ም ሲሆን፣ በ2014 ዓ/ም እርቀ ሰላም እንዲወርድ ተደርጎ ነበር፡፡

ይሁን እንጅ ከእርቀ ሰላሙ ወዲህም ችግር አገርሽቶ በየጊዜው ሞትና መፈናቀሉ ሊቆም አልቻለም፡፡

የሚመለከታቸው አካላት ምን እየሰሩ እንደሆነ ምላሽ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው አልተሳካም፡፡ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆኑ በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

° “ ልጆቻችን ችግር ላይ ናቸው የኢትዮጵያ መንግሥት በሕይወታቸው ይድረስልን ” - በማይናማር ያሉ ኢትዮጵያን ቤተሰቦች

° “ የእኛ ኤምባሲ ከዛ አገር መንግስት ጋር እየተነጋገረ ልጆች የሚመለሱበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እየተሞከረ ነው ” - የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጭ (ባለሥልጣን)

በማይናማር የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ፦
➡️ ከአገር ሲወጡ በተዋዋሉት መሠረት ሳይሆን በተቃራኒው ህገወጥ የማጭበርበር ተግባር ላይ እንዲሰማሩ እንደተገደዱ፣
➡️ በአግባቡ ደመወዝ እንደማይከፈላቸው፣
➡️ ይባስ ብሎ ድብደባ እየተፈጸመባቸው አካላቸው እስከመጉደል እንደደረሱ በቤተሰቦቻቸው ጭምር በቲክቫህ ኢትዮጵካ በኩል መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

በወቅቱ ስለጉዳዩ ምላሽ የጠየቅናቸው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ “ መረጃው ትክክል ነው፡፡ ዜጎች ችግር ላይ ናቸው ተቋሙም ኃላፊነት ወስዶ ለወገኖቻችን ለመድረስ ጥረት እያደረገ ነው ” የሚል ምላሽ ሰጥተውን ነበር፡፡

በማይናማር የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን አሁንስ ቤተሰቦች ምን አሉ ?

“ ልጆቻችን ችግር ላይ ናቸው የኢትዮጵያ መንግሥት በሕይወታቸው ይድረስልን፡፡ ትንሽ ክፍተት አግኝተው ደውለው ሲነግሩን የከፋ ችግር ውስጥ እንደሆኑ ነው የሚያስረዱን፡፡ ተጨነቅን እኮ!

በእርግጥ የኢትዮጵያ መንግስት ጥረት እያደረገ እንደሆነ ሰምተናል፡፡ ግን ልጆቻችን በዬቀኑ ድብደባና እንግልቱ እየከበደባቸው ነውና መንግስት በቻለው መጠን ተነጋግሮ ወደ አገራቸው እንዲገቡ እንድያደርግልን እንማጸናለን፡፡

መንግስትንም ለማጣደፍ የተገደድነው የወላጅ አንጀት አልችል ቢለን ነው፡፡ ልጆች በባዕድ አገር በእንዲህ አይነት የከፋ ችግር ውስጥ ሆነው ማየት ሀዘኑ መራራ እንደሆነ የወለደ ሁሉ ያውቀዋል ” ብለዋል።

በችግር ላሉት ኢትዮጵያዊያን ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ ያቀረብንላቸው አንድ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉና ጉዳዩን ከጅምሩ ጀምሮ የሚያውቁት ባለሥልጣን በበኩላቸው ተከታዩን ምላሽ ሰጥተውናል፡፡

“ ኢትዮጵያ እንደ አገር እዛ አካባቢ ካሉ አገራት ጋር የሥራ ስምሪት ስምምነት የላትም፡፡ ስለዚህ ልጆቹ በግላቸው ነው የሄዱት፡፡ ማንኛውም ሰው ለሥራ የመንቀሳቀስ መብት አለው፡፡ ከዛ አኳያ ሂደዋል፡፡

ነገር ግን ዜጎች ችግር ላይ ሲወድቁ መንግስት ዝም ብሎ ስለማይመለከት የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን ከሰማ ጀምሮ እየሰራ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊያኑ የሚሄዱት በታይላንድ በኩል ነው፡፡ ጉዳዩን የሚከታተሉት ህንድና ጃፓን ያሉት የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ናቸው፡፡

ከዚህ ቀደም ታይላንድ ላይ ታግተው የነበሩ ኢትዮጵያዊያንን ማስመለስ ተችሏል፡፡ እኛም የሥራ ስምሪት ወደ እዛ አገር ስለሌለ ዜጎች ወደዛ ባይሄዱ ይመረጣል የሚል መልዕክት ሰጥተናል፡፡

መሄዳቸው ልክ አይደለም ብቻ ሳይሆን ኃላፊነትም መውሰድ መቻል አለባቸው፡፡ ችግር ሲያጋጥም ብቻ መንግስት ላይ መጮህ ተገቢ አይደለም፡፡

ግን እዛ አካባቢ ተቸግረው የነበሩ ልጆችን መንግስት አስመልሷል፡፡ ነገር ግን ወደ ማይናማር የተሻገሩ አሉ፡፡ ወደ ማይናማር የተሻገሩት የሄዱበት ቦታ አስቸጋሪና ታጣቂዎች ያሉበት ቦታ ነው፡፡ የእኛ ኤምባሲ ከዛ አገር መንግስት ጋር እየተነጋገረ ልጆች የሚመለሱበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እየተሞከረ ነው። ” ብለዋል፡፡

የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በበኩላቸው ከዚህ ቀደም ከሰጡን ማብራሪያ በተጨማሪ፣ “ በተለይ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ፣ ወደ ደቡብ አፍሪካ መስመር ነበር የተለመዱት፡፡ አሁን ደግሞ ባልተለመደ ሁኔታ በጣም አዲስ ነገር ነው ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

“ ሕገ ወጥ ሰዎች ዝውውር በተለይ በደላሎች አማካኝነት ለአደጋ የሚያጋልጥ እንደሆነ ማንኛውም ዜጋ በተለይ ወደ ውጭ አገር ሲንቀሳቀሱ መጠየቅ፣ ማጣራት ያስፈልጋል ” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የሆነው ሆኖ ግን ውጪ ጉዳይ ኢትዮጵያዊያኑ ካሉበት ችግር እንዲወጡ እየሰራ መሆኑን አመላክቷል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Amhara

" ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዝገብ ነው እቅድ የተያዘው ከነሐሴ 20/2016 ዓ/ም ጀምሮ የተመዘገቡት ግን 1.7 ሚሊዮን ናቸው - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ

በመንግስት የጸጥታ ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በየጊዜው የተኩስ ልውውጥ የሚስተዋልበት አማራ ክልል በ2017 የትምህርት ዘመን ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዘገብ እንዳቀደ፣ ከነሐሴ 20 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ የተመዘገቡት ግን 1.7 ሚሊዮን ተማሪዎች መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል፡፡

የክልሉ ትምህርት ቢሮ፣ " ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 292 ሺሕ በላይ፣ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 1.2 ሚሊዮን በላይ፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወደ 180 ሺሕ ተማሪዎች ተመዝግበዋል " ብሏል፡፡

" በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምዝገባው እየተካሄደ ነው፡፡ ትንሽ እሱ ላይ መዘግየት ይታያል፡፡ እስካሁን በጠቅላላ ወደ 1.7 ሚሊዮን ተማሪዎች ናቸው የተመዘገቡት የእቅዱን ወደ 24 ፐርሰንት አካባቢ " ነው ያለው፡፡

በጸጥታው ችግር ባለፈው ዓመት በርካታ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው ይታወቃል፡፡  በ2017 የትምህርት ዘመንስ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ያሉ ተማሪዎች እጣ ፈንታቸው ምንድን ነው ? እውነት ተመዝግበውስ ለመማር አስቻይ ሁኔታ አላቸው ወይ ? ከዚህ አኳያ ቢሮው ምን አቅዷል ? ምንስ እየሰራ ነው? ስንል ቢሮውን ጠይቀናል፡፡

የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን " በክልሉ ከ10 ሺሕ 874 በላይ ትምህርት ቤቶች አሉ፡፡ በአዲሱ የትምህርት ዘመን የእኛ ፍላጎት እነዚህ ሁሉም ትምህርት ቤቶች 7 ሚሊዮን ተማሪዎች እንዲያስተምሩ፣ መማር ማስተማሩ እንዲጀምር/እንዲቀጥል ነው " ብለዋል፡፡

" በተለይ አንዳንድ ቦታዎች ላይ የጸጥታ ችግር ስላለ የትምህርት ሥራን ከዚህ በፊት እንደምናደርገው ሁሉ የምዝገባ ሥራን ለመስራት እንቅፋቶች ቢኖሩም ምዝገባ ተጀምሯል፡፡ የምዝገባ አፈጸጻሙ በምንጠብቀው ልክ ባይሆንም ምዝገባ እየተካሄደ ነው " ሲሉ አቶ ጌታው ተናግረዋል፡፡

የመማር ማስተማር ሂደቱ እዳይደነቃቀፍ በትጥቅ ትግል ላይ ያሉትን ጨምሮ ሁሉም ሰው ኃላፊነት መውሰድ እንዳለበት ቢሮው አስምሮበታል።

" አንድንድ ቦታ ላይ ትላንት ትምህርት ሲጅሩ ልንማር ይገባል የሚል ሞቶ ሁሉ ይዘው የወጡ ተማሪዎች አሉ፡፡ ይሄ በጣም ልብ ይብራል ሰው ሆኖ ለተፈጠረ ሁሉ፡፡ ምሁራን፣ የኃይማኖት አባቶች፣ በዛኛው ወገን ያሉ ወንድሞቻችንም ጭምር ይህን ተረድተው ትምህርትን ነጻ ሆነን እንድንስራ በጎ ሚናቸውን መጫወት አለባቸው " ሲሉ አስገንዝበዋል።

" በ2016 ዓ/ም በተለያየ ምክንያት ትምህርት ተቋርጦባቸው የቆዩ አካባቢዎች፤ ሳይማሩ የቆዩ ተማሪዎች፤ ተዘግተው የቆዩ ትምህርት ቤቶች አሉ " ሲልም ቢሮው ገልጿል፡፡

ከውድመት ጋር በተያያዘም አቶ ጌታቸው በሰጡት ቃል፣ " በክልሉ ካለው የጸጥታ ችግር ወይም ግጭት ጋር በተያያዘ ከፍተኛም መካከለኛም ጉዳት የደረሰባቸው ወደ 1115 ትምህርት ቤቶች አሉ " ነው ያሉት፡፡

" እነዚህን ትምህርት ቤቶች መልሶ ግብዓታቸውን በማሟላት ረገድ አንደኛ በአካባቢው ማህበረሰብ የሚሸፈን በዚያው ነው የሚሸፈኑት " ብለዋል፡፡

" የእኛን የክልሉን ኢንተርቬንሽን ሚጠይቁት ደግሞ አጋር አካላትን እያሳተፍን እቅድ አቅደን እያነጋገርን ነው፡፡ ከነርሱ ሀብት እያፈላለግን ትምህርት ቤቶች እንደገና ቁስቁሳቸው እንዲሟላ፣ እንዲገነቡ የማድረጉን ሥራ ወደፊት የምንስራ ነው የሚሆነው " ሲሉ አክለዋል፡፡

በክልሉ በ2016 ዓ/ም መመዘገብ ከነበረባቸው 6.2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከ2 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት እንዳልተመዘገቡ ተገልጾ የነበረ ሲሆን፣ በ2017 ትምህርት ዘመን ደግሞ ቢሮው ለመመዝገብ ካቀደው ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ይህ ዘገባ እስከተዘጋጀበት ጊዜ ድረስ ተመዘገቡ የተባለው 1.7 ተማሪዎች ናቸው፡፡

#TIKvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
🔈 #የወላጆችድምፅ

“ ወደ ባሕር ዳር ከተማ ልጆቻችንን ለማስመዘገብ ስንሄድ ለሚቀመጡበት ወንበር 6 ሺሕ ብር ክፈሉ እያሉን ነው ” - የተማሪ ወላጆች

“ እኔ የማውቀው ችግር የለም ” - የባሕር ዳር ከተማ ትምህርት መምሪያ

በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ዙሪያ የሚገኙ ወላጆች በጸጥታው ችግር በአካባቢያቸው መማር ያልቻሉ ልጆቻቸውን በባህር ዳር ከተማ ከፍተኛ ትምህርት ቤቶች ለማስመዝገብ ሲሄዱ ከአቅማቸው በላይ የሆነ ገንዘብ ክፈሉ እየተባሉ መሆኑን ለቲካቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

የተማሪ ወላጆች በዝርዝር ምን አሉ ?

“ በጸጥታው ችግር ምክንያት በባህር ዳር ዙሪያ ያሉ ወረዳዎች ትምህርት መቀጠል አልቻሉም፡፡

ጫናውን ተቋቁመን አንጻራዊ ሰላም ወዳለበት ወደ ባህር ዳር ልጆቻችንን ለማስመዘገብ መሸኛ ይዘን ስንሄድ ተማሪዎቹ የሚቀመጡበት አንድ ወንበር ለሦስት ይዛችሁ ስትመጡ ብቻ ነው የሚመዘገቡት እያሉን ነው።

በወላጅ ተለምነው በድርድር ወደ ገንዘብ ይቀይሩታል፡፡

አንድን ሰው 2 ሺሕ ብር፣ ለአንድ ወንበር 6 ሺሕ ብር ይጠይቃሉ፡፡ ልጆቻችን በጭንቀት ውስጥ ስለሆኑ ገንዘቡን በመክፈል ምዝገባ አካሂደናል፡፡

ተማሪዎቹ ቤተሰቦቻቸው በሚገብሩት ግብር የተሰሩ ትምህርት ቤቶች ነበሯቸው ፤ በጦርነቱ ምክንያት ስላልቻሉ ነው የመጡት። ከዚሁ ክልል ውስጥ ነው፡፡

ችግሩ ደግሞ የመጣው እራሳቸው መቆጣጠር ባለመቻላቸው ነው መስዋዕትነት እየከፈልን ያለነው። ችግሩን ተቋቁመን ስንሄድ አበረታትተው መቀበል ሲገባቸው ገንዘብ ያስከፍላሉ፡፡

ገንዘቡን ወንበር ይገዙበታል ወይ የሚለውም አጠያያቂ ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም ገንዘቡን ስንከፍል ደረሰኝ እንኳ አይሰጡንም፡፡

ክፍያውን የሚቀበሉት ለመመዝገብ የተወከሉ ሰዎች ናቸው፡፡ እንዲህ የሚደረገውም በባህር ዳር በሚገኙ ሃይስኩል ትምህርት ቤቶች ነው፡፡ ዞረን በጠየቅንባው ትምህርት ቤቶች ተመሳሳይ አሰራር ገጥሞናል፡፡

በጸጥታ ችግር መማር ሳይችሉ ከሚቀሩ አንጻራዊ ሰላም ወዳለበት አጎራባች ቦታ ሲሄዱ መባል የነበረበት ' እንኳን ደኀና መጣችሁ ' ነበር፡፡ ነገር ግን ተማሪዎቹ ሲሄዱ ሌላ ጫና እየተፈጠረ ነው፡፡

የወንበር ችግር ገጥሟቸውም አይመስለንም፡፡ ወላጅ ላይ የተለዬ ምሬትና ጫና ከመፍጠር በመተዛዘን ተማሪዎቹን ቢያስተናግዷቸው መልካም ነው፡፡ ገንዘቡን መክፈል ያልቻሉ መመዘገብ አልቻሉም። ” ብለዋል።

ለተነሳው ለዚህ ቅሬታ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የባሕር ዳር ከተማ ትምህርት መምሪያን ጠይቋል።

ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ አንድ ኃላፊ በሰጡት ቃል፣ “ ባሕር ዳር ዙሪያ ከባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ሊመዘገብ መጥቶ ሁሉም ትምህርት ቤት ጋር ' ለሦስት፤ ለሦስት አንድ ወንበር አምጡ ወይም ወንበር ይዛችሁ ካልመጣችሁ አላስተናግድም ' ያለ ትምህርት ቤት የለም። ” ብለዋል።

“ እኛ ጋ ' ችግር ደረሰብኝ ' ብሎ የመጣም የለም፡፡ ' ወንበር አምጣ ተብያለሁ ' ብሎ መጥቶ የጠየቀኝ ተማሪም የለም፡፡ ሁሉንም ትምህርት ቤት እየዞርኩ እያየሁ ነው፡፡ የትኛውም ትምህርት ቤት ላይ እየተመዘገቡ ነው። ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ አልፎ አልፎ አንመዘግብም ያሏቸውን እራሴ እየመራሁ ነው ያስመዘገብኳቸው፡፡ ትምህርት ቤቱ የማህበረሰብ ተሳትፎ ሊጠይቅ ይችላል፡፡ ግን አግሪመንት ወስዶ ማህበረሰቡ የፈረመውን ነው እያስከፈለ ያለው። ” ሲሉ አክለዋል።

“ እኔ የማውቀው ችግር የለም ” ያለው ትምህርት መምሪያው፣ እንዲህ የሚያደርጉ ትምህርት ቤቶች ካሉ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ቢያሳውቁት ታች ድረስ ወርዶ እርማት እንደሚያደርግ ገልጿል፡፡

ወላጆች መሰል ችግር ያለባቸውን ቦታዎች ለትምህርት መምሪያ መጠቆም እንደሚችሉ ተመላክቷል።

#TikvahethiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
" ወደ ፖለቲካ ፈጽሞ መመለስ አልፈልግም ! " - የእናት ፓርቲው አቶ ዳዊት ብርሃኑ

የእናት ፓርቲ አባል፣ አመራርና የሕዝብ ግንኙነት ሆነው ያገለገሉት አቶ ዳዊት ብርሃኑ ከዛሬ (መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ/ም) ጀምሮ በፈቃዳቸው ሥራ መልቀቃቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

" በተለይም ፓርቲው አንደኛ መደበኛ ጉባኤውን መጋቢት 30 ቀን 2015  ዓ/ም ባከናወነበት ወቅት በጠቅላላ ጉባኤው በሕዝብ ግንኙነት ከተመረጥኩ በኋላ የተሰጠኝን ኃላፊነት በአግባቡ ስወጣ ቆይቻለሁ " ብለዋል።

" በትብብር ፓርቲዎችም ዘንድ ባለኝ የፀሐፊነት ሚና የበኩሌን ድርሻ ስወጣ ነበር " ነው ያሉት።

" ምንም እንኳ ፓርቲው ከተመሠረተ ያስቆጠረው እድሜ አጭር ቢሆንም የቆየሁባቸው አራት አመታት በሀሳብ ልዕልና እና በሰለጠነ የሀሳብ ጉርብትና ብቻ ፖለቲካ መስራት የሚችሉ አባላትን ያፈራንበትም ወቅት ነበር " ሲሉም አክለዋል።

ከፓርቲው የለቀቁት በምን ምክንያት ነው? በሥራ? ባለመግባባት? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ በምላሻቸው፣ " ከፓርቲው የለቀቁት በግል ውሳኔ ነው " ብለዋል።

በተለይ የፓለቲካ ምህዳሩ እንደ ጠበበ በሚገለጽበት በአሁን ወቅት በፓርቲ ሥራ ውስጥ መቆዬት ተግዳሮቱ ምንድን ነው ? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ፣ " ከባድ ነው። የአገርና ሕዝብን አደራ መሸከም እጅግ በጣም ከባድ ነው" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ተፎካካሪ ፓርቲዎችና ገዢው ብልጽግና ለሻከረ ግንኙነታቸው መፍትሄው ምንድነው ይላሉ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ ምላቸው፣ " ሀቀኛ፣ ሁሉን አቀፍ፣ በአግባቡ የሚመራና ግልጽ የሆነ የፓለቲካ ድርድር ማድረግ " የሚል ነው።

የፓርቲ የሕዝብ ግንኙት አገልግሎትዎ ምን ይመስል ነበር? ለሚለው ጥያቄ ደግሞ፣ " አስቸጋሪ፣ ፈታኝ እንዲሁም ከፊል ስኬታማ ነበር " ብለዋል።

ካሁን ወዲያ በሌላ ፓርቲ እንጠብቀዎት ወይስ በፓርቲ ሥራ እስከወዲያኛው እየወጡ ነው? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ "ወደ ፓለቲካ ፈጽሞ መመለስ አልፈልግም" ነው ያሉት።

እናት ፓርቲ ለወደፊት ምን ያስተካክል? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ አቶ ዳዊት አጭር ምላሻቸው፣ "መሠረቱን" የሚል ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Amhara " ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዝገብ ነው እቅድ የተያዘው ከነሐሴ 20/2016 ዓ/ም ጀምሮ የተመዘገቡት ግን 1.7 ሚሊዮን ናቸው - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በየጊዜው የተኩስ ልውውጥ የሚስተዋልበት አማራ ክልል በ2017 የትምህርት ዘመን ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዘገብ እንዳቀደ፣ ከነሐሴ 20 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ…
#Amhara

“ የእኛ አብዛኛዎቹ ትምህርት ቤቶቻችን ደረጃ 2 ላይ ያሉ ናቸው፡፡ ደረጃቸው ዝቅተኛ ግን መማር ማስተማሩን ማስኬድ የሚችሉ እንደማለት ነው ” - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ

በአማራ ክልል በተለይ በጸጥታ ችግር ሳቢያ የግብዓት እጥረት ያለባቸው ትምህርት ቤቶች እንዳሉ፣ ይህም ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ማነቆ እንደሆነባቸው ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገጸዋል፡፡

ለአብነትም እንደ መጽሐፍት፣ ወንበር መሰል ቁሳቁሶች እንደሌሉ፣ የወደሙ ትምህርት ቤቶች አለመጠገን፣ በግጭት የቀጠና ውስጥ የሆኑ አቅመ ደካማ ወላጆች ደግሞ ለልጆቻቸው እንኳ የትምህርት ግብዓት ማሟላት እንዳልቻሉ ነው ያስረዱት፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ለጉዳዩ ምላሽ እንዲሰጥ የክልሉን ትምህርት ቢሮ ጠይቋል፡፡

ቢሮው ምን ምላሽ ሰጠ ?

“ የግብዓት እጥረት አለብን ያሉ ትምህርት ቤቶች ይኖራሉ፡፡ ትክክል ነው፡፡ የግብዓት እጥረታቸው በሁለት መንገድ ነው የሚፈታው፡፡

አንደኛ የአካባቢውን ማህበረሰብ በማሳተፍ ነው፡፡ ሁለተኛ ደግሞ በክልል ደረጃ ደግሞ የሚሟሉ አሉ፡፡ ለምሳሌ መጽሐፍት በክልል ነው የምናሟላው፡፡

ከ14 ሚሊዮን በላይ መጽሐፍት ታትመው ስርጭት ተደርጓል፡፡ አሁንም በቀጣይ የሚሰራጩ አሉ፤ ከ1 ቢሊዮን በላይ በጀት የክልሉ መንግስት መድቦ አሁንም የሚታተሙ መጽፍት አሉ፡፡

እነርሱን አሳትመን እናሰራጫለን፡፡ የመምህራን ቅጥርም እናሟላለን፣ ትክክል ነው፡፡

የእኛ ክልል ትምህርት ቤቶች ሙሉ ግብዓት የተሟላላቸው፣ ስንታንዳርዳቸውን ያሟሉ አይደሉም፡፡

ትምህርት ቤቶች በ4 ደረጃ ይከፈላሉ፡፡ ደረጃ 1፣ 2፣ 3 እና ደረጃ 4 ተብለው፡፡ ደረጃ 4 የሚባል ትምህርት ቤት በክልሉ የለንም፡፡

ደረጃውን ያሟላ በጣም ኢንተርናሽናል እንደማለት ነው፡፡ ደረጃ 3 የሚባለው ደግሞ ለተማሪዎች መማር ማስተማር የተሻለ የሆነ ትምህርት ቤት ማለት ነው፡፡

የእኛ አብዛኛዎቹ ትምህርት ቤቶቻችን ደረጃ 2 ላይ ያሉ ናቸው፡፡ ደረጃቸው ዝቅተኛ ግን መማር ማስተማሩን ማስኬድ የሚችሉ እንደማለት ነው፡፡ ይሄ ማለት ብዙ ግብዓት የሚጎድላቸው ናቸው፡፡

ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 3ቱም ሳይንስ ቤተ ሙከራ እንዲሟላ፣ ደረጃውን የጠበቀ የኳስ ሜዳ እንዲኖረው፣ አጥር እንዲኖረው፣ ስታንዳርዱን እንዲያሟላ፣ ፋሲሊቲውን በማሟላት ረገድ መስራት የሚጠይቀን ሥራ አለ፡፡

እሱን በእቅድ ለመምራት ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ ግን ሙሉ የሕብረተሰቡን ተሳትፎ የሚጠይቅ ሥራ ነው፡፡

የእኛን ትምህርት ቤቶች በስንት ዓመት እንቀይራቸዋለን ደረጃቸውን ለማሻሻል ብለን አንድ በጣም ትልቅ የለውጥ እቅድ አቅደን ወደ ሥራ በገባን ማግስት ነው የጸጥታው ችግር የተፈጠረው፡፡

በዚህ ዓመት ውስጥ ትምህርት ቤቶቹን እንቀይራለን ብለን ነበር ዞሮ ዞሮ ወደ ሥራ መግባት አልተቻለም ”
ብሏል፡፡

የግብዓት እጥረት ላለባቸው ከባለሀብቶችና ባለንብረቶች ድጋፍ የማሰብሰብ ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
" ጠቅላላ የአካል ጉዳተኞች ሕግ ከሁለት ዓመት በላይ የተስፋ እንጀራ ብቻ ሆኖብናል " - አቶ አባይነህ ጉጆ

የአካል ጉዳተኞችን ዘርፈ ብዙ የሆኑ ችግሮች ይፈታል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል የተባለው " ጠቅላላ የአካል ጉዳተኞች ሕግ " በታቀደለት ወቅት አለመውጣቱ አካል ጉዳተኞችን ዋጋ እያስከፈለ መሆኑን የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማኅበር ፌደሬሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የማኅበሩ ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይነህ ጉጆ  ምን አሉ?

“የአካል ጉዳተኞች ጉዳይ ሲነሳ በርካታ ችግሮች አሉ፡፡ ሆኖም ብዙ ችግሮቻችንን ሊቀርፍልን ይችላል ብለን እየጠበቅን ያለነው ጠቃላላ የአካል ጉዳተኞች ሕግ ይወጣል ብሎ መንግስት ተስፋ ሰጥቶናል።

በተስፋ ብቻ አላበቃም ሕጉ ድራፍት ተደርጎ የጋራ ምክክር ሕጉ ላይ አካል ጉዳተኞችም ተሳትፎ ከተረጋገጠበት በኋላ ለፍትህ ሚኒስቴር ሂዶ ነበር።

ፍትህ ሚኒስቴር አንዳንድ በእኛ በኩልም ተቀባይነት የሌላቸውን ኮመንቶች በመስጠት ወደኋላ መልሶታል። ሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው ሕጉን በባለቤትነት የሚያረቀው።

ጠቅላላ የአካል ጉዳተኞች ሕግ ከሁለት ዓመት በላይ የተስፋ እንጀራ ብቻ ሆኖብናል፡፡

እሱ ሕግ ቢወጣ የተሻለ ነገር ሊያመጣ ይችላል።

ሕጉ ቢወጣ እውነት ለመናገር በርካታ ችግሮቻችንን ይቀርፋል ብለን እናምናለን"
ብለዋል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-09-24

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
" ወደ 28 ሰዎች ናቸው የሞቱት፡፡ በአጠቃላይ 47 ሰዎች ላይ ሞት፤ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል፡፡ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል " - የዞኑ ፖሊስ መምሪያ

በወላይታ ሶዶ ዞን ዛሬ (ረቡዕ መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ/ም) ከቀኑ 7 ሰዓት ደረሰ በተባለ የትራፊክ አደጋ የበርካቶች ሕይወት ሲያልፍ በ47 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት መድረሱን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡

አደጋው የደረሰው መነሻውን ከወላይታ አድረጎ ወደ ዳውሮ ዞን ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ኪንዶ ዲዳዬ ወረዳ ፓፓታ ቀበሌ ሲደርስ መሆኑን ፖሊስ ገልጿል፡፡

በአደጋው የሞቱትና የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ምን ያክል ናቸው ? ስንል የጠየቅናቸው የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ንጋቱ በሰጡን ምላሽ፣ " በወደ 28 ሰዎች ናቸው የሞቱት፡፡ በ14 ሰዎች ከባድ፣ በ5 ሰዎች ቀላል ጉዳት ደርሷል " ብለዋል።

" አጠቃላይ ወደ 47 ሰዎች ላይ ሞት፤ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል " ብለዋል፡፡

" ከሕጻን እስከ አዋቂ ድረስ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ነው ጉዳት የደረሰባቸው " ነው ያሉት፡፡

" የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል፡፡ አሁን ወደ 8 ሰዎችም ወደ ከፍተኛ ህክምና ሪፈር እየተላኩ ስለሆነ ቁጥሩ ሊጨምር ይችላል " ሲሉ ኮማንደሩ ተናግረዋል፡፡

አደጋው የደረሰበት ምክንያት ታውቋል ? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ " የቴክኒክ ምርመራ ተደርጎ ወደፊት ነው የሚገለጸው፡፡ ለአሁን ግን ዳገት ተሽከርካሪው ዳገት እየወጣ እስክራፕ ነው የገጠመው፡፡ ከትልቅ ዳገት ላይ ወደ ቁልቁለትና ርቀት ባለው ወንዝ ውስጥ ነው አጠቃለይ ተሳፋሪዎችን ይዞ የገባው " ሲሉ መልሰዋል።

ተሽከርካሪው ስንት ሰዎችን ነበር ያሳፈረው ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ፣ " አጠቃላይ ቁጥሩን እየመዘገብን ነው፡፡ እስካሁን ባለው መረጃ በ47 ሰዎች ላይ ነው ሞትና ጉዳት የደረሰው፡፡ ጉዳት ሳይደርስባቸው የተረፉ ወደ 6 ሰዎች አሉ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

" ጠቅላላ ተሳፋሪዎቹ ከ56 እስከ 60 ሰዎች ይደርሳል የሚል ግምት አለን " ነው ያሉት፡፡

" ቦታው ወንዝ ውስጥ ነው፡፡ የአካባቢው ማህበረሰብም የጸጥታ ኃይልም ተረባርቦ ጉዳት የደረሰባቸውን የማንሳት፣ የተጎዱ በፍጥነት ወደ ህክምና እንዲደርሱ እየተደረገበት ያለ ሁኔታ አለ " ነው የተባለው፡፡

ምን ያክል ሰዎች ናቸው ወደ ሕክምና የተላኩት ? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ፣ " ጠቅላላ ወደ 21 ሰዎች ወደ ወደ ሆስፒታሎች ተልከዋል፡፡ 8 ሰዎች ከሆስፒታል ሪፈር ተብለው ወደ ክርስቲያን ሆስፒታል ተጭነው እየወጡ ያሉት ሁኔታ ነው ያለው " ተብሏል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ወደ 28 ሰዎች ናቸው የሞቱት፡፡ በአጠቃላይ 47 ሰዎች ላይ ሞት፤ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል፡፡ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል " - የዞኑ ፖሊስ መምሪያ በወላይታ ሶዶ ዞን ዛሬ (ረቡዕ መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ/ም) ከቀኑ 7 ሰዓት ደረሰ በተባለ የትራፊክ አደጋ የበርካቶች ሕይወት ሲያልፍ በ47 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት መድረሱን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡ አደጋው…
#Update!

“ ከባድ ሁኔታ ላይ ያሉ ተጎጅዎች አሉ፡፡ የ26 ሰዎች አስከሬን ተለይቶ ወደ ዳውሮ ዞን፣ የሁለት ሰዎች ደግሞ ወደ ወላይታ ዞን ተሸኝቷል ” - ወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ

ከወላይታ ዞን ወደ ዳውሮ ዞን እየተጓዘ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ዲዳዬ ወረዳ ፓፓታ ቀበሌ ሲድረስ ትላንት በደረሰበት ድንገተኛ አደጋ በ48 ተሳፋሪዎች ላይ ሞት፣ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹን ነግረናችሁ ነበር፡፡

ፖሊስ፣ አስክሬን የመፈልግ ሥራው እንደቀጠለ፣ በተለይ በ8 ተሳፋሪዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ስለደረሰ ሪፈር እንደተባሉና በዚህም የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ነበር የገለጸው፡፡

ሪፈር የተባሉት ተጎጅዎች እንዴት ሆነው ይሆን ? ስንል ዛሬ በድጋሚ የጠየቅናቸው የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ንጋቱ ጌታቸው ምላሻቸው፣ “ ተጎጅዎች ሕክምና እየተከታተሉ ናቸው፡፡ ጉዳቱ ከባድ ስለሆነ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል ” ብለዋል።

“ በክርቲያን ሆስፒታል፤ ኦቶና ሆስፒታልም ሕክምና እየተከታተሉ ነው፡፡ አንዳንድ ከባድ ሁኔታ ላይ ያሉ ተጎጅዎች አሉ ” ብለዋል፡፡

ኮማንደሩ የደረሰውን አደጋ ሂደት በተመለከተም፣ “ አስከሬን ወደ ቤተሰብ የመሸኘት ሥራ ተሰርቷል፡፡ የ26 ሰዎች አስከሬን ማንነታቸው ተለይቶ ወደ ዳውሮ ዞን፣ ሁለት ሰዎች ደግሞ ወደ ወላይታ ዞን ተሸኝቷል ” ነው ያሉት፡፡

“ ቀሪ ከባድና ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው 22 ተሳፋሪዎች በኦቶና ወላይታ ሶዶ ሆስፒታል እየታከሙ ነው ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ አስክሬን የማውጣት፣ ምርመራ የማድረግ ሥራ ሌሊቱን ጭምር እስከ 11 ሰዓት ድረስ ወስዷል፡፡ ሕዝቡ፣ አመራሩ፣ የጸጥታ ኃይሉ፣ ሙያተኞች ሁሉ ተረባርበዋል” ብለው፣ በዛ በአስቸጋሪ ቦታ ርብርብ ላደረጉት የወገን ደራሾች ምስጋና አቅርበዋል።

° አሽከርካሪው በፖሊስ ቁጥጥር ሥር እንደዋለ፣
° ቀላል ጉዳት እንደደረሰበት፣ ከሆስፒታል ክትትል አድረጎ እንደወጣ፣
° አሽከርካሪው ቃሉን ሲሰጥ የተለዬ መረጃ ካልተገኘ በቀር እስከሁን ባለው መረጃ በተሽከርካሪው ተሳፍረው የነበሩት ወደ 56 ሰዎች እንደነበሩ፣
° 6ቱ ተሳፋሪዎችም አደጋ ሳይደረስርባቸው እንደተረፉ አስረድተዋል።

“ የትራፊክ አደጋ ከገዳይ በሽታም በበለጠ የአገር ተረካቢ ትውልድን ጭምር እየጨረሰ፤ መተኪያ የሌለውን ሕይወትም እየቀጠፈ ነው " ብለዋል

" አሽከርካሪዎ፤ ባለንብረቶች፣ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ የትራፊክ ደንብና ሕግን አክብረው እንዲሽከረክሩ ጥሪ አቀርባለሁ ” ሲሉ ኮማንደሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የተሳፋሪዎች ቁጥር ከ56ም ሊጨምር ይችላል የሚል ግምት እንዳለ፣ የአደጋው ቴክኒካል ምክንያት ገና በምርመራ ላይ እንደሆነ የተመላከተ ሲሆን፣ በህክምና ላይ ያሉት ተጎጅዎችን ሁኔታ ጭምር ተከታትለን መረጃ የምናደርሳችሁ ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ተከፍቷል

በአዲስ አበባ ከተማ በመስቀል አደባባይ ከተከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ጋር በተያያዘ  ተዘግተው የነበሩ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ክፍት ተደርገዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ

“ የኢትዮ ቴሌኮም ነጻ ዳታ ሽልማት ለሁሉም አሮጌ ሲም ካርድ ተጠቃሚዎች ” በሚል ሰሞኑን ነጻ ሜጋ ባይት ለማግኘት “ ሊንክ ጠቅ ያድርጉ ” የሚል መልዕክት በማኅበራዊ ሚዲያዎች አማካኝነት ወደተለያዩ ግለሰቦች እየተላከና እየተዘዋወረ ነው፡፡

ይሄው ከሥሩ ሊንክ የተቀመጠበት የሚዘዋወረው መልዕክት ፡-
➡️ 6 ወር ለቆየ ሲም፣ 10GB
➡️ 1 ዓመትና ከዚያ በላይ፣ 20GB
➡️ ከ5 አመት በላይ ለቆየ ሲም፣ 50GB ነጻ ሽልማት ኢትዮ ቴሌኮም እየሰጠ መሆኑን የሚገልጽ ነው፡፡

አንዳንድ ሊንኩን የከፈቱ ሰዎችም፣ “ ስንከፍተው መረጃዎት እየተበረበረ ነው ይላል፡፡ ጉድ ተሰርተናል ” ሲሉ የተስተዋሉ ሲሆን፣ ብዙዎች ደግሞ ይህን ጉዳይ ኢትዮ ቴሌኮም ያውቀዋል ? በማለት እየጠየቁ ነው፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ የሚዘዋወረውን መልዕክት ተቋሙ ያውቀዋል? ትክክለኛስ ነው? ሲል ኢትዮ ቴሌኮምን ጠይቋል፡፡

የተቋሙ ቺፍ ኮሚዩኒኬሽን ኢፊሰር አቶ መሳይ ውብሸት ምን ምላሽ ሰጡ ?

“ የኛ ቲምም ቼክ አድርጎታል፡፡ Phishing የሚሉት የማጭበርበር መልዕክቶችን የሚልኩ ናቸው፡፡

ታማኝ ከሆኑ ካምፓኒዎች የሚላኩ መልዕክቶችን በማስመስልና የሰዎችን መረጃ የሚወስዱ Phishing  ብለን የምንጠራቸው የሳይበር ጥቃት መንገዶች ናቸው፡፡

እኛ ያስቀመጥነውም እንሰጣለን ያልነው ሽልማትም የለም፡፡ የላክነውም መልዕክት የለም፡፡ የኛ የሴኩሪቲ ቲምም እየተከታተለ ነው፡፡

ሊንክ ልከው እርሱን ንኩ ነው ‘ንኩ’ የሚሉት የእድሉ ተጠቃሚ ለመሆን፡፡ ግን ፐርሰናል መረጃዎችን የመውሰድና ላልተገባ ነገር ሰዎችን ለመዳረግ የሚያደርጉት ጥረት ነው፡፡

ዌብሳይቶቹን የኛ ቲሞች ሞኒተር እያደረጉ ሰዎች ላይ ጥቃት እንዳይደርስ ቁጥጥር እያደረጉ ነው፡፡

ሳይቶቹን የመዝጋት ሥራዎች እየተሰሩ ነው በቅንጅት፡፡ ስህተት እንደሆነ፣ የኛ እንዳልሆነ ሰው እንዲያውቅ እናደርጋለን፡፡

ይኛው መልኩን ቀይሮ የሰውን መረጃ ለመውሰድ ሆነ እንጂ ብዙ ጊዜ በተለይ ቴሌግራም አካባቢ ላይ ተከታይ ለማግኘት በኢትዮ ቴሌኮም፣ በቴሌ ብር እየተከፈቱ ደንበኛ ለማብዛት የሚደረጉ ጥረቶች አሉ፡፡

ይሄም ኢንቴንሽኑ ሌላ ቢሆንም ያው ነው፡፡ ከእኛም ብቻ አይደለም ምንጩን ስናጣራው ከሌላ አገር ውስጥ የሚመጣ፣ ወደ ሌላ አገር ሪፈር የሚያደርግ ነው ሊንኩ፡፡

የትልልቅ ተቋማት መልዕክት በማስመስል ሊንኮችን አስቀምጠው አጓጊ ሽልማቶችን እየሰጡ የሰዎችን መረጃ የማጭበበርበር ነገር ነው የሚፈጠረውና Phishing በተለያዬ በኢሜይል፣ በቴክስት፣ በጥሪ መልክም ሊመጣ ይችላል፡፡

ሰዎች ሊንኩን ባለመንካት ከእንደዚህ አይነት አሳሳች መልዕክቶች ራሳቸውን ይጠብቁ፡፡ እንዲህ አይነት ጉዳይ ሲገጥማቸውም በ9090 በነጻ ደውለው በዚያ እንዲያሳውቁንም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ”
ብለዋል፡፡

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) በበኩሉ፣  “ የኢትዮ ቴሌኮም ነጻ ዳታ ስልማት ለሁሉም አሮጌ ሲም ካርድ ተጠቃሚዎች ” በሚል መልዕክቶች ወደ ተለያዩ ግለሰቦች እየተላኩ መሆኑን እንዳረጋገጠ አስታውቋል፡፡

አስተዳደሩ፣ “ መልዕክቱ የግለሰቦችን ሚስጥራዊ መረጃዎችን የማጥመድ ጥቃት (Phishing Attack) መሆኑን ማረግገጥ ችያለሁ ” ብሎ፣ ግለሰቦች ሊንኩን ባለመክፈት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሪልስቴት #Update " ቤት ገብተው የሚኖሩ ሰዎች አሉ በጣም ነው የሚያሳዝኑት መብራትና ውሃ ስለሌለ እንጀራ ጋግረው አያውቁም እሱን እያየን ለመግባት ተቸግረል " - የኖህ ሪልስቴት ቤት ገዢዎች "...ለፕሬስ መግለጫ አልሰጥም  " - ኖህ ሪልስቴት የኖህ ሪልስቴት ሀያት ግሪን ቤት ገዢዎች ድርጅቱ በውሉ መሠረት የቤቱን መሠረተ ልማት እንዳላሟላላቸው በድጋሚ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታ አቀረቡ፡፡…
#Update

" በድጋሚ ቢሮ ሂደን ጠየቅናቸው ግን የተስፋ ቃል ከመስጠት ውጪ መሬት ላይ ምንም ተጨባጭ ነገር አይሰሩም  " - ቤት ገዢዎች

ከ600 በላይ የሚሆኑ የአያት ግሪን ኖህ ሪልስቴት ቤት ገዢዎች፣ በውላቸው መሠረት ድርጅቱ የመብራት፣ የውሃ፣ የታንከር መሠረተ ልማቶችን ባለሟማላቱ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ከፍለው ከገዙት ቤታቸው መግባት እንዳልቻሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል እሮሮ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡

በወቅቱ ለጉዳዩ ምላሽ የጠየቅነው ኖህ ሪልስቴት በበኩሉ፣ አንድ ጊዜ በሰጠን ምላሽ የመብራት፣ ውሃ፣ የታንከር ችግር እንዳለና መሠረተ ልማቶቹን ለማሟላት የዘገየው ችግር ገጥሞት እንደሆነ ገልጾ፣ " በጣም በአጠረ ጊዜ ውስጥ ለመስራት እየሞከርን ነው " ሲል ቃል ገብቶ ነበር፡፡

ይሁን እንጅ ቅሬታቸው ባለመፈታቱ ገዢዎቹ ከወራት በኋላ በድጋሚ ቅሬታ አቅርበዋል፡፡

ድርጅቱን በድጋሚ ጥያቄ ስናቀርብለት ግን፣ " በጠበቃቸው አማካኝነት እየተከታተሉ ስለሆነና ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት የመሄድ እድል ስላለው የድርጅቱን የመከራከር መብት የሚያጣብብ ስለሚሆን ለፕሬስ መግለጫ አልሰጥም " ከማለት ውጪ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጠቧል፡፡

ገዢዎቹ አሁንስ ዝርዝር ምን አሉ ?

" ምን ማድረግ እንዳለብን ጨነቀን፡፡ በገንዘባችን ቤት ገዝተን መሠረተ ልማቱ እንዲሟላ ለዓመታት እየለመንን እንገኛለን፡፡ እኛ ዋናው ጥያቄያችን ቤታችን ተጠናቆልን እንድንገባ ነው፡፡

በድጋሚ ቢሮ ሂደን ጠየቅናቸው ግን የተስፋ ቃል ከመስጠት ውጪ መሬት ላይ ምንም ተጨባጭ ነገር አይሰሩም፡፡ ማጭበርብር ማታለል ነው የተያያዙት፡፡ የሚነግሩን ነገር በብዙ ውሸት ታጀበ ነው፡፡

እየሄድን ስንጠይቅ በቃ መጫወቻ ነው የሚያደርጉን ንቀት ያለበት ቃላት ከመስጠት ውጪ ምንም የሚሰሩልን ነገር የለም፡፡

20፣ 30 እየሆንን እየተሰበሰብን እየሄድን ስድስት፣ ሰባት ጊዜ በአካል ቢሯቸው ሂደን ጠየቅናቸው ግን ቃል ከመግባት ውጪ የሚያደርጉት ነገር የለም፡፡

ስለዚህ ጠበቃ ወክለን በጠበቃችን አማካኝነት ያለበትን ፕሮጀክት ሂደት ስጡን፣ መቼ ትጨርሳላችሁ? ብለን ጠየቅናቸው፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድርም ተሰብስብን ሂደን ጠየቅን ግን ይህንን የሚከታተል አካል የለም፡፡ ሌላው የሚገርመው ነገር ደግሞ ይሄ ነው፡፡

በሌላ በኩል ግን ቤቱ ሳይጠናቀቅ የከተማዋ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ራሱ ሳይቱን ሂዳ መርቃለች፡፡

እኛን ብቻ ሳይሆን እሷንም ሸውደዋታል፡፡ ኤሌክትሪክ ጠልፈው፣ ኤሊቬተሩን አሰርተው፣ ፊኒሽንጉን የጨረሰ አንድ የቤት ባለቤት አለ እርሱን ለምነው ያንን ቤት ነው ያሳዩዋት (ለከንቲባዋ ማለታቸው ነው)፡፡

ከተማ አስተዳደሩም ያለውን እውነታ እንዲያውቅልን እንወዳለን፡፡ ቤቱ ተጠናቀቀ ብለው እኛ ላይ ዜና፤ ፕሮሞሽን ሰርተውብናል፡፡ ቤቱ ግን የውሃና የጋራ መሠረተ ልማቱ ምንም አላለቀም፡፡

አሁንም በውላችን መሠረት የውሃ፣ መብራት፣ ኢሊቬተር መሠረተ ልማቶች እንደሚሟሉልን እንጠይልን " ብለዋል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia