TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ይህ ጉባኤ ትግራይን እና ህዝቡን ወደ አደጋ ከመክተት የዘለለ እርባና የለውም " - አቶ ጌታቸው ረዳ

የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ ከደቂቃዎች በፊት መግለጫ አውጥተዋል።

ጉባኤው " በችኮላና የጋራ መግባባት ሳይደረስበት ፤ በማደናገርና በአቋም አልባነት አሰባስበናቸዋል በሚሉት ኔትወርክ  ' ይቃወሙናል ' የሚሉዋቸው የተወሰኑ #አመራሮች_ለማስወገድ በማለም የሚካሄድ ጉባኤ ነው " ብለውታል።

" ይህ ጉባኤ ትግራይን እና ህዝቡን ወደ አደጋ ከመክተት የዘለለ እርባና የለውም " ሲሉ ገልጸዋል።

ምክትል ሊቀመንበሩ  ፤ " የተሻሻለው የፓለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባ አዋጅ ህወሓት እንደ አዲስ እንደሚዘገብ የሚያደርግ ፣ ወርቃዊው የትግራይ ህዝብ ትግል የሚያጎድፍ በቀጣይ ቅርቃር ውስጥ የሚከት መሆኑን በመገንዘብ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ ብቻ እንዲፈቱ በማእከላዊ ኮሚቴ አባላት መግባባት ተደርሶ ነበር " ብለዋል።

" ይሁን እንጂ የተደረሰው መግባባትና መተማመን ወደ ጎን በመተው ' ከፌደራል መንግስት ተማምነናል ' በሚል ማደናገሪያ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመነጋገር  ከማእከላዊ ኮሚቴ እና ካድሬ በመደበቅ የተሄዴበት ሂደት ወዳልተፈለገ ወጥመድ እንድንገባ ተደርገናል " ብለዋል።

" በዚህ ምክንያት የሚፈጠር ማንኛውም ጥፋት ተጠያቂው ለጠባብ ቡድናዊ ፍላጎቱ ብቻ የሚንቀሳቀሰው ቡድን ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

አቶ ጌታቸው ፥ " የህዝቡ ሰላም እንዳይደፈርስና እንዳይረበሽ ከህዝባችንና ከመላ አባላችን በመሆን እንታገላለን " ብለዋል።

" ሁሉም የትግራይ አቅሞች በማቀናጀት በተደራጀ ትግል ከፍተኛ ፓለቲካዊ ድርድር በማካሄድ የህወሓት ህጋዊነት በመመለስ ካጠላብን ዙርያ መለስ ፈተና በመውጣት የትግራይ የተሟላ ደህንነትና እድገት እንደሚረጋገጥ ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ " ብለዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ድርጅቱ ጉባኤውን እንዳያካሂድ እንቅፋት የሚሆን ከድርጅቱ የተፈለፈለ ከፍተኛ አመራር አለ " - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር)

የህወሓት ከፍተኛ አመራሮችን ለሁለት የከፈለውና በብሔራዊ ምርጫ ቦርድም እውቅና የተነፈገው የህወሓት 14ኛ ጉባኤ መክፈቻ ዛሬ ተደርጓል።

የህወሓት ሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በመክፈቻው ባሰሙት ንግግር ምን አሉ ?

ሊቀመንበሩ " ድርጅቱ ህጋዊ እውቅና እንዳያገኝና ጉባኤው እንዳያካሂድ እንቅፋት የሚሆን ከድርጅቱ የተፈለፈለ #ከፍተኛ_አመራር አለ " ብለዋል።

" በፓርቲያችን ውስጥ ተፈልፎሎ ያደገ፣ ፓርቲያችን ለመበተን እየሰራ ያለው የጥፋት ቡድን ያደረገውና አሁንም እያደረገው ያለው እንቅስቃሴ፥ በየሰዓቱ እየፈጠረው ባለው ማደናገርያ ሁኔታችን ከመጥፎ ወደ ከፋ ደረጃ ተሸጋግሯል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ይህንም ለማስቆም በዘላቂነት ለመቀየር ብቸኛ መፍትሔው 14ተኛ ጉባኤ ማካሄድ እና ማካሄድ ብቻ ነው " ብለዋል።

" ህወሓት አድኖ ህዝብ ከጥፋት መታደግ የጉባኤው ዋነኛ አላማ ነው " ሲሉም ተናግረዋል።

" የድርጅቱና የህዝቡ የተሟላ ድህንነት ማረጋገጥ በሚችል መልኩ በዴሞክራሲያዊ ውይይትና ክርክር ብቃት ያላቸው አመራሮች መምረጥ ይገባል " ሲሉ ተደምጠዋል።

" የአሁኑ ጉባኤ ለድርጅቱ የሞት የሽረት ጉዳይ ነው " በማለት አክለዋል።

" ህወሓት ፈረሰ ማለት የፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት ፈረሰ ማለት ነው " ብለው " በዚህ ግዜ ህወሓት ከፈረሰ የፕሪቶርያው ስምምነት አይኖርም ብቻ ሳይሆን ከነአካቴው ታሪክ ሆኖ ይረሳል ማለት ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

" የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነት ከፈረሰ የትግራይ ህዝብ ለበይ አሳልፎ መስጠት ማለት ነው " ሲሉም ተናግረዋል።

" ስለዚህ እነዚህ ችግሮችና አደጋዎች ለመፍታት ነው ጉባኤአችን በዚህ ፈታኝ ወቅት ለማድረግ የፈለግነው ብቻ ሳይሆን የግድም ልናደርገው የተገደድነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF ' ህወሓት ' ውስጥ እየሆነ ያለው ምንድነው ? ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከትግራዩ ጦርነት በፊት እንደ ህጋዊ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ ስር ተመዝግቦ ይንቀሳቀስ ነበር። ነገር ግን  ቦርዱ ፓርቲው " ኃይልን መሰረተ ያደረገ የአመጽ ተግባር ላይ ተሰማርቷል " በሚል ሰርዞታል። የተወካዮች ምክር ቤትም ፓርቲውን " ሽብርተኛ ድርጅት " ሲልም ፈርጆት ነበር። ደም አፋሳሹና አስከፊው…
#Update

ሰባት የትግራይ የሲቪክ እና የንግድ ማህበራት በጋራ ባወጡት መግለጫ ፤ በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት ጥረት ማድረጋቸውን ነገር ግን ጥረታቸው አለመሳካቱን አሳውቀዋል።

በህወሓት አመራሮች የተፈጠረው መለያየት በድርጅቱ ዙሪያ ብቻ ተወስኖ እንዲቀር አሳስበዋል።

" ፓለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት አልሞ ህዝብ ለመከፋፈል የሚደረገው ጥረት ብፅኑ እናወግዛለን " ብለዋል።

ማህበራቱ ህዝቡ የፓለቲከኞች መሳሪያ ሆኖ ደህንነቱና አንድነቱ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

" የትግራይ የፀጥታ ሃይሎችም የልዩነት ፈጣሪ ከሆኑ ፓለቲከኞች ሳይወግኑ የህዝብ ደህንነት መጠበቅ ይገባቸዋል " በማለት አሳስበዋል። 

ማህበራቱ ፤ በፓለቲከኞቹ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት በመፍታት በኩል በአገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች የሚጠበቅባቸው ሃላፊነት እንዲወጡ ጠይቀዋል።

የሲቪክና ንግድ ማህበራቱ ፦
1. የትግራይ ስቪል ማሀረበረሰብ ጥምረት :
2. የትግራይ ህዝባዊ ግንኙነት ምክር ቤት
3. ጥላ የምዕራብ ትግራይ ስቪክ ማህበረሰብ ማህበር
4. የትግራይ የንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት
5. የትግራይ የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት
6. ግርዓልታ የፓለሲ ጥናትና ስልጠና ስቪክ ማህበር
7. ማሕበር ምውሓስ ሰላምን ልምዓትን ዶብን ወሰንን ትግራይ ናቸው።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia 
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia " መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ይቅርታ አድርጉልኝ ፤ ፕሬዜዳንታችንንም እዛው ሊወጡ ሲሉ ይቅርታ ጠይቂያለሁ አሁንም ይቅርታ ደግሜ ደጋግሜ ጠይቃለሁ !! " - አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ምን አሉ ? " የብር ጉዳይ አይደለም። ለእኛ (ለአሰልጣኞች) እየተሰጠን ያለው Value የተለያየ ነው። እኔ አስተማሪ ነበርኩ ፤ በአስተማሪነት ለ9 ዓመት አገልግያለሁ የጠላሁት ማንም…
#Update

አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ፣ የኢትዮጵያ ፕሬዜዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት ከኢትዮጵያ መንግሥት የተበረከተላቸውን የ2 ሚሊዮን ብር ሽልማት " አልቀበልም " ብለው መልሰው ከመድረክ መውረዳቸው ይታወሳል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር " ገንዘቡ ወደ መንግስት ካዝና ተመላሽ ይሆናል። ምክንያቱም ስጦታ በግድ ውሰዱ ስለማይባል " ሲል ለኤፍ ኤም 97.1 ተናግሯል።

አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ፤ ለሙያውና ለአሰልጣኞች የሚሰጠው ክብር ዝቅ ያለ በመሆኑ በስሜታዊነት ያንን ነገር እንዳደረጉ በዚህም ፕሬዜዳንቷን እና መላው የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ መጠየቃቸው ይታወሳል።

አሰልጣኙ ገንዘቡን ካላስተካከሉት እንደማይቀበሉም ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ መናገራቸው አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጉምሩክ ➡️ “ ከፍተኛ የወደብ ኪራይ የኮንቴነር ዲመሬጅ በየቀኑ እየጨመረብን ነው ” - አስመጪዎች ➡️ “ ከዚህ ሳምንት አያልፍም ” - ጉምሩክ ኮሚሽን አስመጪዎች ፣ ተግባራዊ የተደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ የጉምሩክ ኮሚሽን አዋጅን የሚተካ ' አዲስ መመሪያ ' በማውረድ እስከዛሬ ሲከፍሉት ከነበረው ቀረጥ ከእጥፍ በላይ ካልከፈሉ እቃቸውን መውሰድ እንዳይችሉ እያደረጋቸው መሆኑን ለቲክቫህ…
#Update

" ከሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም በፊት የሠነድ ምዝገባቸው የተከናወኑ እና ተቀባይነት ያገኙ ሠነዶች በበፊቱ የምንዛሪ ተመን ይቀጥላሉ " - ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ

ጉምሩክ ኮሚሽን ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውን የሰጡት ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ናቸው።

በዚህም ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲሱን መመሪያ ተግባራዊ ማድረግ ከጀመረበት ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም በፊት የሠነድ ምዝገባቸው የተከናወኑ እና ተቀባይነት ያገኙ ሠነዶች በበፊቱ የምንዛሪ ተመን እንደሚቀጥሉ አሳውቀዋል።

ጉምሩክ ፤ " የሠነድ ምዝገባ እና ማጣራት ሂደቱን በአግባቡ እየሠራ ይገኛል " ብለዋል።

" የብሔራዊ ባንክ አዲሱን መመሪያ ተግባራዊ ማድረግ ከጀመረበት ከሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም በፊት የሠነድ ምዝገባቸው የተከናወኑ እና ተቀባይነት ያገኙ ሠነዶች በበፊቱ የምንዛሪ ተመን ይቀጥላሉ " ሲሉ አረጋግጠው " የቀረቡ ሠነዶች ያልተሟሉ እና ቀሪ ጉዳዮች ኖረው ተቀባይነት ያላገኙ ሠነዶች የሚስተናገዱት በዕለቱ የምንዛሪ ተመን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ኮሚሽኑ ባለው የአሠራር መመሪያ መሠረት የገቢ ዕቃዎችን ሠነድ በመፈተሽ ወደ ሀገር እንዲገቡ እያደረገ እንደሆነ አስረድተዋል።

" በምንዛሪ ግብይቱ ላይ ባለው ለውጥ ምክንያት የተለያዩ ጥያቄዎች አሉ " ያሉት ኮሚሽነር ደበሌ " ከሕግና መመሪያ ውጭ የተሠራም ሆነ የሚሠራ ሥራ የለም " ሲሉ ገልጸዋል።

" እኛ #የሥራ_መመሪያዎችን ለደንበኞቻችን ሁሉ የማሣወቅ ሥራ እየሠራን ነው ፤ በአሠራር ሂደት ላይ ያሉ ጉዳዮችን ጠንቅቆ ማወቅ ያስፈልጋል " ማለታቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

#EthiopianCustomsCommission #FBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጉምሩክ ➡️ “ ከፍተኛ የወደብ ኪራይ የኮንቴነር ዲመሬጅ በየቀኑ እየጨመረብን ነው ” - አስመጪዎች ➡️ “ ከዚህ ሳምንት አያልፍም ” - ጉምሩክ ኮሚሽን አስመጪዎች ፣ ተግባራዊ የተደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ የጉምሩክ ኮሚሽን አዋጅን የሚተካ ' አዲስ መመሪያ ' በማውረድ እስከዛሬ ሲከፍሉት ከነበረው ቀረጥ ከእጥፍ በላይ ካልከፈሉ እቃቸውን መውሰድ እንዳይችሉ እያደረጋቸው መሆኑን ለቲክቫህ…
#Update

“ ሞጆ ቅርንጫፍ እየተጉላላን ነው። ትላንት የተላከውን ደብዳቤ ስራ አስኪያጅ ‘አልመራበትም’ ተብሎ ” - አስመጪዎች

“ ደብዳቤው ትላንትና ከመሸ ነው እኛ ጋ የደረሰው ከዋና መስሪያ ቤት፡፡ ተመርቶ ለሚመለከተው ክፍል ሰጥጠናል ” - ሥራ አስኪያጅ ክፍሉ

አስመጪዎች የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ በጉምሩክ እያጋጠማቸው ስላለው ሁኔታ ፤ ክፈሉ ስለተባሉትም ከፍተኛ ቀረጥ በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቤት ማለታቸው ይታወሳል፡፡

በወቅቱ ምላሽ የጠየቅነው የኮሚሽኑ የኮሚዩኒኬሽን ክፍል፣ ኮሚሽኑ አስመጪዎቹ የሚያነሱትን ጉዳይ እንደተረዳና በሰርኩላሩ ዙሪያም ውይይት እንደሚያደርግ አስረድቶ ነበር፡፡

ይህ በእንዲህ እያለ አስመጪዎቹ፣ ኮሚሽኑ ውይይት ማድረጉ መልካም ሆኖ እያለ ውሳኔው በዘገዬ ቁጥር ክፍያ እየጨመረባቸው በመሆኑ አፋጣኝ ውሳኔ እንዲሰጥ በድጋሚ ማሳሰባቸው ይታወቃል።

ለዚሁ ቅሬታ ምላሽ የጠየቅነው የኮሚሽኑ ኮሚዩኒኬሽን ክፍልም፣ በጉዳዩ ውይይት እየተደረገ መሆኑን ግልጾ፣ “ ከዚህ ሳምንት አያልፍም ” የሚል ምላሽ ሰጥቶ ነበር፡፡

ጉዳዩ ከምን ደረሰ? አስመጪዎችስ ምን አሉ ?

አስመጪዎችን ቅር ያሰኘው ሰርኩላር ላይ ኮሚሽኑ ማስተካከያ እንዳደረገበትና፣ በማስተካከያው መሠረት ደንበኞች እንዲስተናገዱ ማዘዙን ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ማስተካከያ የተደረገበት ሰርኩላር ያስረዳል፡፡

ማስተካከያውን ተከትሎም አስመጪዎች ዛሬ (ቅዳሜ ነሐሴ 11 ቀን 2016 ዓ/ም) ወደ ጉምሩክ ኮሚሽን ሞጆ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እቃቸውን ለማውጣት እንደሄዱ፣ ነገር ግን የሚያስተናግዳቸው ባለመኖሩ እየተጉላሉ መሆኑን ዛሬም ለቲክቫህ አቤት ብለዋል፡፡

“ ሞጆ ቅርንጫፍ እየተጉላላን ነው። ትላንት የተላከውን ደብዳቤ ስራ አስኪያጅ ‘አልመራበትም’ ብሎ ” ነው ያሉት፡፡

“ ትላንት የእቃ መልቀቂያ ደብዳቤ ወጥቶልን ነበር፡፡ ሞጆ ቅርንጫፍ ግን ጭራሽ እያስተናገዱን አይደለም፡፡ እንዳለ ሠራተኞች ቁጭ ብለዋል፡፡ የሚጭን መኪና ቆሟል፡፡ ከትላንትና ከሰዓት ጅምሮ ግን ምንም ሥራ እየተሰራ አይደለም ” ሲሉ አማረዋል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ አስመጪዎቹ እየተጉላላን ነው የሚል ቅሬታ አላቸው ለምን አታስተናግዷቸውም ? ሲል የኮሚሽኑን ሞጆ ቅርንጫፍ የደንበኞች አገልግሎት ክፍልን ጠይቋል፡፡

የደንበኞች አገልግሎት ክፍል በሰጠው ምላሽ፣ “ ጉዳዩን እናጣራው እኛ ሙያተኞች ነን፡፡ አመራሮች ጋ ጉዳዩን እናጣራ፡፡ ወደ አመራር ሂደው ጉዳያቸው እንዲፈታ ነው የምናደርገው እንጅ ዝም ብለን የምናጉላላበት ጉዳይ የለም ” ብሏል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በተጨማሪም፣ አስመጪዎች “ ሥራ አስኪያጅ ደብዳቤ አልተመራም ” በሚል እያጉላላቸው መሆኑን ቅሬታ አቅርበዋል፤ ደብዳቤው አልደረሳችሁም ? ሲል የኮሚሽኑም ሞጆ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ ክፍል ጠይቋል፡፡

የሥራ አስኪያጅ ክፍሉ ፀሐፊ አመራሮቹ ስብሰባ እንደገቡ ገልጸው፣ “ ደብዳቤው ትላንትና ከመሸ ነው እኛ ጋ የደረሰው ከዋና መስሪያ ቤት፡፡ እሱን ተመርቶ ለሚመለከተው ክፍል ሰጥጠናል ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

(ኮሚሽኑ ማስተካከያ ያደረገበት ደብዳቤ ከላይ የተያያዘ ሲሆን፤ ጉዳዩ ከምን እንደሚደርስ የምንከታተለው ይሆናል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Gamo : ሰሞኑን ለሶስት ተከታታይ ቀናት በጣለ ከባድ ዝናብ በተፈጠረ የመሬት መንሸራተት በጋሞ ዞን በገረሴ ዙሪያ ወረዳ ካምአለ ባርኤ ኦሮ ቀበሌ የ4 ሰዎች ሕይወት አልፏል። መረጃው  የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ጉ/ጽ/ቤት ነው። @tikvahethiopia
#Update

" አራቱ ሟቾች የአንድ ቤተሰብ አባል ናቸው " - በጋሞ ዞን የገረሴ ወረዳ አስተዳዳሪ

በጋሞ ዞን፣ ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ካማአለ ባርኤ ኦሮ ቀበሌ በደረሰ የናዳ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉ ይወቃል።

ከዚህ ባለፈ ደግሞ ከሰላሳ ሰባት በላይ የቤት እንስሳት ላይ ጉዳት ደርሷል ፤ 15 ቤቶችም መፍረሳቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተረድቷል።

የገረሴ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ካሳሁን ካማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " የሟቾችን ቀብር ከአካባቢዉ ማህበረሰብ ጋር በመሆን በክብር አስፈጽመናል " ብለዋል።

በአካባቢዉ ችግር ይከሰታል የሚል ቅድመ ትንበያም ይሁን ግምት ፈጽሞ እንዳልነበር ይልቁኑ በቀርከሀ የተሞላ ደን እያለ አደጋዉ መከሰቱ ሁኔታዉን አስደንጋጭ አድርጎታል ሲሉ ገልጸዋል።

አራቱ ሟቾች የአንድ ቤተሰብ አባል መሆናቸዉን የገለጹት አስተዳዳሪው በአንድ ቤት ዉስጥ ከነበሩት ሰባት ሰዎች ውስጥ በጓዳ የነበሩት አራቱ ሞተው ሶስቱ ከጓዳ ወጭ የነበሩት መትረፋቸውን ነግረውናል።

የሟቾች ስርዓተ ቀብር ከተፈፀመ በኃላ ወደ ቀጣይ ተግባር ተገብቷል ሲሉም ገልጸዋል።

አሁን ላይ የዝናቡ መጠን ከፍ እንደሚል መረጃ ማግኘታቸውን ተከትሎ ሌላ አደጋ እንዳይከሰት እንቅስቃሴ መጀመሩንና የአካባቢውን ሰው በማሸሽ በአጎራባች ቀበሌዎች ውስጥ ባሉ ትምህርት ቤቶች የጤና ኬላዎችና የእምነት ቦታዎች ማሳረፍ መጀመሩን አመልክተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት እና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ? ዛሬ መቐለ ሁለት ስብሰባ ሲካሄድ ውሏል። አንዱ የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የሚገኙበት 14ኛ የድርጅቱ ጠቅላላ ጉባኤ ሲሆን ሌላኛው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ ጉባኤውም የተቃወሙ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት በርካታ የክልል፣ የዞን እና ወረዳ አመራሮች የተገኙበት…
#Update

በህወሓት ምትክል ሊቀመንበር እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የተመራው የዛሬው የመቐለው ስብሰባ ቁጥራቸው አንድ ሺህ መሆኑ የህወሓት አባላትና አመራሮች ተገኝተው እንደነበር ተገልጿል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች ባለ 10 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት የአንድ ቀን ስብሰባቸውን ከምሽቱ 2:30 አጠናቀዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች ካወጡዋቸው ባለ 10 ነጥብ የአቋም መግለጫ አራቱ ነጥቦች የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የፈጠረው አንፃራዊ ምቹ ሁኔታ እንዲቀጥል የሚያስታውስ ነው።

" ሰላም አማራጭ የሌለው አማራጭ መሆኑ በመቀበልና በመረዳት ማንኛውም ወደ ግጭትና ጦርነት የሚመራ የውስጥና የውጭ ተንኮል በፅኑ እንቃወማለን " ይላል።

በአቋም መግለጫው ከተገለፁ አራት ነጥቦች  በህወሓት ሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የ14ኛው ጉባኤ ኢ-ህጋዊነት የሚያትት ሆኖ " ተደናግረው በጉባኤው በመሳተፍ ላይ የሚገኙት የህወሓት አባላት ወደ ቀልባቸው በመመለስ ከህዝባቸው ጎን እንዲሰለፉ " ሲል ያሳስባል።

ዘጠነኛው ነጥብ ደግሞ በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኘው የክልሉ ተወላጅ ፣ የድርጅቱ አባልና ደጋፊ ፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ፣ ማህበራት ፣ በዴሞክራሲያዊ መንገድ ምርጫ ተካሂዶ መንግስት እስኪቋቋም ድረስ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ደግፈው እንዲቆሙ ጥሪ ያቀርባል።

" የተከበራችሁ የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች በድርጅታችን ውስጥ የተፈጠረው የሃሳብ ልዩነት እንደ ሁሉ ጊዜ በጥሞና በማየት በማያዳላ መንገድ የህዝቡ ፀጥታና ሰላም ማስከበር ይገባል " ያለው የውይይቱ ተሳታፊዎች አስረኛ ነጥብ የአቋም መግለጫ የፀጥታ ሃይሎች አሁን የያዙት የማያዳላ አቋም አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቀርበዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

Via @tikvahethiopiatigrigna

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል በማለት በቁጥጥር ስር አውሎ የሽብር ወንጀል ምርመራ የከፈተባቸውን 6 ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ማንነት የሚያሳይ ፎቶ ይፋ አድርጓል። ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ያዋልኳቸው በሀገራችን ካለው የክረምት ወቅት ጋር ተያይዞ በተፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት " ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ አውሮፕላን…
#Update

የአቪዬሽን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ ፈጥረዋል የተባሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ በእነ ዮሐንስ ዳንኤል ላይ በጠየቀው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ላይ የግራቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ብይን ለመስጠት ለነገ ነሐሴ 21ቀን 2016 ዓ.ም ቀጠሮ ይዟል።

ተጠርጣሪዎቹ በጠበቆቻቸው በኩል የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። #ኢብኮ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአቪዬሽን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ ፈጥረዋል የተባሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ በእነ ዮሐንስ ዳንኤል ላይ በጠየቀው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ላይ የግራቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ብይን ለመስጠት ለነገ ነሐሴ 21ቀን 2016 ዓ.ም ቀጠሮ ይዟል። ተጠርጣሪዎቹ በጠበቆቻቸው በኩል የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው…
#Update

የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግር እና ወከባ ፈጥረዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን የግዜ ቀጠሮ ፈቅዷል።

ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው በጠበቆቻቸው አማካኝነት ጠይቀዋል።

ፍርድ ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል።

የፖሊስን የምርመራ ውጤት ለመጠባበቅ ለጳጉሜ 4 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray አሜሪካ በህወሓት እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መካከል ያለው ውጥረት እንዲረግብ ጠየቀች። ትላንት ትግራይ ፣ መቐለ የገቡት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር ተወያይተዋል። በዚህም ወቅት በህወሓትና በጊዚያዊ አስተዳደሩ መካከል የተፈጠረው ውጥረት መርገብ እንዳለበት አሳስበዋል።  አምባሳደሩ ውጥረቱ እንዲረግብ ከሰጡት…
#Update
 
የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ከሚመራው የህወሓት ቡድን ጋር መወያየታቸው ተሰምቷል።

በህወሓት የማህበራዊ  የትሰስር ገፅ የተሰራጨው መረጃ እንዳለው ፤ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ዛሬ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፈፃፀም ዙሪያና በክልሉ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ከድርጅቱ ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር (ማለትም በቅርቡ በተካሄደው ጉባኤ ከተመረጡት አቶ አማኑኤል አሰፋ) እና ሌሎች አመራሮች ጋር ተወያይቷል። 

አምባሳደሩ በውይይቱ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲፈፀም አገራቸው አሜሪካ እንደምትደግፍ ተናግረዋል።

አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ትላንት " በህወሓት እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መካከል ያለው ውጥረት እንዲረግብ " በማስመልከት ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር መወያየታቸውን መዘገባችን ይታወቃል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሪልስቴት #አዲስአበባ ° “ ብራችንን እኔ አውጥተን ተሰቃየን ” - የኖህ ሪልስቴት ቤት ገዥዎች ° “ የመብራት፣ የውሃ፣ የውሃ ታንከር ጥያቄ አለ ትክክል ነው ” - ኖህ ሪልስቴት በአዲስ አበባ ከተማ ፤ በኖህ ሪልስቴት ' የኖህ አያት ግሪን ፖርክ ቤት ' ገዢዎች ኖህ የገባውን ውል በመዘንጋት የቤት መሠረተ ልማቶችን እያሟላ እንዳልሆነ እና በጠበቃቸው በኩል ምላሽ እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም መፍትሄ እንዳላገኙ…
#ሪልስቴት #Update

" ቤት ገብተው የሚኖሩ ሰዎች አሉ በጣም ነው የሚያሳዝኑት መብራትና ውሃ ስለሌለ እንጀራ ጋግረው አያውቁም እሱን እያየን ለመግባት ተቸግረል " - የኖህ ሪልስቴት ቤት ገዢዎች

"...ለፕሬስ መግለጫ አልሰጥም  " - ኖህ ሪልስቴት

የኖህ ሪልስቴት ሀያት ግሪን ቤት ገዢዎች ድርጅቱ በውሉ መሠረት የቤቱን መሠረተ ልማት እንዳላሟላላቸው በድጋሚ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታ አቀረቡ፡፡

ቅሬታቸውን ያቀረቡ በርካታ ገዢዎች፣ ድርጅቱ በገባው ውል መሠረት መብራት፣ ውሃ፣ ጀነሬተር መሠረተ ልማቶች ባለሟሟላቱ ችግር ላይ እንደወደቁ ገልጸዋል።

መሠረተ ልማቱ ሳይጠናቀቅ የቤት ኪራይ ሽሽት ቤታቸው የገቡ ገዢዎች ያለ መሠረተ ልማት ከ1 ዓመት በላይ እንተቀመጡ በምሬት ተናግረዋል፡፡

መሠረተ ልማቱ እስከሚጠናቀቅ በኪራይ ቤት ሆነው እየጠበቁ ያሉ ገዢዎችም፣ ቤቱን ለመግዛት እስከ 4 ሚሊዮን ብር አውጥተው ሳለ መሠረተ ልማቱ ባለመጠናቀቁ አሁንም በቤት ኪራይ ወጪ እየተበዘበዙ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ወደ ቤታቸው ያልገቡበትን ምክንያት ሲያስረዱም፣ " ቤት ገብተው የሚኖሩ ሰዎች አሉ በጣም ነው የሚያሳዝኑት መብራትና ውሃ ስለሌለ እንጀራ ጋግረው አያውቁም እሱን እያየን ለመግባት ተቸግረል " ነው ያሉት።

ከዚህ ቀደም መሠረተ ልማቱን በወር ከ15 ቀን ውስጥ እንደሚያጠናቅቅ በሚዲያ በኩል ቃል ገብቶላቸው እንደነበር አስታውሰው፣ ግን ምንም ሳይሰራ ወራቶች እንደጠቆጠሩ ተናግረዋል።

ውሃው ግቢ ውስጥ ገብቷል ከተባለ ብዙ ጊዜ እንዳስቆጠረ፣ ነገር ግን አገልግሎት ላይ እንዳልዋለ፣ በዚህም የከፋ ችግር ለማሳለፍ እንደተገደዱ ነው የገለጹት፡፡

ድርጅቱ ይባስ ብሎ ቤቱ ሳያጠናቅቅ ጥበቃዎችን እያስወጣ መሆኑን፣ የከተማዋ ከንቲባ ሳይቱን የመረቁት ሳይጠናቀቅ መሆኑንም ተናግረዋል።

ላደረባቸው ቅሬታ ምላሽ ቢሮ ድረስ ሂደው ቢጠይቁም አጥጋቢ ምላሽ እንዳልተሰጣቸው አስረድተው፣ አሁንም መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅናቸው የኖህ የህግ አማካሪና ጠበቃ አቶ የሴፍ ደስታ፣ አጭር የመከላከያ ሀሳብ ከመስጠት ውጪ በቀጥታ ለቅሬታው ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

" በጠበቃቸው አማካኝነት እየተከታተሉ ስለሆነና ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት የመሄድ ዕድል ስላለው የድርጅቱን የመከራከር መብት የሚያጣብብ ስለሚሆን ለፕሬስ መግለጫ አልሰጥም " ነው ያሉት።

ድርጅቱ ከዚህ ቀደም ስለቅሬታው ጠይቀነው በሰጠን ምላሽ፣ " ትክክል ነው የመብራት፣ የውሃ፣ ታንከር ጥያቄ አለ " ብሎ ይህ የገጠመው በተለያዩ ችግሮች እንደሆነ ገልጾ ነበር።

በወቅቱ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤቱን መቼ አጠናቃችሁ ታስረክቧቸዋላችሁ? ስንል ጠይቀናቸው በሰጡት ምሌሽ፣ " ነገ ቢሆን ደስ ይለኛል፡፡ 654 ቤቶችን ሰርተን መብራት ለማስገባት የምንዘገይበት ምክንያት እኔ ራሱ አልገባኝም " ነበር ያሉት።

" ስለዚህ በጣም በጣም ባጠረ ጊዜ ውስጥ ለመስራት እየሞከርን ነው " ማለታቸው ይታወሳል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ትኩረት🚨

ዛሬም ድረስ የሰው ህይወት የሚቀጠፍባቸው የመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች ነዋሪዎች " በፈጣሪ ስም መፍትሄ ይፈለግልን ፤ ተሰቃየን ህይወታችን በሰቀቀን መግፋት ደከመን " ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርበዋል።

" ተደጋጋሚ እርቅ ይፈጸማል ግን ሳይቆይ ያገረሽና ደም ይፈሳል፣ ሰው ይገደላል የምንገባበት አጣን ድምጻችን ይሰማ " ብለዋል።

ከሰሞኑን በመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች የ9 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ የአካባቢዉ ባለስልጣናት መታሰራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።

ባለፉት ጊዜያት የነበረዉ የንጹሀን ግድያ  ለተወሰነ ጊዜ ረገብ ቢልም ከሰሞኑ እንደገና ባገረሸ ግጭት የ9 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 4 ሰዎች ደግም ቆስለዋል።

ይህን ተከትሎ አካባቢዉ ውጥረት ዉስጥ በመግባቱ አሁን ላይ በአካባቢዉ የሚኖሩ ንጹሀን በፍርሀት ውስጥ ናቸው።

" ኢንሴኖ ከተማና አካባቢው በየጊዜው በሚነሳው ግጭት ገጠራማው ቀበሌ የሚኖረው ምስኪን ግድያ ሲፈጸምበት ቆይቷል " የሚሉት ነዋሪዎቹ " በአካባቢው ሲስተዋል የነበረዉ የበቀል መጠፋፋት አሁንም በከፋ ሁኔታ ተመልሶ ይመጣል በሚል ተጨንቀናል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከሰሞኑ በማረቆ ልዩ ወረዳ በሌሊት በተፈጸመ ጥቃት የ7 ሰዎች ህይወት (4ቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት) እንዲሁም በመስቃን ደግሞ 2 ሰዎች ህይወታቸው መቀጠፉን የሚናገሩት ነዋሪዎቹ ሁኔታውን የመንግስት አካላት ቶሎ ካልተቆጣጠሩት ግጭቱ ከፍ ሊል ይችላል ሲሉ ፍርሀታቸውን አስረድተዋል።

ስለሁኔታዉ የጠየቅናቸዉ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ ኃላፊዉ አቶ ተካልኝ ንጉሴ ስለሁኔታው መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ይሁንና በልዩ ወረዳዎቹ ግድያ መፈጸሙን ተከትሎ አካባቢውን ለማረጋጋት ወደቦታው ያቀናው የጸጥታ ኃይል ጥቂት የአካባቢው ግለሰቦችን ጨምሮ ግጭት በተፈጠረባቸዉ አካባቢዎች ለጊዜዉ ስማቸዉ አይጠቀስ የተባሉ የወረዳ ከፍተኛ ባለስልጣናትን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን ለማወቅ ተችሏል።

አሁን ላይ ኢንሴኖን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች የፌደራልና የክልል የጸጥታ አካላት ተሰማርተው ህዝቡን እያረጋጉ ሲሆን የህዝቡ እንቅስቃሴ ግን በጅጉ መቀዛቀዝ ይስተዋልበታል።

ይህ አካባቢ በተደጋጋሚ የሰዎች ህይወት የሚቀጠፍበት ፣ ዜጎች የሚፈናቀሉበት ሲሆን ዘላቂና አስተማማኝ መፍትሄ ሳይገኘ ዛሬም በዛው ቀጥሏል።

#Update : ከመሸ ስልክ ያነሱልን የምስራቅ ጉራጌ ወንጀል መከላከል ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር መሀመድ ሀሰን " አሁን ላይ ሁሉም አካባቢ ሰላም " መሆኑን ጠቅሰው ስለሁኔታው አሁን ላይ መረጃ መስጠት ከባድ መሆኑን ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" በረራውን ለማቋረጥ የተገደድኩት ገንዘብ እንዳላንቀሳቅስ በመታገዴ ነው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ የሚያደርገው በረራ ከመስከረም 20፣ 2016 ዓ.ም ጀምሮ እንዲቆም የሚያሳውቅ ደብዳቤ ጽፎ እንደነበር ይታወሳል።

ዛሬ አየር መንገዱ በሰጠው መግለጫ ውሳኔው ይሻሻላል በሚል ሲጠብቅ እንደነበር እና የኤርትራ የሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣንን ለማናገር በተደጋጋሚ ያደረገው ሙከራ አለማሳካቱን አስታውቋል።

የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በመግለጫው እንደጠቀሱት በአስመራ የሚገኘው ተወካያቸው ከሽያጭ የተሰበሰበ ገንዘብ ለማስገባት ሲል ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ መላክ እንደማይቻል ተነግሮታል። ይህ የሆነው ሐምሌ 18/2016 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ አማካኝነት ነው።

" ' ከነሐሴ 25/ 2016 ዓ.ም በኋላ ሂሳባችሁ ታግዷል ለሀገር ውስጥ ወጪም (oppration fee) መጠቀም አትችሉም ' መባሉን ተከትሎ ከዛሬ ጀምሮ በረራውን ለማቋረጥ ተገደናል። የበረራ ወጪያችንን መሸፈን ባለመቻላችን ተገደን ወጥተናል " ሲሉ ነው የገለጹት።

አየር መንገዱ እንዳያንቀሳቅስ የታገደበት ገንዘብ መጠን ስንት ነው ?

ይህ ጥያቄ ከጋዜጠኞች የቀረበላቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚው የገንዘቡን መጠን ከመግለጽ ተቆጥበው ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አየር መንገዱ በኤርትራ ሁለት አካውንት እንዳለው የገለጹት አቶ መስፍን፥ አንዱ የናቅፋ አካውንት ሲሆን የቆየ እንዲሁም ወደ ዶላር መቀየር ያልተቻለ የማይንቀሳቀስ የሂሳብ አካውንት መሆኑን ገልጸዋል።

ሌላኛው የባንክ አካውንት ደግሞ የዶላር ሲሆን ባለፉት ጥቂት ዓመታት ትኬት ሲሸጥ የነበረው በውጭ ምንዛሬ መሆኑን ገልጸው ይህንን ገንዘብም እገዳው እስከተላለፈበት ቀን ድረስ በተለያዩ ጊዜዎች ገንዘቡን ሲያንቀሳቅስ እንደነበረ ገልጸዋል።

" የበረራ እገዳውን ካወጡብን በኋላ ነው Block ያደረጉብን " ሲሉ ነው የገለጹት።

አቶ መስፍን አክለውም ፥ "ለእኛ ገንዘቡ ካልተለቀቀልን ከዚህ በኋላ የሁለቱ ሀገራት ጉዳይ ነው የሚሆነው " ሲሉ ጉዳዩን ለኢትዮጵያ ለሲቪል አቬሽን ባለሥልጣን እና ለውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቃቸውን ገልጸዋል።

" አየር መንገዱ ከኤርትራ የወጣው ተገዶ ነው " ያሉት አቶ መስፍን ዋናው ችግሩ ለምን እንደታገድን አለማወቃችን ነው፤ በተጻፈው ደብዳቤም ላይ ምንም የተገለጸ ነገር የለም ብለዋል።

" ከዚህም በተጨማሪ በደብዳቤም በስልክም ለማናገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም " ሲሉ ገልጸዋል።

የአየር ቀጠናውን አስመልክቶ ጥያቄ የቀረበላቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚው አሁን ባለው ሁኔታ በኤርትራ የአየር ክልል መብረር እንዳልተከለከሉ ገልጸው የሚያስገድድ ጉዳይ ካለ ግን አማራጭ መጠቀም እንደሚችሉ አንስተዋል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#UPDATE

በኤሌክትሪክ አገልግሎት ታሪፍ ላይ የተደረገው ማስተካከያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሰኔ 13/2016 ዓ.ም መጽደቁ ይታወሳል።

ይህ ተከትሎ  የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አግልግሎት የታሪፍ ማሻሻያው ከመስከረም 1/2017 ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ሽፈራው ተሊላ የታሪፍ ጭማሪው የደንበኞችን የኃይል የአጠቃቀም መሰረት ያደረገ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም፦

የቤት ደንበኞች፤ የንግድ ተቋማት፤ ዝቅተኛ ኢንዱስትሪ፤ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ እንዲሁም የመንገድ መብራት ተጠቃሚዎች በሚል መከፋፈሉን አስታውቀዋል።

የቤት መብራት ተጠቃሚዎችን በተመለከተ " እንደ አጠቃቀማቸው አሁን ከሚከፍሉት እና ጭማሪ ከተደረገበት መካከል ያለውን ልዩነት ሲከፍሉ እንደ አጠቃቀማቸው ድጎማ ተደርጓል " ሲሉ አስረድተዋል።

ድጎማው ምን ይመስላል ?

50kW በታች ለሚጠቀሙ ደንበኞች ያለውን ልዩነት 75 በመቶ የሚሆነውን ይደጎማሉ፤

ከ50kW - 100KW ለሚጠቀሙ ደንበኞች ያለውን ልዩነት 40 በመቶ የሚሆነውን ይደጎማሉ፤

200kW - 300 Kw ለሚጠቀሙ ደንበኞች ያለውን ልዩነት 4 በመቶ የሚሆነውን ይደጎማሉ፤

400kW - 500 KW የሚሆነውን ማሻሻያውን ያለምንም ድጎማ ይከፍላሉ

ከ500kW በላይ የሚሆነውን ደግሞ ሌላውን ተጠቃሚ የሚደግፉበት የጎንዮሽ ድጎማ ሥርዓት ተግባራዊ ይደረጋል።

የአከፋፈሉ ሁኔታ ምን ይመስላል ?

እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ ይህ የተደረገው የታሪፍ ማሻሻያው (የተጨመረው 6 ብር) የሚከፈለው በአንድ ጊዜ ሳይሆን በ16 ዙር በሚደረግ የሂሳብ ማስተካከያ [ከመስከረም 1 /2017 ጀምሮ] በአራት ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሆነ ገልጸዋል።

ኢንጂነር ሽፈራው ይሄንን ሲያስረዱ 50KW የሚጠቀሙ ደንበኞች አሁን የሚከፍሉት 27 ሳንቲም እንደሆነ ገልጸው ከመስከረም ጀምሮ የሚከፍሉት 35 ሳንቲም ይሆናል ብለዋል።

ከአራት ዓመታት በኋላ ደግሞ [በ16 ዙሮች በሚደረግ ማስተካከያ] 1.56 ብር መክፈል ይጀምራሉ ሲሉ አስረድተዋል።

ከኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ ያለው ጫና ተጠንቷል ወይ ?

ይህ ጥያቄ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከጋዜጠኞች የቀረበላቸው ሲሆን በሰጡት ምላሽ በዚህ ላይ ጥናት መደረጉን ጠቅሰው ይህም #ከአራት_ዓመት በኋላ የሚኖረው ተጽዕኖ 2 በመቶ እንደሆነ አንስተዋል።

" ከአከራይ ተከራይ ጋር ያለው ተጽዕኖም በጣም አነስተኛ ነው፤ የሚያጣላቸው ነገር አይኖርም " ሲሉ አስረድተዋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው አክለው ይህ የታሪፍ ማሻሻያው በዋነኛነት የወጣበትን ወጪ ለመሸፈን (A cost reflective tariff) መሰረት ያደረገ መሆኑን አንስተዋል።

#ማብራሪያ: ከላይ የተያያዘው ሰንጠረዥ ድጎማ የተደረገበት የሂሳብ ታሪፍ ሲሆን። በዓመት 4 ጊዜ በ4 ዓመት ደግሞ 16 ጊዜ የሚተገበር የሂሳብ ማስተካከያ የያዘ ነው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray አቶ ጌታቸው ረዳ የጤና አክል ገጥሟቸዋል። ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት ዛሬ ጳጉሜን 2/2016 ዓ.ም የወጣ መግለጫ እንዳመለከተው ፥ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት ዛሬ በአክሱም ሊካሄድ የታቀደው ህዝባዊ ውይይት ተሰርዟል። ፅ/ቤቱ ፕሬዜዳንቱ ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት ከአክሱም ከተማና አከባቢዋ ነዋሪዎች ጋር ሊካሄድ እቅድ የተያዘለት…
#UPDATE

" የጤናዬ ሁኔታ ብዙ የሚያሳስብ አይደለም " - አቶ ጌታቸው ረዳ 

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ ጳጉሜን 2/2016 ዓ.ም በ X ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሑፍ የአዲስ ዓመት መልካም ምኞት በማስቀደም " የጤንነት ሁኔታየና ድህንነቴ ያሳሰባችሁና ያስጨነቃችሁ ሁላችሁም ደህና ነኝ " ብለዋል። 

" ተደጋጋሚ ረጅም መንገድ በመኪና መጓዝና ደካም ተደራርቦ የፈጠረው ጊዚያዊ ችግር እንጂ በሚያሳስብ ሁኔታ እንዳልሆንኩ በፈጣሪና በፅዮን ማርያም ስም እገልፅላችኃለሁ " ሲሉ ፅፈዋል።   

ቀጣይ ህዝባዊ መድረኮች ከተወሰኑ ቀናት በኋላ እንደሚቀጥሉ የገለፁት አቶ ጌታቸው " በመድረኩ ለመሳተፍ አክሱም ድረስ ለተንገላቱ ተሳታፊዎች ደግሜ ይቅርታ እጠይቃለሁ " በማለት አክለዋል።   

ዛሬ ጳጉሜን 2/2016 ዓ.ም ከጊዚያዊ  አስተዳደሩ የፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት የወጣ መግለጫ ፕሬዜዳንቱ የጤና እከለ እንደገጠማቸው በመግለፅ በአክሱም ከተማ ሊካሄድ እቅድ የተያዘለት ህዝባዊ ውይይት ለሌላ ጊዜ መተላለፉና ይቅርታ መጠየቁን መዘገባችን ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግር እና ወከባ ፈጥረዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን የግዜ ቀጠሮ ፈቅዷል። ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው በጠበቆቻቸው አማካኝነት ጠይቀዋል። ፍርድ ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል። የፖሊስን የምርመራ…
#Update

ፍ/ቤት የክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቀደ።

" የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል ፤ የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግር እና ወከባ ፈጥረዋል " ተብለው የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦች ላይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ክስ መመስረቻ ጊዜ መፍቀዱ ተሰማ።

የፌደራል መርማሪ ፖሊስ የምርመራ ቡድን፦
- ዮሃንስ ዳንኤል
- አማኑኤል መውጫ፣
- ናትናኤል ወንድወሰን፣
- ኤልያስ ድሪባ፣
- ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ በተባሉ ግለሰቦች ላይ ሲያከናውን የቆየውን የምርመራ ማጣሪያ ስራ አጠናቆ መዝገቡን ለዐቃቤ ሕግ ማስረከቡን አስታውቋል።

የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ በችሎት ተሰይሞ የምርመራ መዝገቡን ከፖሊስ ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም መረከቡን ጠቅሶ፤ ማስረጃ ተመልክቶ ክስ ለማቅረብ እንዲያስችለው ክስ ለመመስረቻ ጊዜ 5 ቀን እንዲሰጠው ጠይቋል።

የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች " ዐቃቤ ህግ ምርመራውን ሲመራ ቆይቶ እንደአዲስ መዝገቡን ተመልክቼ ክስ ለመመስረት፣ ለመወሰን እንዲያስችለኝ የክስ መመስረቻ ጊዜ ይሰጠኝ ማለቱ " ተገቢ አይደለም በማለት ተከራክረዋል።

ጠበቆቻቸው ደንበኞቻቸው ተጨማሪ ጊዜ በእስር ሊቆዩ እንደማይገባ ገልጸው፤ የዋስ መብታቸው እንዲከበር ጠይቀዋል።

የግራ ቀኝ ክርክሩን የመረመረው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ዐቃቤ ህግ ክስ የመመስረቻ ጊዜ መፍቀድ ስነ ስርዓታዊ መሆኑን በማመን የተጠርጣሪዎችን የዋስትና ጥያቄ በማለፍ ለዐቃቤ ህግ የ5 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ መፍቀዱን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

በዚህም መስከረም 3 ቀን 2017 ዓ/ም ክስ ይመሰረታል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" እንደ ባሪያ ነው የምንታየው ፤ እባካችሁ ጭሁልን !! " - በማይናማር የሚገኙ ወጣቶች ማይናማር እና ታይላንድ ድንበር ላይ ከሚገኙ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የበየነ መረብ ማጭበርበር (Online Scam) ተግባራት ከሚፈጸምባቸው አንዳንድ ቦታዎች ቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክቶችን በቴሌግራም እየተቀበለ ይገኛል። እነዚህ ቦታዎች ላይ በርካታ የሀገራችን ወጣቶች ያሉ ሲሆን " ታይላንድ እንልካችኋለን " በሚል…
#Update

° " ብዙ አካላቸው የጎደለ ሰዎች አሉ፡፡ አካል እስከ ማጉደል ድረስ ነው ቅጣቱ " - ኢትዮጵያዊያን በማይናማር

° " መረጃው ትክክል ነው፡፡ ዜጎች ችግር ላይ ናቸው ተቋሙም ኃላፊነት ወስዶ ለወገኖቻችን ለመድረስ ጥረት እያደረገ ነው " - ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር

በማይንማርን ጨምሮ በአካባቢው የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን በከፋ ችግር ውስጥ እንደሆኑ ከወራት በፊት በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ድምጻቸውን አሰምተው እንደነበር ይታወሳል።

አሁንም ኢትዮጵያውያኑ የኢትዮጵያ መንግስት እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።

መጀመሪያ ከአገር ሲወጡ የተዋዋሉት የሆቴል ቤት ሥራ አስኪያጅ፣ ሀኪም እና የመሳሰሉትን ሥራዎች ሊሰሩና ዳጎስ ያለ ክፍያ ሊፈጸምላቸው እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

ይሁን እንጅ ከዚያ ከደረሱ በኋላ ሽፍታ ወዳለበት የማይናማር ክልፍ እንደወሰዷቸው፣ ጭራሽ ደመወዝ እንደማይፈጽሙላቸው ፣ ከውላቸው ውጪ ዶላር ማጭበርበር እንደሚያሰሯቸው አስረድተዋል፡፡

የሌሎች አገር ዜጎች በአገራቸው መንግስት አማካኝነት እየተለቀቁ ቢሆንም ኢትዮጵያዊያኑ ግን የከፋ ስቃይ ውስጥ እንደሆኑ ገልጸው መንግስት እንዲደርስላቸው በአንክሮ ጠይቀዋል፡፡

ቤተሰቦቻቸው በበኩላቸው፣ መንግስት የልጆቻቸውን ሕይወት እንዲያተርፍላቸው ተማጽነዋል፡፡

ኢትዮጵያዊያኑ በዝርዝር ምን አሉ ?

" እያንዳንዱ ሰው የግድ በቀን 17 ሰዓት መስራት አለበት፡፡ የተሰራበት ደመወዝ ግን አይከፈልም፡፡ ገቢ ካላስገባ ቅጣት አለ፡፡ አለንጋም አላቸው ይገርፋሉ፡፡ ጨለማ ቦታ ላይ ወስደውም ያስራሉ፡፡

በአንድ ጊዜ ሦስት 20፣ 20 ሊትር ጀሪካን ያሸክማሉ፡፡ ሁለቱን በሁለቱ ትክሻቸው፣ አንዱን በእግርና እግር መካከል እንዲሸከሙ የሚገደዱ ኢትዮጵያዊያን አሉ፡፡

በተጨማሪ ብዙ ሰዎች ባሉበት አካባቢ ፊት ለፊት እንደ ማሳያ ተደርገን እንገረፋለን፡፡ በቀን አምስት ሰዓት ብቻ ነው የሚታረፈው፡፡

እጅና ኮምፒዩተር ለአፍታ ከቦዘኑ፣ የሆነ ስህተት ከተሰራ ድብደባ አለ፡፡ ምንም ነጻነት የሌለበት አገር ነው፡፡

ብዙ አካላቸው የጎደሉ ሰዎች አሉ፡፡ አካል እስከማጉደል ነው ቅጣቱ፡፡ እግራቸው፣ እጃቸው፣ ሁሉ ነገራቸው የተጎዳ ሰዎች አሉ " ሲሉ አስረድተዋል።

ኢትዮጵያዊያኑን ካሉበት የከፋ ችግር ለማውጣት ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ ያቀረብንላቸው  የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ ለጉዳዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

" በማይናማር የሚገኙ ዜጎቻችን ጉዳይ ይታወቃል፡፡ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል በተለይ ሳወዝ ኤዢያ ካሉ ኤምባሲዎቻችን ውስጥ አንዱ ጃካርታ ነው፤ ኢንዶኖዢያ፡፡ ጉዳዩ እነርሱም ደርሷቸው እየጠከታተሉ ነው " ብለዋል።

" ይሄ መስመር በአጠቃላይ እንደ አዲስ የሕገ ወጥ ፍልሰት መንገድ ሆኖ ነው እየታዬ ያለው፡፡ እስከሁን ባልተለመደ ሁኔታ ወደዚህ አቅጣጫ ከዚህ ቀደም ከምናውቃቸው ትንሽ ወጣ ያለ ነው። ጉዳዩም ጥናት የሚፈልግ ሆኖ ነው የተገኘው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡

" ዜጎች የትም አገር፣ የትም ቦታ ይሁኑ የመጀመሪያው መዳረሻ ችግራቸውን ለመፍታት ውጪ ጉዳይ እንደመሆኑ መጠን ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ክትትል እየተደረገበት ነው " ብለዋል።

ኢትዮጵያዊያኑ የአካል ጉዳት ጭምር እየደረሰባቸው በመሆኑ በፍጥነት እንዲደረስላቸው እየጠየቁ እንደመሆኑ  ከኤምባሲዎቹ ጋር ያለው ንግግራችሁ ተስፋ አለው ? በምን ደረጃ ላይ ነው ? የሚል ጥያቄ ቲክቫህ ለአምባሳደሩ አቅርቧል።

አምባሳደሩ በምላሻቸው፣ " እንደ አጋጣሚ ሆኖ ኢትዮጵያ ማይናማር ውስጥ ኤምባሲ የላትም፡፡ ምንም አይነት ዲፕሎማሲክ ውክልና የለንም " ብለዋል።

" ስለዚህ ከእርቀት ሆነው ነው ይህን ነገር የሚከታተሉት፡፡ መረጃው ትክክል ነው፡፡ ዜጎች ችግር ላይ ናቸው። ተቋሙም ኃላፊነት ወስዶ ለወገኖቻችን ለመድረስ ጥረት እያደረገ ነው " ሲሉ አክለዋል።

በችግር ላይ እንደሆኑ የሚነገርላቸው
ከ3000 በላይ ኢትዮጵያዊያን እንደሆኑ ነው፡፡ ተቋምዎስ ስንት እንደሆኑ ያውቃል? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄም ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

" ቁጥር ልንሰጥ አንችልም፡፡ ነገር ግን ቁጥራቸው 3000ም ሆኑ ሦስት ኢትዮጵያዊያን ችግር ላይ እስካሉ ድረስ ችግራቸው ችግራችን ሆኖ ተቋሙ ዜጎችን ለመታደግ ይንቀሳቀሳል " ነው ያሉት።

ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ክስ ተመሰረተባቸው። " የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል " በተባሉ 6 ግለሰቦች ላይ በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ክስ ተመሰረተ። የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ የመሰረተው ክስ ምን ይላል ? - አውሮፕላንን ያለአግባብ መያዝ ወንጀል፣ - የመንግስት ሰራተኛ የስራ ግዴታውን እንዳይፈጽም መቃወምና አለመታዘዝ የሚል…
#Update

የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ ተደርጎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዘዘ።

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ደህንነት ጋር ተያይዞ ክስ የቀረበባቸው 6 ግለሰቦች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደረገ።

ግለሰቦቹ ፦
- ዮሃንስ ዳንኤል
- አማኑኤል መውጫ፣
- ናትናኤል ወንድወሰን፣
- ኤልያስ ድሪባ፣
- ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ናቸው።

ዐቃቤ ህግ በ6ቱ ግለሰቦች ላይ የወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።

የቀረበባቸው ክስ ለተከሳሾች ከደረሰ በኋላ በተከሳሾች ጠበቆች በኩል ደንበኞቻቸው " የተከሰሱበት ድንጋጌ በመርህ ደረጃ ዋስትና ሊያስከለክል አይችልም " በማለት የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድ ጠይቀዋል።

ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ፤ የወ/መ/ስ/ህግ ቁጥር 67/ለ ጠቅሶ በልዩ ሁኔታ ዋስትና ሊያስከለክል ስለሚችል በሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም የተሰጠባቸው ማለትም ፦
➡️ ከወንጀሉ ከባድነትና ከክሱ ተደራራቢነት፣
➡️ ከጉዳዩ ባህሪና ከከባቢያዊ ሁኔታዎች አንጻር ዋስትና ሊያስከለክሉ የሚችሉበትን ትርጉም የተሰጠባቸው የሰበር ሰሚ ችሎት መዝገብ ቁጥሮችን ጠቅሶ የዋስትና መብታቸው እንዲታለፍ ጠይቆ ነበር።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ወንጀል ችሎት የግራ ቀኝ የዋስትና ክርክሩን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለዛሬ በሰጠው ቀጠሮ መሰረት ብይን ሰጥቶበታል።

በዚህም ተከሳሾቹ ከቀረበባቸው ተደራራቢ ክስ አንጻር ቢወጡ የዋስትና ግዴታቸውን አክብረው ሊቀርቡ አይችሉም በማለት የጠየቁት የዋስትና ጥያቄን ውድቅ ተደርጎ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዟል።

ክሱን ለመመልከትም ለጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ተቀጥሯል፡፡ #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

° “ ልጆቻችን ችግር ላይ ናቸው የኢትዮጵያ መንግሥት በሕይወታቸው ይድረስልን ” - በማይናማር ያሉ ኢትዮጵያን ቤተሰቦች

° “ የእኛ ኤምባሲ ከዛ አገር መንግስት ጋር እየተነጋገረ ልጆች የሚመለሱበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እየተሞከረ ነው ” - የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጭ (ባለሥልጣን)

በማይናማር የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ፦
➡️ ከአገር ሲወጡ በተዋዋሉት መሠረት ሳይሆን በተቃራኒው ህገወጥ የማጭበርበር ተግባር ላይ እንዲሰማሩ እንደተገደዱ፣
➡️ በአግባቡ ደመወዝ እንደማይከፈላቸው፣
➡️ ይባስ ብሎ ድብደባ እየተፈጸመባቸው አካላቸው እስከመጉደል እንደደረሱ በቤተሰቦቻቸው ጭምር በቲክቫህ ኢትዮጵካ በኩል መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

በወቅቱ ስለጉዳዩ ምላሽ የጠየቅናቸው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ “ መረጃው ትክክል ነው፡፡ ዜጎች ችግር ላይ ናቸው ተቋሙም ኃላፊነት ወስዶ ለወገኖቻችን ለመድረስ ጥረት እያደረገ ነው ” የሚል ምላሽ ሰጥተውን ነበር፡፡

በማይናማር የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን አሁንስ ቤተሰቦች ምን አሉ ?

“ ልጆቻችን ችግር ላይ ናቸው የኢትዮጵያ መንግሥት በሕይወታቸው ይድረስልን፡፡ ትንሽ ክፍተት አግኝተው ደውለው ሲነግሩን የከፋ ችግር ውስጥ እንደሆኑ ነው የሚያስረዱን፡፡ ተጨነቅን እኮ!

በእርግጥ የኢትዮጵያ መንግስት ጥረት እያደረገ እንደሆነ ሰምተናል፡፡ ግን ልጆቻችን በዬቀኑ ድብደባና እንግልቱ እየከበደባቸው ነውና መንግስት በቻለው መጠን ተነጋግሮ ወደ አገራቸው እንዲገቡ እንድያደርግልን እንማጸናለን፡፡

መንግስትንም ለማጣደፍ የተገደድነው የወላጅ አንጀት አልችል ቢለን ነው፡፡ ልጆች በባዕድ አገር በእንዲህ አይነት የከፋ ችግር ውስጥ ሆነው ማየት ሀዘኑ መራራ እንደሆነ የወለደ ሁሉ ያውቀዋል ” ብለዋል።

በችግር ላሉት ኢትዮጵያዊያን ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ ያቀረብንላቸው አንድ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉና ጉዳዩን ከጅምሩ ጀምሮ የሚያውቁት ባለሥልጣን በበኩላቸው ተከታዩን ምላሽ ሰጥተውናል፡፡

“ ኢትዮጵያ እንደ አገር እዛ አካባቢ ካሉ አገራት ጋር የሥራ ስምሪት ስምምነት የላትም፡፡ ስለዚህ ልጆቹ በግላቸው ነው የሄዱት፡፡ ማንኛውም ሰው ለሥራ የመንቀሳቀስ መብት አለው፡፡ ከዛ አኳያ ሂደዋል፡፡

ነገር ግን ዜጎች ችግር ላይ ሲወድቁ መንግስት ዝም ብሎ ስለማይመለከት የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን ከሰማ ጀምሮ እየሰራ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊያኑ የሚሄዱት በታይላንድ በኩል ነው፡፡ ጉዳዩን የሚከታተሉት ህንድና ጃፓን ያሉት የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ናቸው፡፡

ከዚህ ቀደም ታይላንድ ላይ ታግተው የነበሩ ኢትዮጵያዊያንን ማስመለስ ተችሏል፡፡ እኛም የሥራ ስምሪት ወደ እዛ አገር ስለሌለ ዜጎች ወደዛ ባይሄዱ ይመረጣል የሚል መልዕክት ሰጥተናል፡፡

መሄዳቸው ልክ አይደለም ብቻ ሳይሆን ኃላፊነትም መውሰድ መቻል አለባቸው፡፡ ችግር ሲያጋጥም ብቻ መንግስት ላይ መጮህ ተገቢ አይደለም፡፡

ግን እዛ አካባቢ ተቸግረው የነበሩ ልጆችን መንግስት አስመልሷል፡፡ ነገር ግን ወደ ማይናማር የተሻገሩ አሉ፡፡ ወደ ማይናማር የተሻገሩት የሄዱበት ቦታ አስቸጋሪና ታጣቂዎች ያሉበት ቦታ ነው፡፡ የእኛ ኤምባሲ ከዛ አገር መንግስት ጋር እየተነጋገረ ልጆች የሚመለሱበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እየተሞከረ ነው። ” ብለዋል፡፡

የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በበኩላቸው ከዚህ ቀደም ከሰጡን ማብራሪያ በተጨማሪ፣ “ በተለይ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ፣ ወደ ደቡብ አፍሪካ መስመር ነበር የተለመዱት፡፡ አሁን ደግሞ ባልተለመደ ሁኔታ በጣም አዲስ ነገር ነው ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

“ ሕገ ወጥ ሰዎች ዝውውር በተለይ በደላሎች አማካኝነት ለአደጋ የሚያጋልጥ እንደሆነ ማንኛውም ዜጋ በተለይ ወደ ውጭ አገር ሲንቀሳቀሱ መጠየቅ፣ ማጣራት ያስፈልጋል ” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የሆነው ሆኖ ግን ውጪ ጉዳይ ኢትዮጵያዊያኑ ካሉበት ችግር እንዲወጡ እየሰራ መሆኑን አመላክቷል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia