TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አቶ ሚሊዮን ማትዮስ...

የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ #ሚሊዮን_ማቲዎስ:

• አሁን ባለው ሁኔታ እንደከዚህ ቀደሙ የሲዳማን የክልልነት ጥያቄ አፍኖ ለመቀጠል አዳጋች ነው፤

• የደቡብ ክልል ከአምስት ወደ አንድ ሲጠቃለል በዴሞክራሲያዊ መልኩ ህዝቦች ተወያይተውበት፤ ቋንቋዬንና ባህሌን ለማሳደግ ይመቸኛል በሚል አይደለም፤

• ደኢህዴን ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ የወሰነው ዘላቂ ሰላምን ከማረጋገጥ አንፃር ህዝቦች ያዋጣል የሚሉትን ሃሳብ ማዳመጥ ተገቢ ሆኖ በመገኘቱም ጭምር ነው፤

• የሲዳማ ክልል መሆን የክልሉን #አደረጃጀት ይቀይረዋል፤ አደረጃጀቱ ሲቀየር ደግሞ በጥናት ላይ ተመስርቶ የህዝቦች ትስስርና ጥቅም ጥናት ላይ የተመሰረተውን መነሻ ከህዝቦች ጋር ውይይትና ምክክር በማድርግ መፈፀም እንዳለበት ይታመናል፤

ሃዋሳ ከተማን አሁንም ቢሆን የሲዳማ ዞን ዋና ከተማ ናት፡፡

#ሲዳማ_ክልል ከሆነ #ሃዋሳ የሲዳማ ክልል ዋና ከተማ ሆኖ ይቀጥላል ማለት ነው፤

• በሃዋሳ የሚኖሩ የተለየዩ ብሄር ብሄረሰቦችን በሚመለከት የሃገሪቱ ህግና ህገመንግስት በሚፈቅደው መሰረት ዜጎች የመኖር የመስራት መብታቸውን የሚያግድ ነገር ይኖራል ብለን አንገምትም።

Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
#update በወላይታና በሲዳማ ብሄር መካከል እርቀ ሰላም የማውረድ እንቅስቃሴ #ቀጥሏል፡፡ የወላይታ አገር ሸማግሌዎች በግጭቱ የተጎዱ #የሲዳማ_ተወላጆችን #ሃዋሳ ሄደው በባህላዊ ሥርዓት ያፅናኑ ሲሆን የሲዳማ ሸማግሌዎችም ወላይታ ሶዶ በመሄድ ጠይቀዋል፡፡ በቀጣይም እርቀ ሰላም የማውረድና የይቅርታ ሥርዓት ከህዝብና #ከወጣቶች ጋርም ይፈፀማል ተብሏል፡፡


ምንጭ፦ voa
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሃዋሳ

የሀዋሳ ከተማ አብያተክርስቲያናት ወጣቶች ህብረት በሀዋሳ ከተማ ትላንት ቅዳሜ በቀን 06/11/11 ከጠዋቱ 1 ሰዓት ጀምሮ የፅዳት ዘመቻ አካሂዷል።

Via Wondesen/TIKVAH-ETH/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሃዋሳ

ዛሬ በሀዋሳ ከተማ አንፃራዊ ሰላም መስፈኑ ተሰምቷል። የንግድ እና የትራንስፖርት እንቅስቃሴዎች ግን አሁንም እንደ ቆሙ ነው። ነዋሪዎች ግን በከተማይቱ ይንቀሳቀሳሉ። ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የመከላከያ ሰራዊት እና የፌደራል ፖሊስ አባላት ከተማይቱን ሲዘዋወሩ እንደተመለከቱ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት በስልክ ገልፀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሃዋሳ #ሃምሌ19

በሐዋሳ ከተማ በዛሬው ዕለት የተከበረው ዓመታዊው የገብርኤል የንግሥ በዓል ሰላም መጠናቀቁን የከተማው ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር #መስፍን_ዴቢሶ ገልፀዋል። 

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አምቦ #ለኩ #ጅማ #ከሚሴ #ይርጋለም #ሃዋሳ #ሶዶ

ኑ ትውልድ እንገንባ!

#አዲስ_አበባ
0970514616/ዮናስ ገ/መስቀል/
0924140293/መባ/

#ሰበታ
0932540523/ያሬድ ለማ/
0921421493/ያብስራ ካሳ/

#መቐለ
0912178520/ኤርሚያስ ደጀኔ/
0923602445/ፊራኦል መስፍን/

#ራያ_ቆቦ
+251949256094/ሉላይ/

#ጅማ
0911670454/አሰፋ/

#ድሬዳዋ
0915034762/መሃሪ/

#አዳማ
0949377735/ሰላም/

#ሀዋሳ
+251926429534/ተስፋ/
+251935932153/ብስራት/

#ለኩ
0919687777/ዳዊት እንዳለ/

#ይርጋለም
0953804369-/አሸናፊ/
0964039768-ብርሀኑ/

#ከሚሴ
0915543171/ሁሴን/

#ወላይታሶዶ
+251913776084/Aso/
0926172318/Beza/

•ከ1ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ መደበኛ የመማሪያ እና አጋዥ መፅሃፍትን በመለገስ ለመጭው ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን እናውርስ!!

📚የዘንድሮው አመት ተፈታኝ ተማሪዎች እና ወላጆች በዚህ ስራ ላይ በስፋት በመሳተፍ ለመጭው ትውልድ አርዓያ ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን!

5ኛው አመት የTIKVAH-ETHIOPIA የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ!

በዚህ ሀገራዊ ስራ መሳተፍ የምትፈልጉ የበጎ አድራጎት ማህበራትና ግለሰቦች @tsegabwolde

በሁሉም ከተሞች ያሉ አስተባባሪዎችን በየዕለቱ እናሳውቃለን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የመኪና_ስርቆት

አዲስ አበባ ፖሊስ ባደረገው ኦፕሬሽን በተለያዩ ጊዜያት የተሰረቁ 22 ተሽከርካሪዎችን እና 33 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለፀ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ይስተዋል የነበረውን የተሽከርካሪ ስርቆት ለመከላከል እና ወንጀል ፈፃሚዎችን ህግ ፊት ለማቅረብ የአዲስ አበባ ፖሊስ በጥናት ላይ በመመስረት የምርመራ እና የክትትል ቡድን አቋቁሞ ባካሄደው ኦፕሬሽን በተለያዩ ጊዜያት የተሰረቁ 22 ተሽከርካሪዎችን ማስመለሱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

ተሽከርካሪዎቹ እየተሰረቁ አብዛኞቹ ወደ #ሃዋሳ ከተማ እንደሚወሰዱ በምርመራ ማረጋገጥ እንደተቻለ የገለፀው ፖሊስ ከተሰረቁት ተሽከርካሪዎች መካከል ሰባቱ በአዲስ አበባ የተገኙ ሲሆን የተቀሩት 15 ተሽከርካሪዎች ደግሞ በሀዋሳ ከተማ እና ከሀዋሳ ከተማ 100 ኪሎ ሜትር ርቃ በምትገኝ አነስተኛ ከተማ ተይዘው ዛሬ ግንቦት 17 ቀን 2014 ዓ/ም ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ መደረጉን አሳውቋል።

ተሽከርካሪ በመስረቅ፣ የተሰረቀውን ተሽከርካሪ በመግዛት እና በመደለል ተሳትፎ ያደረጉ ከአዲስ አበባ 19 ከሃዋሳ ደግሞ 14 በአጠቃላይ 33 ግለሰቦች ተይዘው ምርመራው በስፋት መቀጠሉን ፖሊስ አክሎ አመልክቷል።

ተሽከርካሪዎቹን ለጥበቃ ምቹ በሆነ ቦታ ባለማቆም በሚፈጠር ክፍተት እና አሽከርካሪዎች ለልዩ ልዩ ጉዳይ የመኪናቸውን ቁልፍ ተሽከርካሪ ላይ ጥለው ሲወርዱ እና የተሽከርካሪውን ቁልፍ በልዩ ልዩ አጋጣሚ በማስቀረፅ ወንጀል ፈፃሚዎቹ የስርቆት ወንጀሉን ሲፈፅሙ እንደነበር በምርመራ ተረጋግጧል።

አዲስ አበባ ፖሊስ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ አስገንዝቦ ለስራው ስኬታማነት ድጋፍ ላደረጉት የፌዴራል ፖሊስና የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ምስጋና አቅርቧል።

Via - AA POLICE

@tikvahethiopia