TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#አዲስአበባ #መታወቂያ “ የትምህርት ቤት ምዝገባው ሲጠናቀቅ አገልሎቱን መስጠት እንጀምለራለን ” - CRRSA ከክልል ከተሞች መሸኛ ይዘው አዲስ አበባ ከተማ ለመጡ ተገልጋዮች የመታወቂያ አገልግሎት “በጣም በአጠረ ጊዜ ውስጥ እንጀምራለን” መባሉን ከወራት በፊት ነግረናችሁ ነበር። አሁንስ ጉዳዩ ከምን ደረሰ ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ አገልግሎቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደምትሰጡ ከዚህ ቀደም ገልጻችሁ ነበር፤…
መታወቂያ መስጠት መቼ ይጀመራል ?

" አሁን ማጣራት ጀምረናል የገቡትን መረጃዎች፣ አሰራሮችና ማኑዋሎች ጭምር ተዘጋጅቷል " - CRRSA

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከክልል ከተሞች መሸኛ ለሚያመጡ ዜጎች የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪነት መታወቂያ መስጠት መቼ እንደሚጀምር ጠይቀነው የሰጠንን ምላሽ በተደጋጋሚ አድርሰናችሁ ነበር።

ኤጀንሲውን ከዚህ ቀደም አገልግሎቱ መቼ ይጀመራል ? ብለን ጠይቀን በሰጠን ምላሽ፣ በጣም ባጠረ ጊዜ ውስጥ እንደሚሰጥ ገልጾ ነበር።

ከቆይታ በኋላ ላቀረብንለት ተመሳሳይ ጥያቄ ቀሰጠው ምላሽ፣ " የትምህርት ቤት ምዝገባ ሲጠናቀቅ አገልግሎቱን መስጠት እንጀምራለን " ነበር ያለው።

የትምህርት ቤት ምዝገባው ሲጠናቀቅ መቼ መሰጠት እንደሚጀመር በወቅቱ ስንጠይቅም፤ ከነሐሴ አጋማሽ 2016 ዓ/ም በኋላ እንደሚሰጥ መግለጹ አይዘነጋም።

አሁንስ አገልግሎቱ መሰጠት ተጀመረ ?

አሁንስ አገልግሎቱን መስጠት ተጀምሯል ? ስንል የጠየቅናቸው አንድ የኤጀንሲው አካል፣ " ገና ነው፡፡ በቅርብ ጊዜ የሚጀመር ይመስለኛል፡፡ ግን ገና ነው " ብለዋል።

ከዚህ ቀደም ከነሐሴ አጋማሽ በኋላ አገልግሎቱን እንደምትሰጡ ገልጻችሁ ነበር ብለን አስታውናቸዋል።

እኝሁ አካልም፣ " አዎ። አሁን ማጣራት ጀምረናል የገቡትን መረጃዎች፣ አሰራሮችና ማኑዋሎች ጭምር ተዘጋጅቷል፡፡ ገና መስጠት አልተጀመረም " ነው ያሉት።

አሁንስ መቼ መሰጠት ይጀምራል ? ስንል ጠይቀናቸው በሰጡት ምላሽ፣ እሳቸው ትክክለኛ ቀኑን እንደማያውቁት አስረድተዋል።

አክለውም፣ " መቼ ቀን እንደሚጀመር እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ በቅርብ ጊዜ ሊጀምር እንደሆነ እርግጠኛ ነኝ "  ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹 “ ... ያለፉትን ዘመናት እኮ #እንደ_ቅንጦት እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው ” - ጎጎት ፓርቲ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ' #የፖለቲካ_ፓርቲዎች_ምን_ይላሉ ? ' በሚል በህጋዊ መንገድ ተመዝገበው ለሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እያቀረበ ያለውን ወቅታዊ ሀገራዊ ጥያቄዎች በመቀጠል ጎጎት ፓርቲን አነጋግሯል። የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ጀሚል ሳኒ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ…
🇪🇹 የፓለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹

“ ሰው በጣም እየተሰቃዬ ነው ያለው መንግስት ኃላፊነቱን መወጣት አለበት ” - ወህዴግ

የወላይታ የህዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ወህዴግ) ፓርቲ አመራር አባል አቶ ተክሌ ቦረና ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

Q. በተለይ የእርስዎ ፓርቲ በሚንቀሳቀስበት አካባቢ ከደመወዝ አለመከፈልና መቆራረጥ ጋ በተያያዘ ሠራተኞች ተማረዋል። ችግሩ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል ? ያላችሁ ግምገማስ ምንድን ነው ?

አቶ ተክሌ፦

“ የደመወዝ ቅሬታ ቅሬታ ሆኖ እስከሚቀርብ መጠበቅ የሌለበት አግባብነት የሌለው ጉዳይ ነው።

ምክንያቱም በዓመቱ መጀመሪያ የደመወዝ በጀት በሠራተኞች ልክ ተሰልቶ ይመደባል በመንግስት።

ግን አዲስ የሰው ኃይል ሳይጨመር በነበረው ሆኖም የተወሰነ ርቀት እንደተሄደ ‘ ደመወዝ የለም ’ የሚያሰኝ ነገር ምን እንደሆ አሳማኝ ነጥብ የለም።

ምናልባት ከደቡብ የክልል አከላለል ጋር ተያይዞ ሠራተኞች ከቦታ ቦታ ይዘዋወራሉና ደመወዝ ከፋዮቹ በዚያ ለማሳበብ ይሞክሩ ይሆናል። 

እሱም ቢሆን ሠራተኞች የሚያገኙትን ደመወዝ ይዘው ይሄዳሉ እንጂ አዲስ ስጡን ብለው አይጠይቁም።

በመሆኑም እንዲህ አይነት ችግር የሚያስከትሉ ሰዎች ምክንያታቸው አጥጋቢ አይደለም።

አንዳንዴ ‘ ከማዳበሪያ ዋጋ ጋር ተገናኝቶ ’ የሚባል ነገር አለ። በምንም ተዓምር የደመወዝ በጀት ቆርሶ ለሌላ ጥቅም ማዋል አይገባም በአገሪቱ ህግ መሠረት። 

ለምን እንደዚህ እንደሚደረግ አይገባንም። ”

Q. የደመወዝ መቆራረጥ ድሮውንም የናረውን የኑሮ ውድነት ለሠራተኞቹ ይበልጥ ፈታኝ እንዳደረገው ስሞታ ይቀርባል። የፓርቲዎ ግምገማና መልዕክት ምንድን ነው ?

አቶ ተክሌ፦

“ በህጉ መሠረት ሠራተኛው ሳይስማማ፣ ፈርሞ ሳያጸድቅ ከደመወዙ አንድ ሳንቲም አይነካም። ደመወዝ ከፋይ እኔ ነኝ እንደፈለኩ አደርጋለሁ የሚል ኃይል አይኖርም።

ያለ ፈቃድ የሚደረግ ነገር በሙሉ ህገወጥ፤ እንደ ወንጀል የሚቆጠር ነው። የሰውን ገንዘብ ቀምቶ እንደመውሰድ ነው።

ደመወዝ ባይቆረጥም የኑሮ ውድነቱ ከደመወዝ ጋር የሚመጣጠን ባለመሆኑ ሠራተኛው ሊቋቋመው አልቻለም። በየሰዓቱ የዋጋ ጭማሪ አለ።

ሰው በጣም ተቸግሮ ነው ያለው። በጣም አስፈላጊ የሆኑትን ፍላጎቶች በማሟላት ብቻ እያብቃቃ ነው የሚኖረው። 

የዋጋ ንረትና የደመወዝ ሁኔታ በምንም ተዓምር ለጎን ለጎን የሚሄዱና ንግግር ውስጥ የሚገቡ ነገሮች አይደሉም። ሰው በጣም እየተሰቃዬ ነው ያለው መንግስት ኃላፊነቱን መወጣት አለበት። ”

Q. ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል አለመወሰን ለኑሮ ውድነቱ መባባስ እንደ መንስኤ ይነሳል። ፓርቲዎስ ያለው ምልከታ ምንድን ነው ?

አቶ ተክሌ ፦

“ ይሄ የመኖርና ያለመኖር ጥያቄ ነው። መንግስት በጣም በተለዬ ሁኔታ ትኩረት ሊሰጠው፣ ሊጸድቅ ይገባል።

ከዚህም ባሻገር መንግስት ምርት መጋዘን እያከማቹ በአንድ ወቅት በማውጣት ዋጋ የሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መውሰድ አለበት።

ችግሩ የ120 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ስለሆነ መንግስት በዬአካባቢው የራሱን ሱቅና መጋዘን ሊከፍት ይገባል። ያኔ ተመጣጣኝ ዋጋ ይኖራል። ”

Q. የተሟላ መሠረተ ልማት አለመኖር ፈታኝ እንደሆነባቸው ነዋሪዎች ሲገልጹ ይስተዋላል። የፓርቲዎ ግምገማ ምን ይመስላል ?

አቶ ተክሌ፦

“ መሠረተ ልማት ይጀመርና ይተዋል። እንደገና 5፣ 6 ዓመታት ከበሰበሰ በኋላ ብዙ ሲገለጽ ይሰማል።

እንዲህ አይነት ችግር በመንገድ፣ በህንፃ ግንባታ በብዙ ቦታዎች  ይስተዋላል።

የመሠረተ ልማት ግንባታ እየተስተጓጎለ ነው። በጀትም በትክክል ሥራ ላይ አይውልም። ስለዚህ ቆምና አሰብ አድርጎ ማስኬድ ያስፈልጋል። ”

Q. እንደ ፓርቲ የሚደርስባችሁ ጫና አለ? ካለ ምንድን ነው?

አቶ ተክሌ፦

“ ጫናው አለ። ለምን ኖረ? የሚለውን ስናይ በተለይ ታች ያሉት የመንግስት ካድሬዎች የሰለጠኑ አይደሉም። 

የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት መኖር ለዴሞክራሲ ስርዓት መዳበር ፋይዳ እንዳለው አያውቁም። ተፎካካሪ ፓርቲዎችን እንደ ጠላት እያዩ ችግር ይፈጥራሉ።

ችግር የሆነብን ይሄ ነው። ስለዚህ መንግስት ታች ወርዶ ከወረዳ እስከ ዞን መስራት አለበት።”

Q. ስለሙስና የፓርቲዎ ግምገማ ቢያጋሩ?

አቶ ተክሌ፦

“ የሙስና ጉዳይ በጣም እድሜ ያስቆጠረ ነው። 
በኢትዮጵያ በኮሚሽን ደረጃ ተቋም ተደራጅቶ ኃላፊነት ወስዶ በመስራት ላይ እንዳለ ነው የምንሰማው ነገር ግን ችግሩ አልተቀረፈም።

አሁንም ጠንካራና የተሻለ ሲስተም መዘርጋትና መቆጣጠሮ ያስፈልጋል። በሌላ በኩል የህዝቡ የኑሮ ውድነት ቢቀረፍ ሁሉም ስለሚዋጋ ችግሩ እየሟሸሸ ይሄዳል ” ብለዋል።

#የፓለቲካፓርቲዎችምንይላሉ? #ወህዴግ

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Urgent🚨 በአማራ ክልል፣ በሰሜን ጎንደር ዞን ፣ ጠለምት ወረዳ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት የበርካታ ወገኖቻችን ህይወት አልፏል። በርካቶችም ችግር ላይ ወድቀዋል፤ ተፈናቅለዋል። ለተፈናቃዮቹ አስቸኳይ ድጋፍ ያስፈልጋል። ደጋግ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ድጋፍ እንዲያደርጉ ወረዳው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርቧል። የወረዳው አስተዳደሪ አቶ ጋሻው እንግዳው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ቃል ፦ “…
#ጠለምት🚨

“ ናዳው ቀጥሏል፡፡  አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 25 ነው ” - ወረዳው

የመሬት መንሸራተት አደጋው መቀጠሉ የተነገረለት ሰሜን ጎንደር ዞን በተለይ ጠለምት ወረዳ የሟቾች ቁጥር መጨመሩን ወረዳው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎች የተከተው ይሄው አደጋ የብዙዎችን ሕይወት መቀጠፉ የሚታወስ ሲሆን፣ በተለይ በጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ ከመሬት መንሸራተቱ በተጨማሪ በሌሎች ቀበሌዎችም “ የህድሞ ” ቤት ናዳ አደጋ መከሰቱን ወረዳው ከሳምንት በፊት ገልጾልን ነበር፡፡

ይህ በእንዲህ እያለ፣ እስከ ነሐሴ 29 ቀን 2016 ዓ/ም ደግሞ የሟቾች ቁጥር በ15 መጨመሩን የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ጋሻው እንግዳው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

“ ናዳው ቀጥሏል፡፡ በጠለምት ወረዳ የሟቾች ቁጠር 25 ደርሷል ” ነው ያሉት፡፡

አስተዳዳሪው በዝርዝር ምን አሉ ?

“ በወረዳው በሚገኙ ቀበሌዎች በናዳና የጎርፍ አደጋ ምክንያት በሰዎችና በንብረት ላይ ጉዳት እየደረሰ ነው፡፡

ከነሐሴ 18 ቀን 2016 ዓ/ም እስከ ነሐሴ 29 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ ብቻ አራት ወንዶች፣ 11 ሴቶች በአጠቃላይ 15 ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል፡፡

ሁለት ወንዶችና ሁለት ሴቶች በድምሩ አራት ሰዎች ደግሞ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

አደጋው ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ነሐሴ 29 ቀን ድረስ በአጠቃላይ በወረዳው የሞቱ ሰዎች ብዛት 25 ደርሷል፡፡

የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ብዛት ደግሞ 10 ደርሷል፡፡ 456 ሰዎች የእርሻ መሬት ተጎድቶባቸዋል፡፡ 476.5 ሄክታር ሰብል ተጎድቷል፡፡

2911 እንስሳት ሞተዋል፡፡ 28 መኖሪያ ቤቶችና 236 የንብ ቀፎዎች ወድመዋል”
ብለዋል፡፡

የተለያዩ ተቋማት የተለያዩ ድጋፎችን እንዳደረጉ የገለጸው ወረዳው፣ አደጋውና መፈናቀሉ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ በመሆኑ የተጀመረው ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል፡፡

አደጋው የተከሰተው በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ሲሆን፣ በተለይም ጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ የተከሰተው የመሬት መንሸራተት መቆም እንዳልቻለ መገለጹ ይታወሳል፡፡

በዞኑ በሚገኙ ሌሎች ወረዳዎች አደጋው በምን ደረጃ እንደሚገኝ በቀጣይ መረጃ የምናደርሳችሁ ይሆናል፡፡

ፎቶ ፦ ፋይል

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ለጥንቃቄ_ከጠቀማችሁ 1. በአዲስ አበባ ከተማ የሜትር ታክሲ አገልግሎት የምትሰጡ ወንድም እህቶቻችን እባካችሁ ጥንቃቄ አድርጉ። ማክሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ገደማ ወደ ጎተራ ማሰለጫ መውረጃ ወይም በተቃራኒ ወደ ቄራ የሚወስደው መስቀለኛ መንገድ አካባቢ አንድ አገልግሎት ሰጪን 3 ተሳፋሪ መስለው የገቡ ወንበዴዎች መሃል አስፓልት ፣ በብዛት መኪና በሚመላለስበት መንገድ ላይ ከውስጥ እቃ ይዘው ሲሮጡ መመልከቱን…
#AddisAbaba

“ የጫት መቃሚያ ፣ የሺሻ ቤቶች የወንጀል ድርጊት የሚዶለትባቸው ቤቶች ናቸው ” - ፓሊስ

በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ወንጀሎች እንደሚደርሱባቸው ነዋሪዎች ይገልጻሉ፡፡

አንዳንዶቹ እንደሚሉት ከሆነ፣ የጸጥታ አካላት ልብስ ለብሰው ጸጥታ አስከባሪ በመምሰል ወንጀል የሚፈጽሙ አሉ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፦

°  ተመሳስለው ወንጀል የሚሰሩ አካላት ላይ ምን አይነት ክትትል እየተደረገ ነው ?

°  ወንጀል በከተማዋ በምን ደረጃ ይገኛል ?

° ሕዝቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ? ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጠይቋል።

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ?

“ ሌባ የተለያዬ የወንጀል አፈጻጸም ስልት አለው፡፡ አንዱ የጸጥታ አካል መስሎ፣ ልብሱን በተለያዬ አይነት መንገድ ለማግኘት ሙከራ አድርጎና ለብሶ ወንጀል ሊፈጽም ይችላል፡፡

ይሄ በጣም ከበ ሁለት ጥፋት ነው፡፡

አንደኛው ህብረተሰቡ ፖሊስ ሊመስለው ከቻለ በፖሊስ ላይ ያለው አመኔታ ምንም ጥያቄ የለውም ይወርዳል፡፡ ሁለተኛው ጉዳት ደግሞ ወንጀሉ በፖሊስ ላይ ጫና/ሥራ ይፈጥራል፡፡

ስለዚህ ጥንቃቄ ማድረግና መረጃዎች በሚኖሩ ሰዓት ቶሎ መስጠት ያስፈልጋል፡፡

በተለይ በእንደዚህ አይነት ሁኔታዎች የሚፈጸሙ ወንጀሎች በጣም አደገኛ ናቸው፡፡ በጣም በጣም፡፡ ትልቅ ዋጋም የሚያስከፍሉ ናቸው፡፡

ወንጀል ፈጻሚውን በመያዛችን የጸጥታ አካላትን ልብስ ከየት አመጣህ ? ብሎ ለመጠየቅና ተባባሪ የሆነ አካል ካለ ተገቢ እርምጃ ለመውሰድ ምቹ ሁኔታ ይፈጥርልናል፡፡

ወንጀሉ ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድና ለህዝብ ግልጽ በማድረግ በእንደዚህ አይነት ወንጀል የተሰማሩ ሰዎች ሁለት፣ ሦስቴ እንዲያስቡ እናደርጋለን፡፡

ግን ሰው መረጃ በመስጠት ተባባሪ መሆን መቻል አለበት፡፡

መረጃ ማድረስ ብቻ ሳይሆን ፈጣን ማድረስ ነው መሆን ያለበት፡፡ አንዳንድ ጊዜ አንዳንድ ሰዎች ሰው መክሯቸው ' መረጃ ስጡ ' ተብለው ነው የሚናገሩት፡፡ ፈጣን ነው መሆን ያለባቸው፤ እንደዚያ ከሆነ ወዲያው በቁጥጥር ሥር እናውላቸዋልን፡፡

ወንጀሎች ከመፈጸማቸው አስቀድሞ ለመፈጸሙ ምክንያት የሆኑ ነገሮችን አስቀድሞ በማወቅ የማስወገድ ሥራ መሰራት አለበት፡፡

ለምሳሌ ፦ የወንጀል መንስኤ ብለን እኛ የምናያቸው የጫት መቃሚያ፣ የሽሻ ቤቶች የወንጀል ድርጊት የሚዶለትባቸው ቤቶች ናቸው፡፡

በዚህ በኩል ፖሊስ የሚወስደው በጣም ጠንካራ የሆነ እርምጃ አለ፡፡ ግን መረጃ ከመስጠት በኩል አሁንም ክፍተቶች አሉ፡፡ አንዳንዶቹ እንዳውም ለፖሊስ መረጃ ከመስጠት ይልቅ የመደበቅ ሁኔታ አለ፡፡

ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ሆነን ነው የወንጀል መከላከልን ሥራ የምንሰራው፡፡ ግን ግለሰቦቹ ወንጀል ከተፈጸመባቸው ወደ ሚዲያ ሳይሆን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ነው መሄድ የሚጠበቅባቸው፡፡ በትክክል የከተማውን የጸጥታ ሁኔታ ቼክ የምናደርግበትም አግባብ ያ ነው፡፡

ስለዚህ ወንጀል ሰዎች ላይ ሊፈጸም ይችላል፡፡ በተቻለ አቅም በከተማው ላይ የወንጀል ስጋት እንዳይኖር ነው እየተሰራ ያለው፡፡ በ2016 ዓ/ም አጠቃላይ የተቋማችን አፈጻጸም 31 ፐርሰንት ወንጀልን ቀንሰናል፡፡

አዲስ አበባ ትልቅ ከተማ በመሆኗ ለተለያዩ ወንጀል መፈጸሞች ምክንያት የሆኑ ነገሮች ሊያጋጥሙ ይችላሉ፡፡ ከክልል ከተሞችም በብዛት ሰዎች ይመጣሉ፡፡ ሰው ሥራ፣ ቋሚ አድራሽ ከሌለው ያለው አማራጭ አንድም መለመን ካልሆነም ወደ ዘረፋ የሚገባበት ሁኔታ ይኖራል፡፡

አጠቃላይ የከተማውን ነባራዊ ሁኔታ ተቋቁመው ከግምት ውስጥ በማስገባት የወንጀል መከላከልን ሥራ በመስራት ከተማዋ የጸጥታ ሁኔታ ላይ እንድትሆን ማድረግ እጅግ በጣም ትልቅ ሥራ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡

ከመደበኛ ሥራችን ጎን በጎን ኦፕሬሽናል የሆኑ ሥራዎችንም በመስራት በሌቦች ላይ ብቻ አይደለም በተቀባዮችም ጭምር ትልቅ ሥራ እየተሰራ ነው፤ በተለይ የመኪና እቃ ስርቆት በሚፈጽሙት፣ እቃውን በሚሸጡ፣ በሚደልሉ ላይ፡፡

በአዲስ ከተማና በልደታ ክፍለ ከተማ እንኳ በተሰራው ሥራ ወደ 71 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር አውለናል፡፡ እጅግ በርካታ ቁጥር ያለው የመኪና እቃም ይዘናል፡፡

ሆኖም በተለያዩ ቦታዎች ላይ ' ወንጀል ተፈጸመብኝ ' የሚል ሰው ሊያጋጥም ይችላል፡፡ እሱን ለመከላከል ደግሞ የምንሰራቸው ሥራዎች አሉ፡፡

ወንጀል የሚፈጽማባቸው አካላት ወደ ፖሊስ መጥተው ያመልክቱ፡፡ በርካታው ሰው ከዚያ ይልቅ ወደ ሚዲያ ይሄዳል፡፡ ወደ ሚዲያ አይሂድ ማለት አይደለም ግን ወደ ፖሊስ ቢመጣ ያለንበት የመከላከል አቅም የቱ ጋ ድርሷል ለማለት ይረዳናል።
"

#TikvahEthiopiaFamilyAA
#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
🔈#የዜጎችድምፅ

🔵 “ በጸጥታው ችግር  ታካሚዎች በሰው ጫንቃ ታዝለው ነው ሆስፒታል የሚሄዱት፡፡ ተሂዶም መድኃኒት የማይገኝበት ጊዜ አለ ” - ነዋሪዎች

⚫️ “ አቅራቢዎች በቂ የመድኃኒት አቅርቦት እያመጡ አይደለም ” - የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል

በአማራ ክልል፣ ባሕር ዳር ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች ከሆስፒታል ውስጥ መድኃኒት ስለማይገኝ ከግል ፋርማሲዎች በከፍተኛ ዋጋ ለመግዛት እየተገደዱ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ችግሩ የሚገጥማቸው በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ለህክምና ሲሄዱ መሆኑን ለአብነት ገልጸዋክ።

አንዳንዴም በጸጥታ ችግር መንገዶች ስለሚዘጋጉ ተመላላሽ ህክምና በወቅቱ መታከም እንዳልቻሉ አስረድተዋል፡፡

ከፍተኛ የሆነ ችግር ውስጥ ከገቡ ከዓመት በላይ እንዳስቆጠሩ ተናግረዋል።

በከተማዋ ተቋማት እንኳ ከሚከፈቱበት የሚዘጉበት ጊዜ እንደሚበዛ አስረድተዋል፡፡

በተለይ ደግሞ የጸጥታ ችግር በሚፋፋምበት ወቅት የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ሲለሚገደብ ታካሚዎች በሰው ጫንቃ ታዝለው ወደ ሆስፒታል እንደሚወሰዱ ጠቁመዋል።

በሸክም ተወስደው መድኃኒትና ሠራተኛ በሆስፒታሉ የማይገኝበት ወቅት እንዳል አስረድተዋል፡፡

በዚህም በተለይ ተመላላሽ ታካሚዎች መዳን እየቻሉ የመሞት እድላቸው እየሰፋ ነውና የሰላም ያለህ! ሲሉ ተማጽነዋል፡፡

ስማቸው እንዲነገር ያልፈቀዱ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ውስጥ የሚሰሩ አንድ ሀኪም፣ ታካሚዎች ሆስፒታሉ ውስጥ ‘ግላቭ ብቻ ነው ያለው ሌላውን ውጪ ነው የምንገዘው’ እንዳሏቸው ገልጸዋል።

“Ampicillin፣ Gentamicin፣ Vancomicin፣ Cefepime፣ Tretionin” የሚባሉ መድኃኒቶች በሆስፒታሉ ውስጥ እንደሌሉ፣ የ“Laboratory፣ CBC፣ Serum electrolyte፣Liver function test፣ CSF analysis፣ Echo፣ CT scan” አገልግሎቶች በተሟላ ሁኔታ እየተሰጡ እንዳልሆነም ገልጸዋል፡፡

በተለይ ከሳምንታት በፊት ትራንስፖርት ተቋርጦ ስለነበር ሠራተኞቹ ሥራ ለመግባት ተቸግረው እንደነበር፣ በዚህም ታካሚዎቹ ሰርጀሪ የሚሰራላቸው ቀኑ እየተራዘመ መሆኑን አልደበቁም፡፡

ለጉዳዩን ምላሽ የጠየቅነው የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል፣ “አቅራቢዎች በቂ የመድኃኒት አቅርቦት እያመጡ አይደለም፡፡ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከጸጥታውም ይሁን ካለው የገበያ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ማለት ነው” ብሏል፡፡

“ከዚያ በሻገር ግን ዛሬ ላይ መደበኛ ሥራችንን ለማስኬድ የሚያስችል ሰቶክም አለን፡፡ ችግሮችም ይኖራሉ ከአቅማችን በላይ በሆኑ ምክንያቶች” ነው ያለው፡፡

“በቂ ስቶኮች አንይዝም፡፡ ልናገኝ አንችልም፡፡ የ3፣ የ6 ወራት ብለን ልንገዛ አንችልም፡፡ እንገዛ ብንል በጀትም አይኖረንም አቅራቢም አናገኝም” ሲል አስረድቷል፡፡

ከጸጥታው ሁኔታ ጋር ተይይዞ ሠራተኞች አይገቡም ተብሎ ለቀረበው ቅሬታ ሆስፒታሉ ፥ “ ሠራተኞች ይገባሉ፡፡ መንገድ በተዘጋ ጊዜ በአምቡላንስ ነው የምናመጣቸው፡፡ ጦርነት በሚኖርበት ጊዜ ግን አስቸጋሪ ነው ” ሲል ገልጿል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#NewsAlert🚨

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የጭነት ተሽከርካሪዎችን እንቅስቃሴን ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 149/2016 አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።

ምን አለ ?

- መመሪያው የሚመለከታቸው የጭነት ተሽከርካሪዎች / የጭነት አቅማቸው ከ1 ቶን ወይም 10 ኩንታል በላይ የሆኑ ተሽከርካሪዎችን ነው።

- እነዚህ ተሽከርካሪዎች ጠዋት ከ1:00 ሰዓት እስከ 3:00 ሰዓት ድረስ እንዲሁም ከሰዓት 10:30 እስከ ምሽት 1:00 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ እንዳይችሉ ገደብ ተጥሎባቸዋል።

- በዋና መንገዶች ላይ ማቆም፤ ጭነት ማውረድና መጫን እንዲሁም መንቀሳቀስ በክልከላው የተካተቱ ናቸው።

- አዲሱ መመሪያ ከዚህ በፊት ከነበረው የሰዓት ገደብ ላይ በቀረቡ ቅሬታዎች ላይ ማሻሻያ ለማድረግ ታስቦ የወጣ እንደሆነ ተመላክቷል።

- አዲሱ መመሪያ ከመስከረም 2/2017 ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን ሲሆን እሁድ እንዲሁም የበዓል ቀናትን አይመለከትም።

የተቀመጡ የቅጣት እርከኖች ምንድናቸው ?

➡️ በተከለከለ ሰዓት በዋና ዋና መንገዶች ላይ የቆሙ የ10ሺ ብር ቅጣት፤

➡️ በተከለከለው የሰዓት ገደብ የተንቀሳቀሰ 20ሺ ብር የገንዘብ ቅጣት፤

➡️ በቅጣት ሂደቱ በድጋሜ የተቀጣ አሽከርካሪ የቅጣት እርከኑን በእጥፍ የሚቀጣ ይሆናል።

➡️ በተጨማሪ የቅጣት ወረቀት በመያዝ በዋና ዋና መንገዶች ላይ የሚንቀሳቀስ ትዕዛዝ ባለማክበር ተጨማሪ ቅጣት የሚተላለፍባቸው ይሆናል ተብሏል።

ቅሬታ ያላቸው በጹሑፍ ቅሬታቸውን ለባለሥልጣኑ በማመልከቻ ማቅረብ የሚችሉ ሲሆን የባለሥልጣኑ ውሳኔ የመጨረሻ ውሳኔ ይሆናል።

ይህ መመሪያ ቁጥር 149/2016 ከዚህ ቀደም የነበረውን መመሪያ ቁጥር 38/2013 እንዲሁም ሰርኩላሮች፣ ልማዳዊ አሰራሮች የሚሽር ነው።

ይህ መመሪያ ተግባራዊ የማይደረግባቸው የትኞቹ ተሽከርካሪዎች ላይ ነው ?

1ኛ. የሀገር መከላከያ፤ የፖሊስ እንዲሁም በጸጥታ አካላት ስም የተመዘገቡ ተሽከርካሪዎች፤

2ኛ. የድንገተኛ አደጋ ተሽከርካሪዎች፤

3ኛ. ነዳጅ የሚያመላልሱ ቦቴዎችን አይመለከትም።

ከዚህ ቀደም ወጥ አተገባበር ባልተስተዋለባቸው የውሃ አመላላሽ ቦቴዎች ላይ አዲሱ መመሪያ እንዴት ይመለከተዋል ? በሚል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላነሳው ጥያቄ ፥ በአዲሱ መመሪያ እንደሌሎች ከባድ ተሽከርካሪዎች እንደሚስተናገዱ ተገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#እንድታውቁት🚨

በአዲስ አበባ የጭነት ፣ ማሽነሪዎችን እና መሰል ተሸከርካሪዎችን እንቅስቃሴ ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 149/2016 ምን ይላል ?

- መመሪያው ወደ አዲስ አበባ ከተማ ክልል በሚገቡና በከተማ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ እንዲሁም ከተማዋን አቋርጠው በሚያልፉ የመጫን አቅማቸው ከ1 ቶን ወይም ከ1ዐ ኩንታል በላይ የሆኑ የተለያዩ የፈሳሽና የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች እና የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡

- ማንኛውም የጭነት ማመላለሻ ተሽከርካሪ እና የኮንስትራክሽን ማሽነሪ ከጠዋቱ 1፡00 እስከ 3፡00 ሰዓት ከሰዓት በኃላ ከቀኑ 10፡30 እስከ ምሽቱ 1፡ዐዐ ሰዓት ወደ ከተማ ውስጥ መግባትም ሆነ በከተማ ውስጥ መንቀሳቀስ፣ ጭነት መጫንም ሆነ ማራገፍ እንዲሁም በዋና ዋና የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው መንገዶች ላይ መቆም የተከለከለ ነው፡፡

- በዚህ መመሪያ መሠረት ወደ ከተማ መግባትም ሆነ በከተማ ውስጥ መንቀሳቀስ የተከለከለ የጭነት ተሽከርካሪ ወይም የኮንስትራክሽን ማሽነሪ ወደ ከተማ ለመግባት በእንቅስቃሴ ላይ እያለ የሰዓት ገደቡ ቢደርስበት በከተማዋ መግቢያ በሮች ላይ ከዋና መንገድ ወጣ ብሎ በሚገኝ ቦታ ላይ የአካባቢውን የትራፊክ እንቅስቃሴ በማያውክ መልኩ በመቆም የሰዓት ገደቡ እስኪያልፍ መጠበቅ አለበት።

- ማንኛውም የጭነት ተሽከርካሪ ወይም የኮንስትራክሽን ማሽነሪ በከተማ ውስጥ በእንቅስቃሴ ላይ እያለ በዚህ መመሪያ የተደነገገው የጊዜ ገደብ ቢደርስበት የአካባቢውን የትራፊክ እንቅስቃሴ በማያውክ መልኩ ከመንገድ በመውጣት መቆም አለበት።

- በዚህ መመሪያ የተደነገገው የሰዓት ገደብ #እሁድ እና #የበዓል_ቀናት ላይ ተግባራዊ የማይደረግ በመሆኑ ማናቸውም የጭነት ተሸከርካሪ ወይም የኮንስትራክሽን ማሽነሪ ወደ ከተማ ውስጥ መግባትም ሆነ በከተማ ውስጥ መንቀሳቀስ፣ ጭነት መጫን ሆነ ማራገፍ ይችላል፡፡

የሰዓት ገደብ የማይመለከታቸው ተሽከርካሪዎች የትኞቹ ናቸው ?

1. ሰሌዳቸው በሀገር መከላከያ ወይም በፖሊስ የተመዘገቡ የሀገር መከላከያ እና ሌሎች የፀጥታ ስራዎችን የሚያከናወኑ ከባድና ቀላል የጭነት ተሽከርካሪዎች፤

2. በህግ መሠረት የድንገተኛ አደጋ ተሸከርካሪዎች ተብለው የተለዩ የድንገተኛ አደጋ የሚሰሩ ቀላልና ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች፤

3. ነዳጅ የሚያመላልሱ ቦቴዎች

አስተዳደራዊ ቅጣቱ ምን ይመስላል ?

🔵 በተከለከለ ሰዓት ወደ ከተማ ውስጥ በመግባትና በዋና ዋና መንገዶች ላይ የቆመ ብር 10,000 (አስር ሺህ ) ይቀጣል፡፡

🔵 በዋና ዋና መንገድ ላይ የተንቀሳቀሰም ሆነ የጭነት መጫንና ማውረድ ተግባር የፈፀመ ወይም የኮንስትራክሽን ስራ የሰራ ብር 20,000 (ሃያ ሺህ) ይቀጣል፡፡

🔵 በመመሪያው ላይ የተደነገገወን የሰዓት ገደብ በመተላለፍ ከተቀጣ በኃላ ለሁለተኛ ጊዜ ጥፋቱን በመድገም የተገኘ ማንኛውም ሰው ከላይ የተገለፀውን ቅጣት በእጥፍ ይከፍላል፡፡

NB. በተከለከለው ሰዓት በከተማው ውስጥ ሲንቀሳቃስ በመገኘቱ ቅጣት የተጣለበት አሸከርካሪ ሰዓቱ ሳይደርስ የቅጣት ወረቀት ይዞ በተከለከለው ሰዓት እንዲንቀሳቀስ አይፈቀድለትም። የትራፊክ ተቆጣጣሪው ፍሰት በማያሰናክል ቦታ ላይ ተሸከርካሪው እንዲቆም በማድረግ ቅጣቱን እንዲከፍል ማድረግ አለበት፡፡

🗓 ይህ መመሪያ ከመስከረም 2 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
👏 #ሲፈን_ተክሉ የአዲስ አበባዋ ተማሪ ሲፈን ተክሉ በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተፈጥሮ ሳይንስ ከ600ው 575 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባለች። ሲፈን የኦግዝሌየም ካቶሊክ ትምህርት ቤት ተማሪ ናት። ተማሪዋ " ጌዜን ትምህርት ላይ ማሳለፌ ፣በቡድን ማጥናቴ ፣ የቤተሰብና የመምህራኖቼ ድጋፍ ለዚህ ስኬት አብቅቶኛል " ብላለች። ለቤተሰቦቿ 2ኛ ልጅ የሆነችው ሲፈን የስርዓተ ምግብ…
#ደሴልዩአዳሪትምህርትቤት👏

“ ትምህርት ቤቱ በአጠቃላይ ውጤት በኢትዮጵያ አንደኛ ፤ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ደግሞ ሁለተኛ ነው ” - የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት

በ2016 ዓ/ም አገር ዓቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በኢትዮጵያ በሁለተኛ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበው በአማራ ክልል፣ የይሁኔ ወልዱ ደሴ መታሰቢያ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ነው፡፡

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃሉን የሰጠው ትምህርት ቤቱ፣ የተመዘገበው ከፍተኛው ውጤት 574 መሆኑን ገልጿል፡፡

ይህን ውጤት ያስመዘገው ተማሪ ጌታቸው እያዩ ይባላል፡፡

ከዚህ ቀጥሎ በትምህርት ቤቱ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 562 መሆኑን ትምህትር ቤቱ ገልጿል፡፡

በትምህርት ቤቱ በሴቶች የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 546 ነው፡፡ ውጤቱ የተመዘገበው በሀያት አብዱ ነው።

የተመዘገበው ዝቅተኛ ውጤት ደግሞ 458 ነው፡፡

ትምህርት ቤቱ በአጠቃላይ ያስፈተናቸው ተማሪዎች ብዛት 65 ሲሆን፣ ከእነዚህ መካከል 45 ተማሪዎች ከ500 በላይ ውጤት አስመዝግበዋል ተብሏል፡፡

“ ትምህርት ቤቱ በአጠቃላይ ውጤት በኢትዮጵያ አንደኛ ነው፡፡ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ሁለተኛ ነው ” ሲል ትምህርት ቤቱ ለቲክቫህ ገልጿል፡፡

አክሎ፣ “ አጠቃላይ ውጤት የሚባለው፣ አንደኛ ትምህርት ቤቱ ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100 ፐርሰንት ሲያሳልፍ፣ ሁለተኛ ደግሞ የተማሪዎቹ ውጤት ተደምሮ ሲካፈል ነው፡፡ በዚህ ትምህርት ቤቱን ማንም ትምህርት ቤት አይበልጠውም አንደኛ ነው ” ብሏል፡፡

“ ትምህርት ቤቱ በአጠቃላይ ውጤት በኢትዮጵያ አንደኛ፤ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ደግሞ ሁለተኛ ነው ” ነው ሲል ገልጿል፡፡

የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት የሚገኝበት የአማራ ክልል ዘንድሮ በብዙ የሰላም እና ፀጥታ ችግር ውስጥ እያለፈ ያለ ክልል ነው።

ባለፉት ዓመታትም ክልሉ በጦርነትና የከፋ የፀጥታ ችግር ላይ ሆኖ እንኳን የሀገሪቱን ከፍተኛ ውጤቶች ያስመዘገቡ ተማሪዎች የወጡበት ነው።

ዘንድሮም ከሀገር ሁለተኛው ከፍተኛ ውጤት በዚሁ ክልል ተመዝግቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" እንደ ባሪያ ነው የምንታየው ፤ እባካችሁ ጭሁልን !! " - በማይናማር የሚገኙ ወጣቶች ማይናማር እና ታይላንድ ድንበር ላይ ከሚገኙ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የበየነ መረብ ማጭበርበር (Online Scam) ተግባራት ከሚፈጸምባቸው አንዳንድ ቦታዎች ቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክቶችን በቴሌግራም እየተቀበለ ይገኛል። እነዚህ ቦታዎች ላይ በርካታ የሀገራችን ወጣቶች ያሉ ሲሆን " ታይላንድ እንልካችኋለን " በሚል…
#Update

° " ብዙ አካላቸው የጎደለ ሰዎች አሉ፡፡ አካል እስከ ማጉደል ድረስ ነው ቅጣቱ " - ኢትዮጵያዊያን በማይናማር

° " መረጃው ትክክል ነው፡፡ ዜጎች ችግር ላይ ናቸው ተቋሙም ኃላፊነት ወስዶ ለወገኖቻችን ለመድረስ ጥረት እያደረገ ነው " - ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር

በማይንማርን ጨምሮ በአካባቢው የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን በከፋ ችግር ውስጥ እንደሆኑ ከወራት በፊት በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ድምጻቸውን አሰምተው እንደነበር ይታወሳል።

አሁንም ኢትዮጵያውያኑ የኢትዮጵያ መንግስት እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።

መጀመሪያ ከአገር ሲወጡ የተዋዋሉት የሆቴል ቤት ሥራ አስኪያጅ፣ ሀኪም እና የመሳሰሉትን ሥራዎች ሊሰሩና ዳጎስ ያለ ክፍያ ሊፈጸምላቸው እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

ይሁን እንጅ ከዚያ ከደረሱ በኋላ ሽፍታ ወዳለበት የማይናማር ክልፍ እንደወሰዷቸው፣ ጭራሽ ደመወዝ እንደማይፈጽሙላቸው ፣ ከውላቸው ውጪ ዶላር ማጭበርበር እንደሚያሰሯቸው አስረድተዋል፡፡

የሌሎች አገር ዜጎች በአገራቸው መንግስት አማካኝነት እየተለቀቁ ቢሆንም ኢትዮጵያዊያኑ ግን የከፋ ስቃይ ውስጥ እንደሆኑ ገልጸው መንግስት እንዲደርስላቸው በአንክሮ ጠይቀዋል፡፡

ቤተሰቦቻቸው በበኩላቸው፣ መንግስት የልጆቻቸውን ሕይወት እንዲያተርፍላቸው ተማጽነዋል፡፡

ኢትዮጵያዊያኑ በዝርዝር ምን አሉ ?

" እያንዳንዱ ሰው የግድ በቀን 17 ሰዓት መስራት አለበት፡፡ የተሰራበት ደመወዝ ግን አይከፈልም፡፡ ገቢ ካላስገባ ቅጣት አለ፡፡ አለንጋም አላቸው ይገርፋሉ፡፡ ጨለማ ቦታ ላይ ወስደውም ያስራሉ፡፡

በአንድ ጊዜ ሦስት 20፣ 20 ሊትር ጀሪካን ያሸክማሉ፡፡ ሁለቱን በሁለቱ ትክሻቸው፣ አንዱን በእግርና እግር መካከል እንዲሸከሙ የሚገደዱ ኢትዮጵያዊያን አሉ፡፡

በተጨማሪ ብዙ ሰዎች ባሉበት አካባቢ ፊት ለፊት እንደ ማሳያ ተደርገን እንገረፋለን፡፡ በቀን አምስት ሰዓት ብቻ ነው የሚታረፈው፡፡

እጅና ኮምፒዩተር ለአፍታ ከቦዘኑ፣ የሆነ ስህተት ከተሰራ ድብደባ አለ፡፡ ምንም ነጻነት የሌለበት አገር ነው፡፡

ብዙ አካላቸው የጎደሉ ሰዎች አሉ፡፡ አካል እስከማጉደል ነው ቅጣቱ፡፡ እግራቸው፣ እጃቸው፣ ሁሉ ነገራቸው የተጎዳ ሰዎች አሉ " ሲሉ አስረድተዋል።

ኢትዮጵያዊያኑን ካሉበት የከፋ ችግር ለማውጣት ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ ያቀረብንላቸው  የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ ለጉዳዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

" በማይናማር የሚገኙ ዜጎቻችን ጉዳይ ይታወቃል፡፡ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል በተለይ ሳወዝ ኤዢያ ካሉ ኤምባሲዎቻችን ውስጥ አንዱ ጃካርታ ነው፤ ኢንዶኖዢያ፡፡ ጉዳዩ እነርሱም ደርሷቸው እየጠከታተሉ ነው " ብለዋል።

" ይሄ መስመር በአጠቃላይ እንደ አዲስ የሕገ ወጥ ፍልሰት መንገድ ሆኖ ነው እየታዬ ያለው፡፡ እስከሁን ባልተለመደ ሁኔታ ወደዚህ አቅጣጫ ከዚህ ቀደም ከምናውቃቸው ትንሽ ወጣ ያለ ነው። ጉዳዩም ጥናት የሚፈልግ ሆኖ ነው የተገኘው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡

" ዜጎች የትም አገር፣ የትም ቦታ ይሁኑ የመጀመሪያው መዳረሻ ችግራቸውን ለመፍታት ውጪ ጉዳይ እንደመሆኑ መጠን ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ክትትል እየተደረገበት ነው " ብለዋል።

ኢትዮጵያዊያኑ የአካል ጉዳት ጭምር እየደረሰባቸው በመሆኑ በፍጥነት እንዲደረስላቸው እየጠየቁ እንደመሆኑ  ከኤምባሲዎቹ ጋር ያለው ንግግራችሁ ተስፋ አለው ? በምን ደረጃ ላይ ነው ? የሚል ጥያቄ ቲክቫህ ለአምባሳደሩ አቅርቧል።

አምባሳደሩ በምላሻቸው፣ " እንደ አጋጣሚ ሆኖ ኢትዮጵያ ማይናማር ውስጥ ኤምባሲ የላትም፡፡ ምንም አይነት ዲፕሎማሲክ ውክልና የለንም " ብለዋል።

" ስለዚህ ከእርቀት ሆነው ነው ይህን ነገር የሚከታተሉት፡፡ መረጃው ትክክል ነው፡፡ ዜጎች ችግር ላይ ናቸው። ተቋሙም ኃላፊነት ወስዶ ለወገኖቻችን ለመድረስ ጥረት እያደረገ ነው " ሲሉ አክለዋል።

በችግር ላይ እንደሆኑ የሚነገርላቸው
ከ3000 በላይ ኢትዮጵያዊያን እንደሆኑ ነው፡፡ ተቋምዎስ ስንት እንደሆኑ ያውቃል? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄም ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

" ቁጥር ልንሰጥ አንችልም፡፡ ነገር ግን ቁጥራቸው 3000ም ሆኑ ሦስት ኢትዮጵያዊያን ችግር ላይ እስካሉ ድረስ ችግራቸው ችግራችን ሆኖ ተቋሙ ዜጎችን ለመታደግ ይንቀሳቀሳል " ነው ያሉት።

ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba #ባጃጅ በአዲስ አበባ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት በሂደት ሙሉ በሙሉ መቋረጡ አይቀሬ እንደሆነ ተሰምቷል። በአዲስ አበባ ከተማ የባለሶስት እና አራት እግር ተሽከርካሪ ወይም ባጃጅ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች  የአሰራር ፣ የአጀረጃጀት፣ የአገልግሎት አሰጣጥና የዲሲፒሊን ቁጥጥር አፈጻጸም መመሪያ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጎ ነበር።                               …
#AddisAbaba

“ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ከተማው ጸጥታ ስጋት የሆኑ ባጃጆች አሉ ” - የኡ/ ትራንስፖርት ቢሮ

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ከአዲስ አበባ ውጪ መጥተው የሚሰሩ ባለሦስትና አራት እግር አሽከርካሪዎች የአዲስ አበባ መታወቂያ፣ የአዲስ አበባ ሰሌዳ እስከሚያሟሉና በማኅበር እንስከሚደራጁ ድረስ በከተማዋ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዳይሰጡ እንደሚደረግ ማሳወቁ ይታወሳል።

ቢሮው ይህን ያለው በእነዚህ የተሽከርካሪ አይነቶች ወንጀል እየተፈጸመ መሆኑን በመግለጽ ነው፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ጉዳዩን በተመለከተ ከወጣው መግለጫ በተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጥ ከከተማው ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራ ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡

Q. በታገዱት የትራንስፖርት አይነቶች ሥራ ተሰማርተው ቤተሰብ የሚያስተዳድሩ አሽከርካሪዎች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ለምን ሰፋ ያለ ጊዜ አልተሰጣቸውም ? ቀድሞ ማሳወቅ አይቻልም ነበር ?

አቶ ዳኛቸው ፦

“ አዲስ አበባ ዋና ከተማ እንደመሆኗ መጠን የሚበረታታውና የሚደገፈው ማስ ትራንስፖርት ነው፡፡ ከማስ ትራንስፖርት አንጻር አዲስ አበባ አውቶብስ ድርጅት አለ፡፡ ድጋፍ ሰጪ የምንላቸው ሦስት ቁጥር ታክሲዎች አሉ፡፡ ከዚያ ውጪ ቁጥር አንድ የምንላቸው ታክሲዎች አሉ፡፡

ከእነዚህም የበለጠ የሚበረታታውና የሚደገፈው ማስ ትራንስፖርቱ ነው፡፡ ከባጃጅ ትራንስፖርት ጋር ባለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አደራጅቶ ስምሪት መስጠት የሚችለው በአዋጁ መሠረት ራሱ የሰጠውን ታርጋ ብቻ ነው፡፡

ይሄ በአዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ክልሎችና ከተሞች በራሳቸው ታርጋ የሰጡት፣ የመዘገቡት ብቻ ነው አደራጅተው ማሰማራት የሚችሉት፡፡

ከባጃጂ ጋር ተያይዞ አዲስ አበባ ውስጥ ወደ 5,000 አካባቢ የሚጠጉ ባጃጆች በ93 ማኅበራት፣ እንዲሁም በ73 መስመሮች አካባቢ ላይ ታፔላ ወስደው እየተሰማሩ ነው ያሉት፡፡

አዲስ አበባ በዚህ ደረጃ አጣዳፊ ሥራውን ማሰማራት ተገቢነት የለውም፡፡

ከአዋጅ ውጪ ነው የሚል ቅሬታዎች በተደጋጋሚ ሲነሳ ነው የቆየው፡፡ ቅሬታውም ተገቢ ነው፡፡  ስለዚህ በዚህ ሰዓት ባጃጅን ማበረታታት፣ ማሰማራት አይደገፍም፡፡

በአንድ በኩል የአዲስ አበባ ታርጋ የላቸውም ኦልሞስት 99 ፐርሰንት፡፡ 243 ብቻ ናቸው የአዲስ አበባ ታርጋ ያላቸው ከ5 ሺዎቹ፡፡

አንደኛ ሕጉ መከበር አለበት፡፡ ስህተት በስህተት ላይ መደገም የለበትም፡፡ ሁለተኛ እነዚህ ባጃጆች አካባቢ ሌብነት ይካሄዳሉ፡፡

ህዝቡም እሮሮ ያቀርበል፡፡ ብዙ ቅሬታዎች ናቸው የሚቀርቡት፡፡ የጽንፈኛ ኃይልም አጋዢ ሆነው የሚሰሩ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ለከተማው ጸጥታ ስጋት የሆኑ ባጃጆች አሉ፡፡

ከተማ አስተዳደሩ ቅድሚያ የሚሰጠው ለከተማው ሰላም ነው፡፡ ስለዚህ እንዚህ ባጃጆች እንዲቆሙ ሳይሆን ወደ ሕግ እንዲመለሱ ነው፡፡ ወደ ሕግ እንዲመለሱ ሲደረግ ደግሞ አንደኛ መደረግ ያለበት አንደኛ ታርጋ ማውጣት ነው፡፡

ታርጋ ለማውጣት ደግሞ እዘዚህ ባጃጆች ታርጋ ያወጡበት ሂደው ክሊራንስ፣ ሊብሬ አምጥተው የአዲስ አበባ ታርጋ ወስደው እንዲደራጁና ወደ ስምሪት እንዲገቡ ማድረግ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ታርጋ ይወስዳሉ፣ ይዘጋጃሉ፣ ወደነበሩበት ይመለሳሉ”።


Q. ቢሮው አጣድፎ ውሳኔውን የወሰነበት ምክንያት ምንድን ነው? አጭር ጊዜ አልሆነም ወይ? ለሚለው ጥያቄ ቀጥታ ምላሽ እንዲሰጡ በድጋሚ ጠይቀናቸዋል፡፡

አቶ ዳኛቸው፦

“ ከተማ አስተዳደሩ ቅድሚያ የሚሰጠው ለከተማው ሰላም ነው፡፡ ትራንስፖርት ሰላምን መሆንን፣ ምቹ መሆንን፣ ተደራሽ መሆንን ይፈልጋል። ስለዚህ በባጃጆች አካባቢ ያለው ሌብነት፣ ዝርፊያ፣ ያለው የከተማውን ሰላም የማናጋት መጠቀሚያነት ከህዝብ በተደጋጋሚ እሮሮ የመጣበት ነው።

ሁለተኛ ታርጋ የሰጥዋቸው ክልሎች፣ ‘አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እኛ የሰጠነውን ካርታና ሊብሬ አደራጅቶ የማሰማራት ስልጣን የለውም ሕገ ወጥ ሥራ ነው እየሠራ ያለው’ የሚል ቅሬታ፣ ስሞታ፣ ክስ አለ፡፡

እውነት ነው በሰላማዊ መንገድ ሥራ የሚሰሩ ልጆች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ እነርሱንና ጤናማ ያልሆኑትን ለመለየት ወደ ሕጋዊ መስመር መመለስ ግድ ስለሆነ፡፡

ሰፊ ጊዜ የሚፈልግ ጉዳይ አይደለም፤ ምርምር አይደለም፡፡ ታርጋ ያወጡበት፣ መረጃቸው ያለበት ሂደው ማምጣት ነው፡፡ አብዛኛው ደግሞ መረጃ የሚያሳየው ሸገር ዙሪያ ነው፡፡

ምክንያቱም አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባጃጂ ታርጋ ሲሰጥ ስላልነበረ አብዛኛው ያወጡት እዚህ አካባቢ ናቸው። አማራ ክልልም ተጭነው የመጡ አሉ ይታወቃል፡፡ ሌሎች አካባቢዎችም ተጭነው የመጡ አሉ ይታወቃል፡፡

ዞሮ ዞሮ ግን ለምን ተጣደፋችሁ? ለሚለው ነገር የከተማውን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅ ማንኛውም ተሽከርካሪ ሕግ አክብሮ እንዲሰራ ለማድረግ ነው”፡፡


Q. አሽከርካሪዎቹ በከተማዋ ለመስራት እንደያሟሉ ከተጠየቁት መስፈርት አንዱ የአዲስ አበባ የነዋሪነት መታወቂያ መሟላት ነው፡፡ ይህን አገልግሎት ደግሞ ኤጀንሲው እየሰጠ አይደለም፡፡ መታወቂያውን የት አምጥው ያሟላሉ ተብሎ ነው እንዲህ የተደረገው ? ቢሮው ጉዳዩን አጢኖት ነበር ?

አቶ ዳኛቸው፦

“ ይሄ ጥያቄ ለምን Issue ሆኖ ይነሳል? የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መታወቂያ እየሰጠ አይደለም የሚለው መረጃ ስህተት ነው፡፡

ወሳኝ ኩነት ከከተማ ጀምሮ እስከ ወረዳ አደራጅቶ በቴክኖሎጅ ታግዞ ነዋሪው ግልጽ በሆነ መንገድ መታወቂያ እንዲያገኝ አመቻቾቶ መስራት ከጀመረ አመታት ተቆጥረዋል። "


Q. ከክልል ከተሞች በመሸኛ ለሚመጡት እየሰጠ እንዳልሆነ መረጃው እንዳለን ገልጸንላቸው፣ በድጋሚ ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠይቀናቸዋል፡፡
አቶ ዳኛቸው፦


“ አሁን እኛ እያወራን ያለነው ከክልል ሰው አዲስ አበባ ውስጥ መታወቂያ አውጥቶ ሥራ ይስራ እያልን አይደለም ያለነው፡፡ ግልጽ ነው አቅጣጫው ለምንድን ነው የአዲስ አበባ ነዋሪ መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈለገው ?

ዝርፊያዎች፣ ሌብነት፣ ተለያዩ ጽንፈኛ ኃይሎች መጠቀሚያ መሆን ማስቀረት ከተፈለገ የነዋሪነት ወታወቂያ የግድ ያስፈልጋል። ”
ብለዋል፡፡

ሌላ ጥያቄ እያቀረብንላቸው በነበረበት ወቅትም ማብራሪያቸውን መቅዳት እንድናቆም አስገድደው፣ ለጥያቄው ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ምላሽ ላልሰጠባቸው ሌሎች በርከት ያሉ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆነ በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia