TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የቀን ማስተካከያ፦

#StopHateSpeech በዚህ ሳምንት የሚደረጉት መድረኮች ላይ የቀን ማስተካከያ ተደርጓል። በዚህም መሰረት፦

#ረቡዕ የጉዞ መነሻ ከሀዋሳ፣ወልቂጤ፣ ከአርባ ምንጭ፣ ከወ/ሶዶ ከተሞች --- #ደብረ_ብርሃን ይታደራል።

√ሀሙስ - ወሎ ዩኒቨርሲቲ ከTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ጋር ውይይት ይደረጋል።

√አርብ - ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ከTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ጋር ውይይት ይደረጋል።

√ቅዳሜ - መቐለ ዩንቨርስቲ ልዩ ዝግጅት ተዘጋጅቷል።

አዲስ ነገር...👇

በዚህ ዘመቻ ላይ በወጣቶች ብቻ የተመሰረተ የሙዚቃ ባንድ ይቀላቀለናል፤ በረቂቅ ሙዚቃም ፍቅር እና ሰላምን ይሰብካሉ። እንዲሁም በሴቶች ላይ ስለሚነገሩ እና ስለሚሰነዘሩ የጥላቻ ንግግሮች ግንዛቤ ለመስጠት #መራሂት እና #ያንቺ_ንቅናቄ በሴቶች ላይ የሚሰሩ ቡድኖች አብረውን ይጓዛሉ።


@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ደብረ_ብርሃን_ዩኒቨርሲቲ

ተመራቂዎች በኢትዮጵያ እየታዬ ያለውን የሰላም መደፍረስ እና ዘረኝነት እንዲታገሉ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ አሳሰበ፡፡ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ለተከታታይ ሶስትና ከዚያ በላይ ዓመታት ያሰለጠናቸውን ከ3 ሺህ በላይ ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በመደበኛ እና በተከታታይ መርሀ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 3 ሺህ 64 ተማሪዎች ማስመረቁ ታውቋል፤ 1 ሺህ 226 የሚሆኑት ደግሞ ሴቶች ናቸው፡፡

የዩኒቨርሲቲው ተወካይ ፕሬዝዳንት ዶክተር ደረጀ አንዳርጌ ተመራቂዎች ያካበቱትን እውቀት ተጠቅመው ሕዝባቸውን እና ሀገራቸውን በታማኝነት እና በቅንነት እንዲያገለግሉ መልዕክት አስተላፈዋል፡፡

በኢትዮጵያ እየታዬ ያለውን የሰላም መደፍረስ እና ዘረኝነት ለመታገልም በቁርጠኝነት መስራት እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል፡፡ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የዘንድሮውን ሳይጨምር ከ26 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ማስመረቁ ታውቋል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
🎂TIKVAH ETHIOPIA~2 ዓመት🎂

#ደብረ_ብርሃን #ወሎ #ጅማ #ሀረማያ #ሀዋሳ #ወልቂጤ #መቐለ #ወልዲያ #ወላይታ_ሶዶ #አርባምንጭ #ሆሳዕና/#ዋቸሞ/

📎የሰውልጅ በሰውነቱ የሚከበርበት፤ የግለሰቦች አመለካከት፣ እምነት፣ ባህል፣ ቋንቋ፣ የኔ ነው የሚሉት ሁሉ የሚከበርበት፤ ፍቅር፣አንድነትና መተባበር የነገሰበት፣ የሰው ልጅ ሁሉ መሰብሰቢያ የሆነች ከጥላቻ የራቀች ሀገር እንገነባለን!! ተባብረን እንሰራለን፤ ለመጭው ትውልድ ኢትዮጵያን እናወርሳለን!!

እኛ ስንኖር ኢትዮጵያ ትኖራለች፤ ኢትዮጵያ ስትኖር እኛም እንኖራለን!

#ድፍን_ሁለት_ዓመት_በፍቅር_በመተባበር!

ነገ 6:00 አበበች ጎበና የህፃናት እንክብካቤ እና ልማት ድርጅት እንገናኝ፤ ከእናታችንም ምርቃት እንቀበል!! ሁላችሁም የዚህ ገፅ ባለቤቶች ናችሁ!!

@tsegabwolde @tikvahethiopia