TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ቦይንግ

ዛሬ የተከሰከሰው #ቦይንግ_737_Max ከላይ በምስሉ ላይ የሚታየው አይነት አውሮፕላን ሲሆን አየር መንገዱ ካሉት በጣም #አዲስ አውሮፕላኖች አንዱ ነው። የዚህ አውሮፕላን አይነት ስሪት ጥቅምት ወር ላይ #ኢንዶኔዥያ ላይ ተከስክሶ 189 ሰዎች ሞተው ነበር።

Via Elias Mesert
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Fake Video‼️

በማህበራዊ ሚዲያ(በተለይም በfacebook) #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ ንብረት የሆነው #ቦይንግ_737 "ከመከስከሱ በፊት" ተብሎ እየተሰራጨ የሚገኘው #ቪድዮ_ሀሰተኛ ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ: ትናንት የኢትዮጵያ አየር መንገድ #ቦይንግ 737 #ET302 አውሮፕላን የተከሰከሰበት ቦታ በቁፋሮ የወጡ ነገሮችን ከላይ ባለው ፎቶ መመልከት ይቻላል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ‼️

የኢትዮጵያ አየር መንገድ #አብራሪዎቹን ለማሰልጠን የሚያስችሉ የተሟሉ ሰባት ምስለ በረራዎች ወይም የበረራ ማሰልጠኛዎች አሉት።

•በአሁን ወቅት ብቁና የተሟሉ ኪው 400፣ ቢ737 ኤን ጂ፣ ቢ 737 ማክስ፣ ቢ 767 ፣ ቢ 787 ፣ ቢ 777 እና ኤ 350 የተሰኙ ሰባት ምስለ በረራዎች አሉት።

•በዋሽንግተን ፓስት የወጣው መረጃ በመረጃ ላይ ያልተደገፈና #የተሳሳተ ነው።

•ማነነታቸው ካልታወቁ አካላት ተገኙ ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ በአለም አቀፍ ደረጃ ከበረራ ስለታገደው #ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላንን ትኩረት ለማስቀየር ነው፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር 302 ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋ #ምርመራ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት #በቅርቡ እንደሚለቀቅ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ #ነቢያት_ጌታቸው ለሮይተርስ ተናግረዋል፡፡ ሪፖርቱን ይፋ የሚያደርገው ትራንስፖርት ሚንስቴር ነው፡፡ ውጤቱ ለአውሮፕላኑ የተገጠመለት (MCAS) ሶፍትዌር #ከካፒቴኑ ቁጥጥር ውጭ አውሮፕላኑ አፍንጫውን ቁልቁል ዘቅዝቆ እንዲከሰከስ እንዳደረገው እንደሚገልጽ ይጠበቃል፡፡ #ቦይንግ ኩባንያ ሶፍትዌሩን አሻሽያለሁ ብሏል፤ በሚዲያ ዘመቻ ራሱን ለመከላከል እየሞከረ ነው፡፡

Via ሮይተርስ(በዋዜማ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከኢትዮጵያ ወደ ኬንያ ሲበር በነበረው #ቦይንግ_737_ማክስ አውሮፕን የደረሰው አደጋ ከመከሰቱ በፊት የአሜሪካ አውሮፕላን አብራሪዎች ቡድን በዚህ መሰል አውሮፕላኖች የደህንነት ስጋት እንዳለ ለኩባንያው አሳውቀው አንደነበር ተገለፀ፡፡ በቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ከዚህ ቀደም በኢንዶኔዥያ ከደረሰው አደጋ በኋላ ሙከስ ተብሎ በሚጠራው መቆጣጠሪያ ስርዓት ላይ ችግር እንደነበረበትና በአፋጣኝ እንዲፈታ አሳስበው እንደነበር ተገልጿል፡፡ የአሜሪካው አውሮፕላን አምራች ኩባንያ፣ ቦይንግ ግን አብራሪዎች ያነሱትን ጥያቄ ወደጎን በመተው ወደ ፊት የበረራ መቆጣጠሪያ ሶፍትዌሩን ለማስተካከል ቃል መግባቱን ዘገባው አክሏል፡፡ ኩባንያው ባለሙያዎቹ ያቀረቡትን ስጋት ባለመቀበሉ ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ተከስክሶ የ157 ሰዎች ህይወት ማለፉ ይታወሳል፡፡ ከችግሩ ጋር በተያያዘም በዓለም ላይ የነበሩ ሁሉም የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች እንዳይበሩ መታገዳቸው ይታወሳል፡፡

ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ቦይንግ

ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ማምረት #ሊያቆም እንደሚችል ገለጸ፡፡ ቦይንግ ከዚህ ቀደም ያመረታቸው አውሮፕላኖች ወደ በረራ ካልተመለሱ የ737 ማክስ ምርቱን ሊያቋርጥ እንደሚችል አስጠንቅቋል፡፡

ኩባንያው ይህን ያለው በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን 3 ነጥብ 4 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ኪሳራ በሩብ ዓመት ብቻ በማስመዝቡ ነው፡፡ አሁንም በዓለማቀፍ ደረጃ የበረራ ባለስልጣናት ፈቃድ ካልሰጡና አውሮፕላኖቹ ወደ ሥራ ካልተመለሱ ምርቱን ሊቀንስ በሂደትም ማምረቱን ሊያቆም እንደሚችል አስጠንቅቋል፡፡

የቦይንግ ኃላፊ ዴኒስ ሙይልበርግ ግን በመጭው ጥቅምት አውሮፕላኖቹ ወደ በረራ እንደሚመለሱ ተስፋ አድርገዋል፡፡ ‹‹ጥረታችንን ቀጥለናል፤ 737 አውሮፕላኖቻችን ችግሮቻቸው ተቀርፈው ወደ በረራ እንደሚመለሱ ተስፋ እናደርጋለን›› ብለዋል፡፡

‹‹ነገር ግን ወደ በረራ የመመለሻ ጊዜው ከተገመተው በላይ ጊዜ ከወሰደ ምርትን ከመቀነስ አልፎ የማክስ አውሮፕላኖችን ምርት ወደ ማቆም እንገባለን›› ብለዋል ኃላፊው፡፡

ባለፈው መጋቢት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን ተከስክሶ 157 ሰዎች መሞታቸውና አደጋው በጥቅምት ወር መጨረሻ አካባቢ ሌላ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን በኢንዶኔዥያ ተከስክሶ 189 ከሞቱበት አደጋ ጋር መመሳሰሉ ምርቱ ችግር እንዳለበት ፍንጭ መስጠቱ ይታወቃል፡፡ ይህንን ተከትሎም አብዛኞቹ የዓለም ሀገራት ሞዴሉን ከበረራ አግደውታል፤ ይህም ኩባንያውን ለኪሳራ ዳርጎታል፡፡

ምንጭ፡- ቢቢሲ/AMMA/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሰበር ዜና‼️ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ ቦይንግ 737 አውሮፕላን ዛሬ ጠዋት #ከአዲስ_አበባ ተነስቶ ወደ ኬንያ #ናይሮቢ ሲበር #ተከስክሶ የሰው ህይወት አልፏል። @tsegabwolde @tikvahethiopia
#ቦይንግ

አውሮፕላን አምራች የሆነው ቦይንግ መጋቢት 01 ቀን 2011 ዓ.ም በኢትዮጵያ አየር መንገድ 737 ማክስ አደጋ ከሞቱት 157 መንገደኞች እና የበረራ ሠራተኞች ቤተሰቦች ጋር ስምምነት ላይ ደረሰ።

ቦይንግ በአደጋው ለሞቱት ሰዎች ኃላፊነቱን እንደሚወስድና ተጠያቂነቱንም እንደሚቀበል በቺካጎ ከሚገኘው የፍርድ ቤት ሰነዶች መረጃ ማግኘት ተችሏል።

በምላሹም የተጎጂ ቤተሰቦች ከኩባንያው የቅጣት ካሳ አይጠይቁም።

የተጎጂ ቤተሰቦች ጠበቆች እንዳሉት ቦይንግ ለአደጋው "ሙሉ በሙሉ ተጠያቂ ይሆናል" ሲሉ ስምምነቱን እንደ ትልቅ ምዕራፍ ተቀብለውታል።

ከዚህም ዜና ጋር ተያይዞ የቦይንግ አክሲዮኖች ድርሻ 1 በመቶ፣ ወደ 218.50 ዶላር ወርዷል።

ስምምነቱ ከአሜሪካ ውጪ ያሉ እንደ #ኢትዮጵያ እና #ኬንያ ባሉ አገራት ያሉ የተጎጂ ቤተሰቦች በአገራቸው ሳይሆን በአሜሪካ ፍርድ ቤቶች ካሳ እንዲከፈላቸው መንገድ ከፍቷል።

ካሳው የሚፈጸመው በየአገራቸው ቢሆን የበለጠ ሁኔታውን ፈታኝ እንደሚያደርገውና ክፍያውም ዝቅተኛ እንደሚሆን ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።

@tikvahethiopia
#ቦይንግ

ቦይንግ የአፍሪካ ዋና መሥሪያ ቤቱን በአዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ እንደሚከፍት ማስታወቁ ተዘግቧል።

ውሳኔው ግዙፉ የኤሮስፔስ ኩባንያ ቦይንግ፤ በአፍሪካ ላቀደው የማስፋፊያ ስራ ኢትዮጵያ ከኬንያ እና ደቡብ አፍሪካ እንድትቀድም አድርጓታል።

ይህም ደግሞ ኬንያ ወይም ደቡብ አፍሪካ የቦይንግ የማስፋፊያ ቦታዎች ይሆናሉ የሚለውን ግምት ውድቅ አድርጓል።

እ.ኤ.አ. በ2023 ላይ ኢትዮጵያ እና ቦይንግ አንዳንድ የአውሮፕላን ክፍሎችን በኢትዮጵያ ለማምረት የጋራ ስምምነት አድርገዋል።

ቦይንግ በድረ-ገፁ ላይ እንዳሰፈረው " የአፍሪካ ዕምቅ የተፈጥሮ ሀብት እና እያደገ የመጣው ወጣት የሰው ሃይል በሚቀጥሉት ሁለት አስርተ ዓመታት ውስጥ በአየር ትራፊክ እና በአውሮፕላን ፍላጎት ላይ ከፍተኛ እድገት ያመጣል " ብሏል።

ቦይንግ ኩባንያ ፥ የአፍሪካውያን የመጓጓዣ አገልግሎት በሚቀጥሉት 20 ዓመታት ከ1,000 በላይ አዳዲስ ጄት አውሮፕላኖችን እንደሚፈልጉ ገምቷል።

ከእነዚህ ውስጥ 80% ነባር አውሮፕላኖችን ለማስፋት ያለመ እንደሆነ DW Africa ዘግቧል።

@tikvahethiopia