TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#OFC

ባለፈው ሳምንት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ከፍተኛ አመራሮች አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ጃዋር መሀመድ ፣ አቶ ደጀኔ ጣፋ ፣ አቶ ሀምዛ ቦረና እና ሎሎችም በአቶ ጃዋር መዝገብ ስር ያሉ ግለሰቦች ከእስር መፈታታቸው ይታወሳል።

ከእስር ስለተፈቱ ግለሰቦች ኦፌኮ አሰተያየቱን ለቪኦኤ ሰጥቷል።

ኦፌኮ የፓርቲው አመራሮች እና አባላት መፈታታቸው ደስ እንዳሰኘው የፓርቲው የፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ጥሩነህ ገምታ ተናግረዋል።

አቶ ጥሩነህ ፥ " በጣም ደስ ብሎናል ደስታችን ወደር የለውም፤ እነዚህ አባሎቻችን በመፈታታቸው አመራሮች ናቸው ያው ኦፌኮ አመራር የተሟላ ይሆናል ብለን ስለምናስብ እነሱም ከቤተሰቦቻቸው ፣ ከወዳጆቻቸው ፣ ከዘመዶቻቸው ጋር መቀላቀላቸው በጣም ደስ አሰኝቶናል። በዚህም የተነሳ አባሎቻችን ፣ ደጋፊዎቻችን ፣ መላው ህብረተሰባችን ፣ በሀገር ውስጥም ይሁን ከሀገር ውጭ የሚገኙ በዚህ መጥፎ ጊዜ ከጎናችን በመቆማቸው አመስግነናቸዋል " ብለዋል።

አክለውም ፥ " ያሰራቸው መንግስትም ስለፈታቸው ፣ የተፈቱበት ምክንያት የፈለገው ነገር ይሁን እነዚህ ወገኖቻችን በመፈታታቸው ግን መንግስትንም አመስግነናል ደስ ብሎናል " ሲሉ ተናግረዋል።

መንግስት አሁን እየተዘጋጀበት ያለውን የብሄራዊ ውይይት ኦፌኮ በ2009 ዓ/ም ነው መጠየቅ የጀመረው ያለቱ አቶ ጥሩነህ የፓርቲው አመራሮች እና አባላት መፈታት ለውይይቱ ትልቅ አስተዋጾ ይኖረዋል ብለዋል።

መንግስት አሁን ጀመረውን ታሳሪዎችን የመፍታት እርምጃ አጠናክሮ መቀጠል አለበት ያለቱ አቶ ጥሩነህ ፥ የኦፌኮ አባላት፣ የዞንና የወረዳ ኃላፊዎች ዛሬም ቢሆን እስር ላይ ናቸው እነዚህ ሁሉ ቢፈቱና የሀገሪቱን፣ ሰላም ፣ እድገት፣ ልማት አብረን እጅ ለእጅ ብንገነባ የተሻለ ይሆናል ይሄ ጥሪያችን አሁንም ይቀጥላል " ብልዋል ለሬድዮ ጣቢያው።

@tikvahethiopia
አቶ ጃዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባ ዛሬ ባወጡት መግለጫ ምን አሉ ?

• የአርቲስት ሃጫሉ ግድያን ተከትሎ "በተሳሳተ መንገድ ለእስር ተዳርገው" ላለፉት 18 ወራት በእስር መቆየታቸውን ገልፀዋል።

• እስራቸው " ፖለቲካዊ " እንደነበር ገልፀዋል። ለእስር የተዳረግነው ገዢው ፓርቲ በምርጫ የተሻለ ድምጽ እንዲያገኝ ከፖለቲካዊው ምኅዳር ገለል እንድንል ታስቦ ነው ብለዋል።

• በኦሮሚያ፣ ትግራይ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር እና አማራ ክልሎች በሲቪሎች ላይ የደረሰው ጉዳት አሳዛኝ ነው ብለዋል።

• ባለፉት 13 ወራት በአገሪቱ እና በሕዝቦቿ ላይ የደረሱትን ጉዳቶችን መቀልበስ ባይቻልም፤ ተጨማሪ ጉዳቶችን ማስቀረት የምንችልበት ጠባብ ዕድል አለ ብለዋል።

• በቅርቡ መንግሥት ሰላም እና መግባባትን ለመፍጠር ያሳየው አዎንታዊ ምላሽ ተጨባጭ እና በማይቀለበሱ ተግባራት መረጋገጥ አለባቸው ብለዋል።

• በኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ የሚገኘው የእርስ በእስር ጦርነት በሰላም እንዲጠነናቀቅ እና በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋገት እንዲሰፍን የውጭ አካላት አዎንታዊ ሚና እንዲጫወቱ ጠይቀዋል።

• የውጭ አካላት ለተዋጊ አካላት ፖለቲካዊ እና ቁሳዊ ድጋፎችን በማቅረብ ግጭቱን ከማባባስ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።

• የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን በተመለከተ ተዓማኒነት ያለው ምርመራ እንዲደረግ፤ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ እና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፓርቲ አባላት እና ደጋፊዎች ከእስር እንዲለቀቁ ጠይቀዋል።

• ከጠበቆቻችን መካከል ለአቶ አብዱልጀባር ሁሴን ልዩ ክብር ለመስጠት እንወዳለን ብለዋል።

• በግንኙነታችን ወቅት ልዩ አክብሮትን ላሳዩልን የፌደራል ፖሊስ አባላት እና የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ጥበቃዎች እና አስተዳዳሪዎች አድናቆታችንን እንገልፃለን ብለዋል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/OFC-01-11

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አቶ ጃዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባ ዛሬ ባወጡት መግለጫ ምን አሉ ? • የአርቲስት ሃጫሉ ግድያን ተከትሎ "በተሳሳተ መንገድ ለእስር ተዳርገው" ላለፉት 18 ወራት በእስር መቆየታቸውን ገልፀዋል። • እስራቸው " ፖለቲካዊ " እንደነበር ገልፀዋል። ለእስር የተዳረግነው ገዢው ፓርቲ በምርጫ የተሻለ ድምጽ እንዲያገኝ ከፖለቲካዊው ምኅዳር ገለል እንድንል ታስቦ ነው ብለዋል። • በኦሮሚያ፣ ትግራይ፣ ቤኒሻንጉል…
#OFC

በቅርቡ ከእስር የተፈቱት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) አመራሮች እነ አቶ ጃዋር መሀመድ ፣ አቶ በቀለ ገርባ እና ሌሎችም በአዲስ አበባ በሚገኘው የፓርቲው ፅ/ቤት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ኦፌኮ ፤ አሁንም በእስር ላይ ያሉ የቀሩ አባላቱ ከእስር እንዲፈቱ ፣ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አመራሮችና ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ በድጋሚ ጥሪውን አቅርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NEBE ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 26 የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርጉ ማሳሰቡ ይታወሳል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ዛሬ ማብራሪያ ሰጥቷል። በዚህም እስካሁን ጠቅላላ ጉባኤ ያካሄዱ ፓርቲዎች ብልጽግና ፣ ህዳሴ ፣ ካፋ አረንጓዴ ፓርቲ ፣ ጋህነን መሆናቸውን አመልክቷል። እንደ ምርጫ ቦርድ ማብራሪያ ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ በጊዜ ገደቡ መሰረት ቀን ያሳወቁ 3 ፓርቲዎች አሉ። ቦርድ 12 ፓርቲዎች…
#OFC

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ።

የፓርቲው ጉባኤ ዛሬ እና ነገ የሚካሄድ ሲሆን በተለያዩ የፓርቲው ውስጣዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።

በዛሬው የፓርቲው ጉባኤ መክፈቻ ላይ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ አቶ ጀዋር መሀመድ ፣ አቶ በቀለ ገርባ ፣ አቶ ደጀኔ ጣፋን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች እና አባላቶች ተገኝተዋል።

የጉባኤውን ሂደት ተከታትለን የምናሳውቅ ይሆናል።

ፎቶ ፦ ኡቡንቲ ሚዲያ እና Tikvah Family

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የኦፌኮ ጠቅላላ ጉባኤ ፕ/ር መረራ ጉዲና ሊቀመንበር ሆነው እንዲቀጥሉ መረጠ። አቶ በቀለ ገርባ ደግሞ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው እንዲቀጥሉ ተመርጠዋል። ፕ/ር መረራን ለሊቀመንበርነት የጠቆሟቸው አቶ ጃዋር መሀመድ ሲሆኑ የጉባኤው አባላቶች ለሊቀመንበርነት እና ለተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበርነት አቶ ጃዋር መሀመድን ቢጠቁሙም ጥቆማውን Decline ማድረጉ ተገልጿል። በሌላ በኩል ፤…
#OFC

ትላንት በኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተመረጡት የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ አባላት በጉባኤው ፊት ቃለመሃላ ፈፅመዋል።

በሌላ በኩል ፤ የፓርቲው የኦዲት እና ኢንስፔክሽን አባል የሆነው የተመረጡ አባላትም ቃለመሃላ ፈፅመዋል።

ትላንትና በነበረው የመጀመሪያው ቀን የኦፌኮ ጠቅላላ ጉባኤ ፕ/ር መረራ ጉዲና - ሊቀመበር ፣ አቶ በቀለ ገርባ - ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ፣ አቶ ጃዋር መሃመድ - ምክትል ሊቀመንበር ሆነው መመረጣቸው እና የፓርቲው የስራ አስፈፃሚ አባላት መመረጣቸው ይታወሳል።

አቶ ጃዋር ምንም እንኳን ለሊቀመንበርነት እና ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበርትነ በጉባኤተኛው ተጠቁመው ውድቅ ቢያደርጉም ጉባኤው የፓርቲው ም/ ሊቀመንበር አድርጎ መርጧቸዋል።

የኦፌኮ ም/ ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ ለረጅም ዓመታት በውጭ ሀገር ሆነው የ " ኢህአዴግ " መራሹን መንግስት ተገዶ ወደ ለውጥ እንዲገባ በማስገደድ በሚዲያው እና በአክቲቪዝሙ መስክ ጉልህ ድርሻ የተጫወቱ ሲሆኑ በኃላም ወደ ሀገራቸው በመግባት ምርጫቸውን ኦፌኮ በማድረግ ሙሉ በሙሉ የፖለቲካውን ዓለም ሊቀላቀሉ ችለዋል።

አቶ ጃዋር መሀመድ ለአንድ አመት ከመንፈቅም ታስረው ከወራት በፊት ታህሳስ 29/2014 ዓ/ም መፈታታቸው አይዘነጋም።

Photo Credit : Ubuntu TV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#OFC ትላንት በኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተመረጡት የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ አባላት በጉባኤው ፊት ቃለመሃላ ፈፅመዋል። በሌላ በኩል ፤ የፓርቲው የኦዲት እና ኢንስፔክሽን አባል የሆነው የተመረጡ አባላትም ቃለመሃላ ፈፅመዋል። ትላንትና በነበረው የመጀመሪያው ቀን የኦፌኮ ጠቅላላ ጉባኤ ፕ/ር መረራ ጉዲና - ሊቀመበር ፣ አቶ በቀለ ገርባ - ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ፣ አቶ…
#OFC

የኦሮሞ ፊዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሁለተኛው መደበኛ ጉባዔ ተሳታፊዎች ባለ 5 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል።

በዚህ መግለጫ ላይ ፤ ባለፉት 3 ዓመታት በሀገራችን የተከሰቱ ለአያሌ ንፁሃን ህይወት መቀጠፍ፣ ለከፍተኛ ንብረት ውድመትና ፣ ለዜጎች ክብር ውርደት የዳረጉ የርስ በርስ ጦርነቶች ማዘናቸውን ገልፀዋል።

ከጥቂት ወራት ወዲህ ለእርስ በእርስ ጦርነቶቹ ሰላማዊ መፍትሄ ለመፈለግ መንግስት ያደረገውን የአካሄድ ለውጥ በበጎ እንመለከታለን ብለዋል።

በቅርቡ የፌዴራሉ እና የትግራይ ክልላዊ መንግስት ጦርነት ለማቆም ያሳለፉት ውሳኔ በፍጥነት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዲለወጥ ፣ ያልተገደበ እርዳታ ለህዝቡ እንዲደርስ ፣ ግጭትም መልሶ እንዳይቀሰቀስ የሚደረጉ ስራዎች እንዲሰሩ በአፋጣኝ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ጥሪ አቅርበዋል።

በሌላ በኩል ፤ በሰሜን የሀገራችን ክፍል ያለውን ጦርነት ለማስታቆም እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች ቢደነቁም ባለፉት 3 ዓመታት ኦሮሚያን እያመሰ ያለው የእርስ በእርስ ጦርነት የሚገባውን ትኩረት ያለማግኘቱ እንዳሳዘናቸው ጉባኤተኞች ገልፀዋል።

ስለዚህም የፌዴራል መንግስት የሰላም እጁን ለትግራይ ኬ እንደዘረጋ ሁሉ ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር የገባበትን ጦርነት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቁርጠኛ አቋም ላይ ሳይዘገይ እንዲደርስ አሳስበዋል።

ጉባኤተኞቹ በመግለጫቸው ፤ ሰላማዊ ኦሮሚያ ሳትኖር አስተማማኝ ሰላም እና መረጋጋት ያላትን ኢትዮጵያ ማሰብ አይቻልም ብለዋል።

(ሙሉ መግለጫቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#JawarMohammed

ኦፌኮ በብሄራዊ ምክክር ላይ አልሳተፍም ብሏል ?

አቶ ጃዋር መሀመድ (ምክትል ሊቀመንበር) ፦

" ትንሽ የግንዛቤ ችግር አለ። እኛ እንደ ኦፌኮ አንሳተፍም አይደለም ያልነው ቅድመ ሁኔታዎችን ነው ያስቀምጥነው። ብሄራዊ መግባባት (National Dialogue) የኦፌኮ አጀንዳ ነው።

... ስለዚህ ኦፌኮ የብሄራዊ ድርድርን ወይም የብሄራዊ መግባባትን አይፈልግም የሚለው የተሳሳተ አመለካከት ነው፤ እንፈልጋለን፤ አሁንም ቢሆን እንፈልጋለን ፤ አሁንም ቢሆን ለሀገራችን የሚጠቅመው እሱ ነው ብለን ነው የምናምነው።

ነገር ግን ብሄራዊ መግባባት ሲባል ፕሮሰስ አለው ፤ ብሄራዊ መግባባት በሁለት ደረጃ ነው በአንድ ሀገር ውስጥ ሊካሄድ የሚችለው።

አንዱ የፖለቲካ ልዩነቶች ወደ ጦርነት እንዳያመሩ የቅድመ ጦርነት ንግግር የሚባል ነው የፖለቲካ ልዩነቶች ፣ የፖለቲካ ሽኩቻዎች ሀገርን እና የፖለቲካ ኃይሎችን ወደ ጦርነት እንዳያስገቡ በንግግር እና በድርድር ለመፍታት የሚደረግ ብሄራዊ መግባባት አንድ አለ፤ ያ ሳይደረግ እድል አምልጦ ሀገር ወደ ጦርነት ከገባች በኃላ ደግሞ ጦርነት ቆሞ ከጦርነት በኃላ ለጦርነት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችም ሆኑ በጦርነት የተፈጠሩ ክስተቶች ለሌላ ጦርነት እንዳይጋብዙ ከስር መሰረቱ ለመፍታት የሚደረግ ክንውን ነው ፤ ይሄን መገንዘብ አስፈላጊ ነው።

ብሄራዊ መግባባት በጦርነት መካከል ሊካሄድ አይችልም። ሀገራችን በጦርነት መሀከል ነች፤ 2019/20 መጀመሪያ አካባቢ ቢሆን 2019/18 ጥሩ ጊዜ የነበረው ለውጡ እንደመጣ የመጀመሪያ ወራት መጀመር ነበረበት ያ አምልጧል አሁን ጦርነት ውስጥ ነው ያለነው።

ብሄራዊ መግባባት ሲባል የመጀመሪያው criteria ሁሉንም ያሳተፈ መሆን አለበት።

በተለይ ጦርነት ከተገባ ፣ ከሁሉም የበለጠ ብሄራዊ መግባባት ውስጥ መግባት እና መሳተፍ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገባው በጦርነት ውስጥ የተሳተፉት ቡድኖች ናቸው። ጦርነት እየተካሄደ እነዚህ በጦርነት የተሳተፉ ቡድኖች ማሳተፍ አልቻልም። Legally ሆነ በ Security wise ማሳተፍ አይቻልም። ይህ ስለሆነ ዋናው እኛ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጥነው ብሄራዊ መግባባት ጥሩ ነው መንግስት ረጅም ጊዜ አልሰማም ብሎ አሁን የብሄራዊ መግባባት ማለቱ ጥሩ ነው ደስ ብሎናል ነገር ግን ይሄን ነገር በአግባቡ እንስራው ስለዚህ ጦርነት ይቁም ፤ ጦረኞቹ ሙሉ በሙሉ ይታረቁ አይደለም እያልን ያለነው ብሄራዊ መግባባቱ ላይ ሊታረቁ ይችላሉ ነገር ግን active fighting እንዲቆም ማድረግ በሰሜንም ፣ በትግራይ ድምበርም ፣ በቤኒሻንጉልም፣ በኦሮሚያም በተለያየ አካባቢ እየተደረገ ያለው ጦርነት መጀመሪያ መቆም አለበት... "

#ያንብቡ ➡️ https://telegra.ph/Jawar-Mohammed-05-27
#OFC

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ በላከው መግለጫ " በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም በተቀሰቀሰው ጦርነት እና በኦሮሚያ ክልል የቀጠለው ግጭት በመባባሱ እጅግ አዝናለሁ " ብሏል።

ፓርቲድ የነዚህ ግጭቶች መባባስ እና መቀጠል ህዝቡን ዳግም ለከፋ ሞት እና መፈናቀል የሚዳርግ ከመሆኑ ባሻገር ለንብረትና መሰረተ ልማቶች ውድመት የተዳረጉ አካባቢዎችን ለበለጠ አለመረጋጋት ይዳርጋል ብሏል።

ኦፌኮ ጦርነቶቹ ከመቀሰቀሳቸው ቀድም ብሎ ጦርነት ለኢትዮጵያ ውስብስብ የፖለቲካ ችግሮች መፍትሄ ሊሆን እንደማይችል እንደገለፅኩት አሁን ዳግም በአፅንዖት እገልፃለሁ ብሏል።

አሁን ያሉት ችግሮች በዘላቂነት ሊፈቱ የሚችሉት በእውነተኛ እና ሁሉን አቀፍ ድርድር ብቻ ነው ሲል እምነቱን ገልጿል።

በሁሉም ወገን ያሉ ተፋላሚ ሀይሎች ግጭቱን በማብረድ ሰላማዊ መፍትሄ እንዲሹ ጠይቋል።

ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ በግጭት በተጎዱ አካባቢዎች ሁሉ ተጨማሪ ሞት እና የዜጎችን መከራ ለማሰቀረት በንቃት እና በተቀናጀ መልኩ ይረባረብ ሲልም ጥሪ አሰምቷል።

ኦፌኮ በኦሮሚያ እየተስፋፋ ነው ያለውን ግጭት ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለመፍታት ቀርቶ እውቅና ሊሰጠው አልቻለም ያለ ሲሆን ይህ እንደሚያሳስበው ገልጿል።

በክልሉ በተለይም በግጭትና በድርቅ በተጎዱ አካባቢዎች ያለው ሰብዓዊ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲልም ገልጿል።

የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እየተባባሰ ያለው ግጭት በአስቸኳይ እና ሰላማዊ በሆነ መንገድ በድርድር እንዲፈታ ሁኔታዎችንን እንዲያመቻች ጠይቋል።

ፓርቲው የኢትዮጵያ ህዝብ ፣ ገዥው ፓርቲ፣  ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሚዲያ ተቋማት፣ የማህበራዊ ሚዲያ ባለሙያዎች እና አክቲቪስቶች ግጭቱን ከሚያባብሱ ንግግሮች እንዲታቀቡ እና ችግሩን ለማርገብና ለመፍታት በአንድ ድምፅ እንዲተባበሩ ተማጽኗል።

@tikvahethiopia
#OFC #OLF

ቀጣይ በሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ላይ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከእያንዳንዳቸው 50 በመቶ ተወካዮችን ይዘው ለመቅረብ እየሰሩ መሆኑ ተሰምቷል።

የኦፌኮ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ከሰሞኑን ከ " ሪፖርተር ጋዜጣ " ጋር ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር።

በዚህ ቃለ ምልልስ ፓርቲያቸው በቀጣይ ለሚደረገው ሀገራዊ ምርጫ ምን አይነት ዝግጅት እያደረገ እንደሆነ ተጠይቀው ምላሽ ሰጥተዋል።

ፕ/ር መረራ ፤ መንግሥት አሁን ላይ እየሄደበት ባለው መንገድ ወደፊት ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ በኢትዮጵያ ይደረጋል የሚል እምነት እንደሌላቸው ገልጻዋል።

ያም ሆኖ ግን ለምርጫው ከኦነግ ጋር ስምምነት እንዳላቸው ጠቁመዋል።

፣ ከእኛ ሃምሳ በመቶ ከእነሱ ሃምሳ በመቶ ተወካዮችን አዘጋጅተን በምርጫ ለመምጣት ዕቅድ አለን፡፡ " ያሉት ፕሮፌሰር መረራ ጉዲያ "  ከኦነግ ጋር በትብብር ለመሥራት ተስማምተናል " ሲሉ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ፤ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ እንዲሁም የኢህአዴግን ስርዓት በመጣል ውስጥ ከፍተኛ ተፅእኖ ያላቸው የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ በምን ምክንያት እንደጠፉ የተጠየቁት ፕ/ር መረራ ምላሽ ሰጥተዋል።

" እኔ እንደምገምተው የፖለቲካ ምኅዳሩ አልተመቸውም፡፡ " ያሉት ፕ/ር መረራ " የፖለቲካው ምኅዳር ጠቦበታል፣ በዚህ በኩልም እሳት ነው ፤ በዛም እሳት ነው መንግሥትም እሳት ሆነበት  " ሲሉ መልሰዋል።

ከዚህ በተጨማሪ አቶ ጃዋርን ጨምሮ እሳቸው እና የሚመሩት ፓርቲ ከመንግሥት ጋር አብሮ እየሰራ ነው የሚባለው ወሬ ሀሰት መሆኑና ከመንግሥት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌላቸው ፕ/ር መረራ ጉዲና ለጋዜጣው ተናግረዋል።

ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ፦
- አሁን ላይ ዝምታ መርጠው ስለጠፉበት ሁኔታ፤
- ስለ ኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ፤
- በኦሮሚያ ክልል ስላለው ቀውስ እና ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ቀውስ መፍትሄ፤
- ስለ ኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እና የመንግስት ድርድር፤
- ስለ ህገመንግስት መሻሻል ፤
- በኦሮሞ እና በአማራ ፖለቲካ ስላለው ሁኔታ፤
- ስለ ሀገሪቱ ኢኮኖሚ እና ሌሎችም ጉዳዮች ላይ ተጠይቀው ምላሽ የሰጡበት የ " ሪፖርተር ጋዜጣ " ቃለ ምልልስ በዚህ ይገኛል ፦ http://www.ethiopianreporter.com/

@tikvahethiopia
#OFC

የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና አሜሪካ መግባታቸውን ለማወቅ ተችሏል።

ፕሮፌሰሩ በአሜሪካ ለአንድ ወር እንደሚቆዩ የፓርቲው ዓለም አቀፍ ድጋፍ ቡድን አሳውቋል።

በአሜሪካ ቆይታቸው ፦
- ወደ ተለያዩ ግዛቶች በማቅናት ከኦሮሞ ተወላጅ ዳያስፖራዎች ጋር ውይይት ያደርጋሉ።
- ይፋዊ / መደበኛ ባልሆኑ የተለያዩ ግብዣዎች ላይ በመገኘት ከወዳጆቻቸው እና ከፓርቲው ደጋፊዎች ጋር ይነጋገራሉ።
- በኦፌኮ-ዓለም አቀፍ የድጋፍ ቡድን አዘጋጅትነት የሚካሄድ ቨርቹዋል ኮንፈረንስ በመምራት ከዓለም አቀፍ የኦሮሞ ተወላጅ ዲያስፖራዎች ጋር በመገናኘት በወቅታዊ ክልላዊ ፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ፤ በወቅታዊ የኢትዮጵያ አሳሳቢ ችግሮች ላይ እንዲሁም የኦሮሞ ህዝብ ትግል አሁናዊና ቀጣይ ሁኔታን በተመለከተ ይመክራሉ።

ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ወደ አሜሪካ ሀገር ያቀኑት የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ  ፤ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ያለው ፖለቲካዊ ሁኔታ " በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ሆነ በግል በነጻነት ለመኖር " አሳሳቢ በመሆኑ በሄዱበት አሜሪካ ሀገር ጥገኝነት መጠየቃቸውን ካሳወቁ ከ12 ቀናት በኃላ ነው።

ፎቶ - ፋይል

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#OROMIA #PEACE " የመንግሥት ወታደሮች ፣ ሌላም ፣ ንጹሃንም ዋጋ መክፈል የለባቸውም፤ ... ለሰላም ክፍት ነን ድርድሮችም እንዲቀጥሉ እንፈልጋለን " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አሁንም ቢሆን ያሉ ችግሮች #በሰላም እንዲፈቱ መንግሥት #ለድርድር ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል። የክልሉ መንግሥት አመራሮች ከኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጋር በአዲስ አበባ…
ኦነግ እና ኦፌኮ በውይይቱ ተገኝተው ነበር ?

#አልተገኙም

" ውይይት መደረጉን የሰማነው እራሱ በሚዲያ ነው " - ኦፌኮ

በኦሮሚያ ክልል ይንቀሳቀሳሉ ከተባሉ ፓርቲዎች ጋር የክልሉ መንግሥት አድርጎታል በተባለው ውይይት ላይ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) እና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) #አልተሳተፉም

የኦፌኮ ዋና ፀሀፊ አቶ ጥሩነህ ገምታ ለቪኦኤ ሬድዮ ፥ " ውይይቱ መደረጉን የሰማነው ከብዙሃን መገናኛ ነው። እንደ ግለሰብ ይሁን እንደ ተቋም የደረሰን ጥሪ የለም የኮሚኒኬሽን ክፍተቱ ከማን በኩል እንደሆነ አላውቅም " ብለዋል።

ኦፌኮ የክልሉ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባል ቢሆንም ባለው ቅሬታ ሙሉ ተሳትፎ እያደረገ እንዳልሆነ ገልጸዋል።

አቶ ጥሩነህ ፤ ለውይይት በም/ቤት ይሁን በመንግስት ጥሪ አልደረሰንም ብለዋል።

የኦነግ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለሚ ገመቹ በበኩላቸው ፤ ፓርቲያቸው በውይይቱ #እንዳልተሳተፈ ገልጸዋል።

" ለውይይቱ ጥሪ ሊደረግ ይችላል እኛ ግን የምንፈልገው በአንድ አካል አቅራቢነት የሚደረገውን ውይይት ሳይሆን ሁሉም በእኩልነት የሚሳተፍበትን ውይይት ነው። " ብለዋል።

" የምንፈልገው አንድ ሀገርን የሚያስተዳደር መንግሥት በሚሰጥህ ቦታ ተወስኖ መወያየት ሳይሆን እራሳችንን የመፍትሄ አካል ነን ብለን የምናይ አካላት በአንድ ላይ ሆነን በተመሳሳይ ድምጽ ተወያይተን ዘላቂ መፍትሄ የምናስቀምጥበት ካልሆነ ኦነግ በአንድ አካል ጥሪ የሚሳተፍበት መድረክ አይኖርም " ሲሉ ተናግረዋል።

የኦሮሞን ችግር የሚፈተው በእውነታ ላይ የተሰመሰረተ አካታች ውይይት እንደሆነ የገለጹት አቶ ለሚ ፤ ውይይት ሂደቱን ጠብቆ አካታች በሆነ መልኩ መከናወን አለበት አሁን ያለው አካሄድ ሂደቱን ያልጠበቀ ቅንነት የሌለው በአንድ አካል ብቻ ተጎትቶ እየሄደ ያለ ነው ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ም/ቤት ሰብሳቢ እና የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዜዳንት አቶ ሰለሞን ታፈሰ ኦነግ እና ኦፌኮ ከውይይት መቅረታቸውን አረጋግጠዋል።

" በድረገጻችን ላይ ለቀናል፣ በዋትስአፕ ላይ ተለቋል። እንደምንሄድ ኮሚቴው ሲወስን ተለቋል። በአካል አነጋሬያለሁ የሚመለከታቸውን ኦሮሚያ የኢትዮጵያ እምብርት ናት እናተ ስለሚመለከታችሁ ለምን አብረን አንሄድም? ብዬ ነግሬያቸዋለሁ። ተጋብዘዋልም " ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

#Ethiopia
#Oromia #VOA
#OFC #OLF

@tikvahethiopia
#OFC #Ethiopia

" በአንድ ፓርቲ ፍላጎትና ሙሉ ቁጥጥር በሚመራ መንገድ የ120 ሚሊዮን ህዝብ ቁመት የሚሆን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በፍጹም አይፈጠርም !! " - ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና (ለቪኦኤ ሬድዮ ከሰጡት ቃል) ፦

" ዋና የኢትዮጵያ ችግር ፈጣሪ መንግሥት ነው። ይሄ ምንም ጥያቄ የለውም።

ከፖለቲካ ኃይሎች ጋር ሆነን ፣ከዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡም ጋር ሆነን ሀገር ውስጥም ከሀገር ውጭም ያላደረግነው ነገር የለም።

ዋናው ጉዳይ ስልጣን የያዘው ቡድን ሀቀኛ ፍትሃዊ የሚባለውን ነገር በጭራሽ አይፈልገውም።

' ስልጣን እኛ እጅ ነው ' ተንበርከኩና እኛ ጋር ግቡ ወይም የስልጣን ፍርፋሪ ኑና ውሰዱ ካልሆነ በስተቀር የኢትዮጵያ ህዝብ ከመገዳደል ፖለቲካ ወደ መደራደር ፖለቲካ እንዲገባ አይፈልግም።

ችግሩ ይሄ ነው በአንድ እጅ ማጨብጨብ አይቻልም።

እኛ የምንችለውን ያክል ይሄ ሀገር መሸጋገር የሚችለው ፣ የተሳካ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር መምጣት የሚችለው ፣ የተሳካ ሰላም እና መረጋጋት መምጣት የሚችለው ሁሉም የኢትዮጵያ ኃይሎች የተሳተፉበት ፦
- ብሔራዊ እርቅ
- ብሔራዊ ድርድር
- ብሔራዊ ምክክር ሲደረግ ነው እያልን ስንጠይቅ ነበር።

ፖለቲካ እስከሚገባን ድረስ አሁን እየተገፋ ባለበት መንገድ 3 ነገሮች በኢትዮጵያ ምድር መሆን አይችሉም።

1ኛ. ሀቀኛ ሰላምና መረጋጋት አይመጣም ፥ ሰላምና መረጋጋት አሁን እየገፉ ባሉበት መንገድ መምጣት አይችልም። እኛም ኖርን አልኖርን !

2ኛ. በኢትዮጵያ ምድር ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር ፣ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር ፣ ሀቀኛ ፌዴራላዊና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ፣ በነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ስልጣን ላይ የሚወጣ መንግሥት ፣ የህዝቡን ይሁንታ ካጣ ከስልጣን የሚወርድ መንግሥት መፍጠር አይቻልም።

3ኛ. በአንድ ፓርቲ ፍላጎት ፣ ሙሉ ቁጥጥር በሚመራ መንገድ የ120 ሚሊዮን ህዝብ ቁመት የሚሆን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በፍጹም አይፈጠርም።

አንድ ቀን እነሱም ሰምተው ፤ ችግሩም ደግሞ አስተምሯቸው መስመር ሊይዝ ይችላል።

እኛ እንሞክር ነበር አሁንም ያንኑ ህጋዊ እና ሰላማዊ ትግላችንን እንቀጥላለን።

በሀገሪቱ ግጭት ያባባሰው ስር የሰደደው የፖለቲካ ችግር የሚፈታው በፖለቲካዊ ንግግር ብቻ ነው። "


#OromoFederalistCongress

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#OLF " ለ4 ዓመታት ያህል በግፍ ታስረው የቆዩት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራሮች ከእስር መለቀቃቸውን " የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አመራር አቶ ጃዋር መሀመድ አወደሱ። ፖለቲከኛው ፥ በአመራሮቹ መፈታት እጅጉን እንደተደሰቱ ገልጸዋል። " መንግስት የቀሩትን የፖለቲካ እስረኞች በመፍታት የትጥቅ ግጭቶችን ሁሉ በውይይት እንዲቆሙ በማድረግ ይህንን በጎ እርምጃ ማሳደግ ይኖርበታል " ብለዋል።…
#OLF #OFC

የኦፌኮ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጡሩነህ ገምታ ከእስር የተፈቱትን የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራሮች በአካል በማግኘት " እንኳን በሰላም ከእስር ተፈታችሁ ! " በማለት በኦፌኮ ስም ደስታቸውን ገልፀዋል።

አቶ ጥሩነህ " በተለያዩ እስር ቤቶች በህገ ወጥ መንገድ የታሰሩ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ ደጋግመን እየጠየቅን ነበር " ብለዋል።

" የኦሮሞ ታጋዮች አቋምና ድጋፍ እንዲሁም በኦፌኮ እና በOLF ድርጅቶች መካከል ያለው ትብብር ለአገር ድል ወሳኝ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia