#Update
የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግር እና ወከባ ፈጥረዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን የግዜ ቀጠሮ ፈቅዷል።
ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው በጠበቆቻቸው አማካኝነት ጠይቀዋል።
ፍርድ ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል።
የፖሊስን የምርመራ ውጤት ለመጠባበቅ ለጳጉሜ 4 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።
@tikvahethiopia